Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • May 2024
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    2728293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ጽዮን’

Powerful Thunderstorms in Texas: Millions in Houston Are Without Power

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 18, 2024

በቴክሳስ ኃይለኛ ነጎድጓድ፤ በሂዩስተን ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የመብራት ሃይል የላቸውም

Colors of Zion / የ ጽዮን ቀለማት ❖

⚡ At least four people were killed and nearly a Million are without Power as Powerful Storms Move through with 80-117 mph Winds Toppling large transmission power lines and Shattering skyscrapers Windows.

💭 “I have been reminded firsthand in recent trips from Texas to Ethiopia about the unique role the Gates Foundation plays…Mark Suzman

💭 Statement from Gates Foundation CEO Mark Suzman about Melinda French Gates

💭 የጌትስ ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ማርክ ሱዝማን ስለ ሜሊንዳ ፈረንሳዊ ጌትስ የተሰጠ መግለጫ

  • TExas
  • TEgray (Tigray)
  • TEdros (Tigray Native)
  • TEsla (Besides, Elon Musk owns Ethereum (CRYPTO: ETH = Ethiopia)

💭 Texas & Tegray (Ethiopia) Massacres + Tedros (TE) & The Queen | ትግራይና ቴክሳስ + ቴድሮስ & ንግሥቲቱ

👉 Continue reading/ሙሉውን ለማንበብ

Posted in Ethiopia, News/ዜና | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የቅድስት ልደታ ለማርያም ክብረ በዓል ከ ሰባት ዓመታት በፊት | Lideta Le Maryam Wereb

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 8, 2024

❖❖❖ ልደታ ለማርያም፡ ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ ይህች ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀባት ዕለት ናት | ምስጋና ❖❖❖

❖❖❖በሰንበት ተማሪዎች የቀረበ ወረብ ፥ የቅድስት ልደታ ለማርያም ክብረ በዓል ፩ ግንቦት ፪ሺ፱ ዓ.ም ❖❖❖

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግንቦት አንድ ቀን (የግንቦት ልደታ) የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት የሚከበርበት ዕለት ነው፡፡ ይህ ዕለት ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም “የመመኪያችን ዘውድ፣ የንጽሕናችንም መሰረት” ያላት ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም የተወለደችበት ነው፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ “ድንግል ትጸንሳለች፤ ወንድ ልጅም ትወልዳለች” [ኢሳ ፯፡፲፬] ብሎ ትንቢት የተናገረላት ያቺ ድንግል በዚህች ዕለት ተወለደች፡፡ ይህች ቀን ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት ” የወርቅ ልብስ ተጎናጽፋ ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች።” [መዝ ፵፬፡፱] ብሎ የተናገረላት ንግሥት የተገኘችባት ዕለት ናት፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም በራዕዩ “ፀሐይን የተጎናጸፈች፣ ጨረቃን የተጫማች፣ አስራ ሁለት የክዋክብት አክሊል በራሷ ላይ ያላት።”[ራዕ ፲፪፡፩] ብሎ የመሰከረላት የብርሃን እናቱ ድንግል ማርያም የተወለደችባት ቀን ናት፡፡ የእርስዋም ልደት እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውኃ ፈሳሽ ድንገት የተከሰተ ሳይሆን አስቀድሞ በትንቢት፣ በምሳሌና በራዕይ የሰውን ልጅ ድኅነት በጉጉት ሲጠባበቁ ለነበሩ ቅዱሳን ሲገለጽ የነበረ ነው፡፡

የድንግል ማርያም ልደት በነቢያት አንደበት

መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን፡ መሠረቶችዋ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፡፡ [መዝ ፹፮፥፩፡፯]

እግዚአብሔር የዝማሬና የትንቢት ጸጋን ያበዛለት ክቡር ዳዊት ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥርወ ልደት አስቀድሞ በመንፈስ ቅዱስ መነጽርነት ተገልጾለት “መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን /መሠረቶችዋ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው/” በማለት ትንቢት ተናግሯል፡፡ “የተቀደሱ ተራሮች” ያለውም የእመቤታችን ሥርወ ልደት ከቤተ መንግሥትና ከቤተ ክህነት ከሆኑት ከተቀደሱት ከኢያቄምና ከሐና የመሆኑን ነገር ሲያመለክት ነው፡፡ ይህንን ትንቢትና እውነተኛውን የእመቤታችንን የትውልድ ሀረግ አስማምታ ቤተክርስቲያን “የእመቤታችን ማርያም ትውልዷ ባባቷ በኩል ከንጉሡ ከዳዊት ወገን ነው፤ በናቷም በኩል ከካህኑ ከአሮን ወገን ነው፤ የአባቷ ስም ኢያቄም ነው፤ የእናቷም ስም ሐና ነው፡፡” ብላ ታስተምራለች፡፡

ትወፅእ በትር እምሥርወ ዕሴይ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ፡ ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከእርሷ ይወጣል፡፡ [ኢሳ. ፲፩፡፩]

ቁጥሩ ከዐበይት ነቢያት ወገን የሆነው ነቢዩ ኢሳይያስም ጥበብንና እውቀትን በሚገልጽ ስለሚመጣውም ነገር ትንቢትን በሚያናግር በመንፈስ ቅዱስ ተመርቶ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ከነገደ ዕሴይ እንደሚሆንና እርሷም ጽጌ (አበባ) የተባለ አካላዊ ቃል ክርስቶስን በሕቱም ድንግልና እንደምትወልድ ተገልጾለት “ትወፅእ በትር እምሥርወ ዕሴይ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ /ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከእርሷ ይወጣል/” በማለት ታላቅ ትንቢትን ተናግሮ ነበር፡፡ ይህች በትርም ከእሴይ ዘር የተገኘችው በዚህች ዕለት ነውና ልደቷን በታላቅ ድምቀት እናከብራለን፡፡ ይህንን መሰረት በማድረግ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም “መልካሟ ርግብ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ፤ ከእሴይ ሥር የተገኘሽ መዓዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ” በማለት በውዳሴ አመስግኗታል፡፡ “በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ” [መዝ.፻፴፩፡፲፫]” የተባለልን የአባቶቻችን ልጆች እኛም እንዲሁ እያልን እናመሰግናታለን፡፡

ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ፡ ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ፡፡ [መኃ ፬፡፰]

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት መሰረት የእመቤታችን የትውልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለው ተራራማ ሀገር ነው፡፡ በሊባኖስ ስለመሆኑ አስቀድሞ ጠቢቡ ሰሎሞን “ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ ንዒ ወተወፅኢ እምቅድመ ሃይማኖት እምርእሰ ሳኔር ወኤርሞን አምግበበ አናብስት ወእምአድባረ አናምርት /ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ ከአማና ራስ ከሳኔር ከኤርሞን ራስ ከአንበሶች መኖሪያ ከነብሮችም ተራራ ተመልከች/” በማለት ተናግሮ ነበር፡፡ የዚህ ትንቢት ምስጢርም የእመቤታችን መካነ ልደት የሊባኖስ ተራራ ስለመሆኑ የሚያጠይቅ እንደሆነ ምስክርነታቸው የታመነ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡ ትንቢቱም ሲፈጸም ቅድስት ድንግል ማርያም ግንቦት ፩ ቀን በ፲፭ ዓ.ዓ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በሊባኖስ ተራራ ተወልዳለች፡፡

ኢትዮጵያዊ ቄርሎስ የተባለው የነገረ ማርያም ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ እመቤታችን በሊባኖስ እንደምትወለድ አስቀድሞ ሰሎሞን የተናገረው ቃልም መፈጸሙን ሲገልጽ “….የአናብስት ልጅ አልኩሽ፡፡ ሰሎሞን እንዲህ ሲል እንደተናገረ፡- ሙሽራዪት ሆይ ከሊባኖስ ተራራ ነዪ፤ ከአንበሶች ጒድጓድ ወጥተሽ ነዪ፤ ከምርጥ ነገድነት የተነሣ ከሚመካ ወገን የመወለድሽ ዜና እጅግ ግሩም ነው፡፡” በማለት አመስጥሮታል፡፡ እመቤታችንም በሊባኖስ ተራራ እንድትወለድ ምክንያት የሆነው በማሕፀን ሳለች የአርሳባንን ልጅ ዓይን በማብራቷና ሳሚናስ የሚባለውን የጦሊቅን ልጅ ከሞት በማስነሳቷ አይሁድ በቅናት ተነሳስተውባቸው ስለነበር ሐናና ኢያቄም ወደ ሊባኖስ ተራራ እንዲሄዱ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለኢያቄም ተገልጾ ስለነገራቸው እንደሆነ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት ያስረዳሉ፡፡

የድንግል ማርያም ልደት በራዕይና በምሳሌ

ከትንቢቱ በተጨማሪም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት በራዕይና በምሳሌም አስቀድሞ የተገለጸ ነበር፡፡ ከእነዚህም መካከል ከእርሷ ሰባት ትውልድ አስቀድሞ ለነበሩት ደጋግ ሰዎች እንዲሁም ለእናትና ለአባቷ የተገለጹት ምሳሌዎች በቅዱሳት መጻሕፍት በሰፊው ሰፍረው ይገኛሉ፡፡

ሰባተኛዪቱ እንቦሳ ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃዋ ደግሞ ፀሓይን ስትወልድ አየሁ (ቴክታ)

በቅድስና የሚኖሩ ነገር ግን መካን የነበሩት ቴክታና ጴጥርቃ ነጭ እንቦሳ ከበረታቸው ስትወጣ ፤ እንቦሳይቱ እንቦሳ እየወለደች እስከ ስድስት ስትደርስ ፤ ስድስተኛዪቱ ጨረቃን ጨረቃዋም ፀሐይን ስትወልድ አይተው በሀገራቸው መፈክረ ሕልም (ሕልም ፈች ሊቅ) አለና ሂደው ነገሩት፡፡ ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ፤ ጨረቃይቱ ከፍጡራን በላይ የምትሆን ልጅ ትወልዳላችሁ፡፡ የፀሐይ ነገር ግን አልተገለጸልኝም፤ እንደ ነቢይ እንደ ንጉሥ ያለ ይሆናል አላቸው፡፡ እነርሱም ጊዜ ይተርጉመው ብለውት ሄዱ፡፡ ከዚህ በኋላ ልጅ ወለዱ፡፡ ስሟንም “ረከብኩ ስእለትዬ፤ ረከብኩ ተምኔትዬ” /የተሳልኩትን አገኘሁ፤ የተመኘሁትን አገኘሁ/ ሲሉ “ሄኤሜን”አሏት፡፡ ሄኤሜን ዴርዴን፤ ዴርዴ ቶናን፤ ቶና ሲካርን፤ ሲካር ሄርሜላን፤ ሄርሜላ ሐናን ወለደች፡፡ ሐና ለአካለ መጠን ስትደርስ ከቤተ ይሑዳ ለተወለደ ኢያቄም ለሚባል ደግ ሰው አጋቧት፡፡ ከኢያቄምና ከሐናም በጨረቃ የተመሰለች ድንግል ማርያም ተወለደች፡፡

ፀዓዳ ርግብ ሰባቱ ሰማያትን ሰንጥቃ መጥታ በማሕፀኔ ስታድር አየሁ (ቅድስት ሐና)

ኢያቄምና ሐና መካን ስለነበሩ እግዚአብሔር ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ ጸልየው፤ ሲሰጣቸውም መልሰው ለእርሱ እንደሚሰጡ ስዕለትን ተስለው ነበር፡፡ ጸሎታቸው ሲደርስ ለሐና በሕልም ተገልጾላት ለባለቤቷ ለኢያቄም “ብእሴሃ አነኑ ርኢኩ በሕልምየ ርግብ ጸዐዳ መጽአት ኀቤየ ወነበረት ዲበ ርእስየ ወቦአት ውስተ እዝንየ ወኀደረት ውስተ ከርሥየ /ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብቶ በማሕፀኔ ስትተኛ አየሁ፡፡” ብላዋለች፡፡ የዚህ ራእይ ምስጢርም ርግብ የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስትሆን፤ ፀዓዳ (ነጭ) መሆኗ ንጽሕናዋ፣ ቅድስናዋ፣ ዘላለማዊ ድንግልናዋ ነው፡፡ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማሕፀኔ ስትተኛ አየሁ” ማለቷ ብሥራተ ገብርኤልን በጆሮዋ ሰምታ በግብረ መንፈስ ቅዱስ አምላክን የምትፀንሰውን ንጽሕት ርግብ የተባለችውን እመቤታችንን የምትወልድ መሆኗን ሲያጠይቅ ነው::

ከሰባተኛው ሰማይ ነጭ ዖፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ (ቅዱስ ኢያቄም)

በተመሳሳይ ኢያቄምም በሕልሙ ያየውን ለባለቤቱ ለሐና “እንዘ ይትረኀዉ ሰብዐቱ ሰማያት ዖፍ ጸዐዳ መጽአ ኀቤየ ወነበረ ዲበ ርእስየ /ሰባቱ ሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ዖፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ” ብሎ በሕልሙ የተገለጸለትን ነግሯታል፡፡ የዚህም ራዕይ ምስጢር ዖፍ የተባለው አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን፤ ነጭነቱ ንጽሐ ባሕርዩ ነው፡፡ ኢያቄም “ከላይ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ” ማለቱ የኢያቄምን ባሕርይ ባሕርይ እንደሚያደርግ የሚያጠይቅ ሲሆን ሰባቱ ሰማያት የተባሉ የጌታችን ልዩ ባህርይው፣ ምልአቱ፣ ስፍሃቱ፣ ርቀቱ፣ ልእልናው፣ ዕበዩና መንግስቱ ናቸው።

የድንግል ማርያም ልደት በሐዲስ ኪዳን ሊቃውንት

የሐዲስ ኪዳን ሊቃውንትም ትንቢተ ነቢያትንና ወንጌልን በማጣጣም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት አመስጥረው አስተምረዋል፤ አመስግነዋል፤ ተቃኝተዋልም፡፡ የእርሷን ልደት እጅግ ብዙ ሊቃውንት በስፋትና በጥልቀት ያመሰጠሩት ሲሆን ለምሳሌ ያህል የሚከተሉት ይጠቀሳሉ፡፡

ማርያምስ ከጥንት ጀምሮ በአዳም ባሕርይ ውስጥ እንደ ነጭ ዕንቁ ታበራለች (ቅዱስ ያሬድ)

ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ስለእመቤታችን ልደት “ማርያምሰ ተኀቱ እምትካት ውስተ ከርሱ ለአዳም ከመ ባሕርይ ጸዓዳ/ ማርያምስ (ማርያም ግን) ከጥንት ጀምሮ በአዳም ባሕርይ ውስጥ እንደ ነጭ ዕንቁ ታበራለች፡፡” በማለት እርሷ በደፈረሰው ዓለም በንጽሕና፣ በቅድስናና በድንግልና ስታበራ እንደነበርና ኋላም የዓለም ብርሃን የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን መውለዷን አመስጥሮ ተናግሯል፡፡ በተጨማሪም ስለ ሥርወ ልደቷ “እንተ በምድር ሥረዊሃ ወበሰማይ አዕጹቂሃ…ሐረገ ወይን/ ሥሮቿ በምድር ጫፎቿም በሰማይ ያሉ…የወይን ሐረግ” በማለት የተወለደችው በምድር ከነበሩት ኢያቄምና ሐና መሆኑን የወለደችው ግን ሰማያዊውን ንጉሥ እንደሆነ በማመስጠር ዘምሯል፡፡ በዚህም ሰውና እግዚአብሔርን ያገናኘች መሰላል መሆኗል ገልጾ አስተምሯል፡፡

ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም፤ በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐናና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ (አባ ሕርያቆስ)

የብህንሳው ሊቀ ጳጳስ አባ ሕርያቆስም በቅዳሴ ማርያም “ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ/ ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም፤ በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐናና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ” በማለት የድንግል ማርያም ጽንሰትና ልደት እንዴት እንደነበር በድርሰቱ አስፍሮታል፡፡ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት የሚላት የሁላችን እናት ድንግል ማርያም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐናና ከኢያቄም ነሐሴ ፯ ቀን ተፀንሳ ከዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በኋላ ግንቦት ፩ ቀን ተወልዳለች፡፡ እርስዋም ስትፀነስ ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ ከጥንተ አብሶ (original Sin) ጠብቋታል፤ አበሳው አልነካትም፡፡ ይህንንም ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ በኃጢአት በተከበበ፣ መርገም በሞላበት ዓለም ውስጥ ከኃጢአት ከበደል ርቃ (ተለይታ) እንደ ጌዲዮን ጸምር በንጽህና የጠገኘች ንጽህት ዘር መሆኗን ሲያስረዳ “የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ሰዶም በሆንን እንደ ገሞራም በመሰልን ነበር፡፡”[ኢሳ.፩፡፲፱]በማለት ተናግሯል፡፡ እንዲሁም ጠቢቡ ሰሎሞን ንጽህናዋን በትንቢት መነጽር አይቶ “ወዳጄ ሆይ፣ ሁለንተናሽ ውብ ነው፣ ምንም ነውር የለብሽም፡፡ ሙሽሪት ሆይ ከሊባኖስ ነዪ፡፡”[መሓልይ ፬፡፯፡፲፮] በማለት በንጽህና በቅድስና ያጌጠች፣ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ያልነካት፣ የድህነታችን ምክንያት፣ የንጽህናችን መሰረት የሰው ባህርይ ከእግዚአብሔር ጋር እንዲዋሀድ ምክንያት የሆነች ንጽሕት የሰርግ ቤት ድንግል ማርያም በሊባኖስ የመወለዷን ነገር አስቀድሞ ነግሮናል፡፡

ይህች ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀባት ዕለት ናት (ቅዱስ እንድርያስ)

የቀርጤሱ ቅዱስ እንድርያስ የከበረ ስለሆነው ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ታላቅነት “ይህ በዓል በሐዲስና በብሉይ ኪዳን መካከል መገኛ ሆነ፡፡ ምሳሌዎቹ በእዉነታ፣ አሮጌው በአዲስ ቃል ኪዳን ተተኩ፡፡ ፍጥረት ሁሉ በደስታ ይዘምራል፤ የዚህን ቀንም ደስታ ይካፈላል፡፡ ይህ ዕለት (ጌታ) መቅደሱን የሰራበት ዕለት ነው፡፡ ይህ ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀበት ዕለት ነው፡፡” በማለት ገልጾታል፡፡ በእውነት የእርሷ ልደት የልዑል ማደሪያው መቅደስ የተሰራበት ዕለት ነውና ሁላችን እናከብረዋለን፡፡ በዚህም ዕለት “ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም/ እነሆ ዛሬ በእመቤታችን ልደት ደስታ ሆነ” እያልን እንዘምራለን። ይህችን የልዑል ማደሪያ እናቷ ሐናና አባቷ ኢያቄምም በእጅጉ ተደስተው በተወለደች በስምንተኛ ቀኗ ስሟን “ማርያም” ብለው ሰይመዋታል፡፡

የእመቤታችን የልደት በዓል አከባበር

አባታችን አዳም በኃጢአት ከወደቀ በኋላ፣ ንስሃ በገባ ጊዜ አምላካችን ጌታ እግዚአብሔር የድህነት ቃል ኪዳን ገባለት፡፡ ቃል ኪዳኑም “ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ” የሚል ነበር፡፡ ስለሆነም አዳም ፶፻፭፻/5500 ዘመን የሕይወት ምክንያት የሆነች የልጅ ልጁ እመቤታችን ድንግል ማርያም ከአብራኩ ከተከፈሉ ቅዱሳን ልጆቹ የምትወለድበትን ቀን ተስፋ እያደረገ ኖረ፡፡ የእመቤታችንን የድንግል ማርያምን የመወለዷን ዜና ተስፋ በማድረግ “ሴት” ይላት የነበረውን ሚስቱን ሔዋንን በእመቤታችን ምሳሌነት “ሔዋን”፣ የሕያዋን ሁሉ እናት ብሎ ሰየማት፡፡ [ዘፍ.፫፡፳] ዳግማዊ አዳም የተባለ ክርስቶስም የአዳምን ተስፋ በመስቀል ላይ በፈጸመ ጊዜ እውነተኛዋን ሔዋን (ዳግሚት፣ አማናዊት ሔዋንን) ድንግል ማርያምን በዮሐንስ ወንጌላዊ በኩል ለሕያዋን ምዕመናን ሁሉ እናት አድርጎ ሰጠ፡፡ [ዮሐ. ፲፱፡፳፮] ይህን የከበረ ምስጢር የማይረዳ “ክርስቲያን” እንዴት ያሳዝናል!? እኛ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ግን የቀዳማዊ አባታችንን የአዳምን፣ እንዲሁም በዳግም ተፈጥሮ ያከበረንን ዳግማዊ አዳም የተባለ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ቃል ተቀብለን “የሕያዋን ሁሉ እናት” ድንግል ማርያምን ልደቷን በፍፁም ደስታ እናከብራለን፣ ከተወደደ ልጇ ምሕረትን ትለምንልን ዘንድም ወደ እርሷ እናንጋጥጣለን፡፡

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያለን ምዕመናን ከጌታችን ልደት ቀጥሎ በታላቅ ድምቀት የምናከብረው የልደት በዓል የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም የልደት ቀን ነው፡፡ ስለ ቅዱስ ዮሐንስ “በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።”[ሉቃ ፩፡፲፬] ከተባለ የድንግል ማርያም ልደት ምንኛ የሚያስደስት ይሆን?! የነቢያቱ ትንቢት የተፈፀመበት፣ የታየው ራዕይም በገሀድ የተከናወነበት፣ የብሉይ ኪዳን ማብቂያ የሐዲስ ኪዳን መጀመሪያ ናትና ልደቷ ለሰው ልጆች ሁሉ (ለሕያዋን ሁሉ) ታላቅ የደስታ ቀን ነው፡፡ ሰማያውያን ቅዱሳን መላእክትም በንጽህናዋ በቅድስናዋ ተደንቀው “እህትነ ነያ/እህታችን እነኋት” ብለው ያመሰግኗታል፡፡ በዘመናችን ያሉ የሰዎች ልደት በድምቀት የሚከበር ከሆነ ለሰው ልጅ መዳን ምክንያት የሆነች የአምላክ እናት የተወለደችበት ቀን ምንኛ ሊከበር ይገባው ይሆን?! ቤተ ክርስቲያን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት በታላቅ ድምቀት የምታከብረው ከዚህ ታላቅ በዓል በረከት ረድኤትን እንድናገኝበት ነው፡፡ የሕይወት ክርስቶስ እናት ዛሬ ተወልዳለችና፡፡

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትዉፊት መሰረት ሐና እና ኢያቄም ከአይሁድ ለማምለጥ ተሰደዉ በአድባረ ሊባኖስ ስር እመቤታችንን ወለዱ፡፡ በወቅቱ ከቤት የወጡት ለሽሽት ነበርና ስንቅ ስላልያዙ ምግባቸዉ “ንፍሮና ጥራጥሬ” ነበር፡፡ይህንን ትዉፊት በመያዝ በዓሉ ከቤት ዉጭ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡ነገር ግን በበጎ ነገሮች ሰበብ ክፉ ዓላማዉን ማስፈጸም የሚፈልገዉ ዲያቢሎስ በማር መካከል መርዝን ከሚጨምርባቸዉ መንፈሳዊ በዓላት አንዱ የግንቦት ልደታ (የእመቤታችን የልደት በዓል) ነዉ፡፡ በዚህ ዕለት አንዳንዶች ባለማወቅ ሌሎች ደግሞ በድፍረት “ለአድባር አዉጋር ነዉ፤ ቆሌዉን ለመለመን ነዉ” እያሉ ለማያውቁት አምልኮ ንፍሮ የሚበትኑ፣ ቡና የሚረጩ፣ ቅቤ የሚቀቡ፣ የከብት ደም የሚያፈሱ አሉ፡፡ እውነታው እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸው፡፡ እኛ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ግን እነዚህን የሃይማኖት ለዋጮች ሥራቸውን እንጸየፋለን፡፡ ስለሆነም ከእንደዚህ ዓይነቱ ባዕድ አምልኮ በመለየት ይህንን ታላቅ በዓል በተገባና በተረዳ ነገር ልናከብረው ይገባል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን በሠራችልን ሥርዓት መሰረት በቀናች በተዋሕዶ እምነት ሆነን፤ በምሕረቱ የጎበኘንን አምላካችንን ብቻ እያመለክን፤ የድኅነታችን ምክንያት የሆነችውን ድንግል ማርያምንም እያመሰገንን ልናከብረው ይገባል፡፡

አምላካችን እግዚአብሔር ከእመቤታችን ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡ አሜን፡፡

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

The Good Friday procession of the Ethiopian Orthodox Church in Jerusalem | ስቅለት በኢየሩሳሌም

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 3, 2024

✞ ኢትዮጵያ ከዘመነ ሙሴ ጀምሮ አምልኮተ እግዚአብሔር የሚታወቅባትና ሰሟም በቅዱስ መጽሐፍ በየቦታው የተጠቀሰ ከመሆኑም በላይ የኢትዮጵያውያንና ቅድስት ሃገር ኢየሩሳሌም ግንኙነት ከብሉይ ኪዳን እስከዛሬም ያልተቆረጠ ሲሆን ይህም በብዙ ታሪክ ዘጋቢዎች ፡ ጽሁፎች ፣ ተረጋግጧል። በመሆኑም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአሁኑ ጊዜ በእስራኤል አገር ሰባት ገዳማት ይዛ መገኘት ለዚህ ምስክር ነው።

✞ የገዳማቱ ዝርዝር፦

  • ፩. ዴር ሱልጣን ገዳም በ፫፻፳/ 320 ዓ.ም/ በአሮጌው ከተማ ውስጥ በጌታ መቃብር አጠገብ/
  • ፪. ደብረ ገነት ገዳም በ፲፰፻፶/ 1850 ዓ.ም ተመስርቶ / በኢየሩሳሌም ከተማ የሚገኝ/
  • ፫. ቅዱስ ፊሊጶስ ገዳም በ ፲፰፻፹፫/ 1883 ዓ.ም /ኢየሩሳሌም ከተማ /
  • ፬. ቅድስት ሥላሴ ገዳም በ፲፱፻፲፭/ 1915 ዓ.ም /ዮርዳኖስ ወንዝ አሁን ኢያሪኮ ድርብ/
  • ፭. ቅዲስ ገብርኤል ገዳም በ፲፱፻፳/ 1920 ዓ.ም/ ኢያሪኮ ከተማ/
  • ፮. ምስካነ ቅዱሳን ዓልዓዛር ገዳም በ፲፱፻፵፭/ 1945 ዓ.ም/ ቤታንያ/
  • ፯. ቤተልሄም ገዳም በ፲፱፻፹፪/ 1982 ዓ.ም/ ቤተልሄም/

እነዚህም ገዳማት ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዓማኞች ብቻ ሳይሆን ለማንኛውም ኢትዮጵያዊና ለመላው ጥቁር ሕዝብ ጭምር ኩራት በመሆናቸው፣ የገዳማቱ ታሪክ ይዘት እንዲጠበቅ ሁሉም ባለው ዓቅምና ሙያ ሊሳተፍ ይገባል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ካሏት ፯/7 ገዳማት ውስጥ ፮/6ቱ በገዳሙ መነኮሳት ማህበር ቁጥጥር ስር በመሆናቸው ሁሉም ከተባበረ የሚፈለገውን የማሻሻል ስራ ማከናወን ይቻላል።

ዋናውና አንገብጋቢው ግን ጌታ በተቀበረበት በጎልጎታ ለረጅም ጊዜ በዙ ያለም መረጃዎች እንደሚያረጋግቱት እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በዋናው ጎልጎታ ውስጥ የነበሩን እራት መቅደሶች ተወስደው የቀረንም አንዱ ይዞታችን በአንደኛ ተራ ቂጥር የተጠቀሰው የዴር ሡልጣን ገዳም በመባል የሚታወቀው ነው።የዴር ሡልጣን ገዳማችን ያለበትን ውጣ ውረድ ሕዝብ ሊያውቀውና ሊሳተፍ ባለመቻሉ ዓቅማችን ደካማ በሆነበት ጊዜ በግፍ ከመነጠቃችንም በላይ ከንጭራሱ ከዚያ ደብዛችን እንዲጠፋ የማያቋርጥ ተጽዕኖ ቁልፉን በያዙት ግብጾች ከፍተኛ ተጽዕኖ በመነኮሳቱ ላይ በመደረግ ላይ መሆኑ ነው።

የዴር ሡልጣንን ገዳም በሚመለከት በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጽህፈት ቤት እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር 2000 ዓ ም የተዘጋጀው ጸሁፍ የገዳሙን ታሪኩንና ችግሩን ያካተተ በመሆኑ ጽሁፉን እንዳለ ኢትዮጵያውንን ለማሳወቅ ሰለሚረዳ ከዘህ በታች ሙሉውን እንዳለ ለንባብ አቅርበነዋል።

✞ “ደብረ ሥልጣን (ዴር ሡልጣን)

ይህ በጎልጎታ ከጌታችን መቃብር አጠገብ ተያይዞ የሚገኘው የዴር ሡልጣን መድሃኔዓለም የኢትዮጵያ ገዳም ነው

ዴር ሡልጣን ፦ሥያሜው በግዕዝ ደብረ ሥልጣን ፥ በዓረብኛ ሡልጣን ሲሆን ይህ ገዳም የሚገኘው ከጌታ ቅዱስ መቃብር ቤተመቀደስ በስተምስራቅ ከቅድስት ዕሌኒ ቤተመቅደስ በላይ ነው።ዴር ሡልጣን ማለት “የንጉሥ/የመሪ/ገዳም” ማለት ሲሆን እንደ ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት ትርጓሜ ሥያሜውን ያገኘው ቦታው ጥንቱንም ንጉስ ሰሎሞን ከኢትዮጵያ ለበዓላት ለሚመጡ መንገደኞችና መልዕክተኞች ማረፊያ እንዲሆን ለንግስት ሳባ የሰጣት በመሆኑና ኋላም በክርስትናው ዘመን ገዳም ተመሥርቶበት በኢትዮጵያውን ነገስታት ሲረዳ የኖረ መሆኑ ነው።

1. መሰረታዊ ታሪክ፦

የኢትዮጵያውያንና የቅድስት ሀገር ትውውቅ እስከ ብሉይ ኪዳን ይዘልቃል።

· ከክርስቶስ ልደት በፊት ዝነኛው የንግሥተ ሳባና የንጉስ ሰሎሞን የኢየሩሳሌም ግንኝነትነው /1ኛ ነገ 10፡1᎗13/።

· በሐዲስ ኪዳን ያለው ትውውቅ የመጀመሪያው ደግሞ ከጌታ ልደት በኋላ ትንቢተ ኢሳይያስን እያነበበ በሠረገላው ሲጓዝ ቅዱስ ፊልጶስ በመንፈስ ተልኮ ያስተማረውና ያጠመቀው ኢትዮጵያዊ

ጃንደርባ ታሪክ ነው። / የሐዋ ሥ ም 8፡26/

· በ380 ዓ ም ሁለቱ የቅዱስ ጀሮም ደቀመዛሙርት ቅድስት ፓውላን ልጇ ቅድስት ኢዮስቶቹም ሮም ለሚገኙት ሊይታና ማርሴላ ለተባሉት ጓደኞቻቸው ወደ ኢየሩዳሌም መጥታችሁ ኑሩ በማለት በላቲን በጻፉት ሁለት ደብዳቤዎች ላይ በየቀኑ መነኮሳ,ት በቡድን ከህንድ፡ ከፋርስና ከኢትዮጵያ ወደ ኢየሩዳሌም እንደሚደርሱ አመልክተዋል። /ደብዳቤችን መፈለግና ማቅረብ/

· በ636 ዓ ም ከሊፋ ዑመር ኢብንኧልኸታብ ኢየሩሳሌምን ከተቆጣጠረ በኋላ ለክርስቲያኖች ,በሰጠው ቃልኪዳን (ኦማራይት ኮብናንት) ላይ “ ,,,, በኢየሩሳሌም ውስጥ ከሚኖሩት ሌሎች ክርስቲያኖችም ማለት ጆርዳናውያን፡ኢትዮጵያውያን(ሀበሾች) እንዲሁም ቅዱሳት መካናትን ለመሳለም(ለመጎብኘት) የሚመጡ እውሮፓውያን ኮፕቶች (ግብጻውያን)፡ አሶራውያን (ኩርዶች),,,” የመለው ንባብ የኢትዮጵያውያን ማህበር ከሌሎች ለመሳለም ከሚመጡት አንጻር እንደ ነዋሪ እንደሚታዩ ያረጋግጣል።

በኋላ ዘመንም ቢሆን የኢትዮጵያውያንና የቅድስት አገርን ግንኙነት በተለይም ደግሞ የያዟቸውን ይዞታዎች በትክክል የሚያሳዩ መረጃዎች በብዙ ተሳላሚዎ ች ጽሁፍ በነገስታት አዋጆችና ሌሎች እንደ ሽሪዓ ፍርድ ቤት ድንጋጌዎች ባሉት ውስጥ ይገኛል።

· በ786 ዓ ም ዊልባልድ የተባለ ጅርመናዊ ጳጳስ በገሊላ አንድ ኢትዮጵያዊ ተሳላሚ እንዳገኘ አመልክቷል።

· በ1323 ዓ ም ሁለቱ ፍራንሲስካን መነኮሳት ሲሞና ኹጎ የኢትዮጵያውያንን የቅዳሴ ሥርዓት እንደተሳተፉ ሲገልጹ ይህ ዓይነት ቅዳሴ በጎልጎታ ውስጥ በምትገኘው የቅድስት ማርያም ቤተመቅደስና በቅዱስ ሚካኤል መቅደስ የሚካኬድ እንደሆነ እንዲሁም በ1374 ዓ ም ሂኮሎ ዳ ፖጌቦንሲ የተባለ አባት ገልጻል።

· ከ27 ዓመት በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም የመጣው ሊዎናርዶ ፍሪስኮባልዲ ኢትዮጵያውያን አራት መቅደሶች እንዳሏቸውና ከእነዚህም አንዱ የቅዱስ ሚካኤል መቀደስ መሆኑን ሲገልጽ ሌሎች መንገደኞች ለምሳሌ እንደጀርመናዊው ሲባልድ ሬይተርና ጅሃን ተኑድ ያሉት ይኸንኑ ደግመው አረጋግጠዋል።

· በ1517 ዓ ም በሡልጣን ሳሌም በተሰጠ አዋጅና በ1550 በንጉስ ሱልጣን ሱሌይማን የጸናው የኢትዮጵያውያንን ይዞታ የሚዘረዝር አዋጅ ላይ ስለዴር ሡልጣን እንዲህ ተጽፏል።” በስተደቡብ በኩል የሚከፈተው ታችኛው የኢትዮጵያውያን ቤተመቅደስና በመካነ መቃብሩ ቤተክርስቲያን የሚገባው የሡልጣን ገዳም (ዴር ሱልጣን ከነቤቶቹና ከነመኖሪያዎቹ የኢትዮጵያውያን ንብረት ነው።”

· በተጨማሪም በ1530 ዓ ም ፈረንሳዊ ተሳላሚ ዴንስ ፖስት “,,,, አብረሃም ልጁን ይስሃቅን በሰዋበት ቦታ ሀበሾች የሚባሉት ጥቁር ህዝቦች ቤተመቅደስ ይጠብቃሉ፣ በተጨማሪም አብረሃም ልጁን ሲሰዋ ያምር እንደነበር የሚያምር የወይራ እንጨት አለበት፡” በማለት ከነትውፍታዊ መረጃው አረጋግጧል።

· ከዚህ ሌላ ፍራንሲስኮ ቨርኔሮ በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን “ ,,,እነርሱ (ኢትዮጵያውያን) ክጌታ ቅዱስ መቃብር ቤት መቅደስ አደባባይ ፊት ለፊት ቤተመቅደስ አላቸው። በዚያም ጥቂት ጠበብ ያሉ ጨለማ ክፍሎች አሉ። በዚያው ባዶ መሬት ላይ ይተኛሉ” ሲል በዘመኑ የነበሩ ኢትዮጵያውያን በዴር ሱልጣን ያሳለፉትን የተጎሳቆለ ኑሮ አስቀምጧል።

የኢትዮጵያውያን መነኮሳት ከ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በፊት የተከበረ ማህበር እንደነበራቸው ብዙ መረጃዎች ያመለክታሉ።

· በ1531ና በ1547 ሁለት የኢየሩሳሌም የሸሪዐ ካውንስል ድንጋጌዎች የሚያሳዩት የኢትዮጵያውያን ማህበር እለቃ ከጥንት ጀምሮ ከግሪክ ፓትርያርክ ሳይቀር ቀድሞ የቅዳሜ ሥዑር ዕለት ከጌታ መቃብር /ጎልጎታ/ ውስጥ ብርሃን ያወጣ እንደነበር ሲያረጋግጥ ፣

· በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ነገስታት ለምሳሌ አጼ ዐግብዐጽዮን በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን እና አጼ ዘርአያዕቆብ በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኢየሩሳሌም ለሚኖሩ መነኮሳት የጻፏቸው ደብዳቤዎች የኢትዮጵያውያን ማህበር ከነገስታቱ በቂ ድጋፍ ይደረግላቸው የነበረ መሆኑን ያሳያል።

· ይሁን እንጂ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የግራኝ መሐመድ መነሳትና በኋላም የዘመነ መሳፍንት መከሰት ምክንያት ግንኙነቱ በመቋረጡ አንዳንዶቹ ኢትዮጵያውያን መነኮሳት ወደ አውሮፓ ለመሰደድ በቅተዋል። ችግሩን ችለው የታሪክና የቅድስና ቦታቸውን ለመጠበቅ በኢየሩሳሌም የቀሩትም በጎልጎታ ውስጥ ያላቸውን መብት በግፍ ከመነጠቃቸውና በዴር ሡልጣን ከመወሰናቸውም ሌላ ከላይ ፍራንሲስኮ ቭርኖሮ ለገለጸው ዓይነት መራራ ኑሮ ተዳርገዋል። ይሁን እንጂ ዘመን መሳፍንት አክትሞ ዘመነ ነገስታት ሲተካ ለማህበሩ የሚደረገው ድጋፍ ቀጥሏል።

መላ ያጣው ክርክር፡

· በ1774 ዓ ም የኢትዮጵያ መነኮሳት ኢብራሂም ጁሃሪ የተባለውን ግብጻዊ ከአገልጋዮቹ ጋር በእንግድነት ያስጠጉታል። ውሎ አድሮ አለቃ ልሁን ማለት ይገምራል።

· ይሁን እንጂ እንደ ጳጳስ ሳሙኤል ጎባትና የብሪታንያ ቆንስል ጀምስ ፊን ኮፕቶች በዴር ሡልጣን ላይ ግልጽ የይገባኛል ክርክር ያነሱት በገዳሙ በ1838 ዓ ም ከተከሰተ የተስቦ ወረርሽኝ በኋላ ነው።በዚህ ወረርሽኝ የኢትዮጵያ መነኮሳት በተስቦ ሲያልቁ ኮፕቶች በአርመን ጳጳስ እርዳታ የዴር ሡልጣንንና የሁለቱን ቤተመቅደሶች ቁልፍ ከተረፉት መነሎሳት እጅ በጉልበት ይነጥቃሉ። ከዚያም በኋላ በማጽዳት ስም ቦታውን ለማቃጠል እንዲፈቀድላቸው በወቅቱ የኢየሩሳሌም አስተዳዳሪ ክነበረው ግብጻዊ ኢብራሂም ፓሻ ይጠይቃሉ ። በአጋጠማቸው ዕድል ተጠቅመው የኢትዮጵያውያንን ትልቅ ቤተመጻሕፍት ያቃጥላሉ።

· ከዚህ በኋላ በባይዛንታይን ዘመን በአብርሃም ገዳም ምክንያት የተነሳውን ክርክር ይዘው ይገባናል በማለት ጥያቄ ያቀርባሉ። ነገር ግን በወቅቱ የነበሩት ቱርኮች በአብርሃም ገዳምና በዴር ሡልጣን መካከል ልዩ ነት እንዳለ አስረድተው በ1846 ዓ ም እምቢ ይሏቸዋል። ቢሆንም ግን በተለያዩ ጊዜያት በተደረጉት ድርጊቶች የቱር`ክ አስተዳደር ለግብጾች ማድላቱን የተለያዩ መረጃዎች አመልክተዋል።

· በ1850 በሳሙኤል ጎባት ምክር የኢትዮጵያውያን የዴር ሡልጣንን ቁልፍ መልሰው እጅ አደረጉ። በመቀጠል በ1890 ዓ ም ኮፕቶች የሰሚኑን ግድግዳ ለማፍረስ ፈልገው ኢትዮጵያውያኑ መነሎሳት አምርረው በመቃወማቸው የቱርክ መንግስት በይርጋ ደንብ መሰረት አግዷቸዋል።

· በዚህም ንዴት የሁለቱን መቅደሶች ቁልፎች ለውጠው ዘጉ። እስከ 1870?ዓ ም ለኢትዮጵያውያን ዝግ ሆነው በቆየበትም ወቅት ኢትዮጵያውያን የትንሣኤን በዓል በድንኳን ለማክበር ተገደዱ። ሆኖም አጼ ሚኒልክ በደጃዝማች መሸሻ መሪነት የላኩት የልዑካን ቡድን በሰበሰበው መረጃና ኋላም በተገኙት መረጃዎች መሰረት ለጆርዳን መንግስት አቤቱታ ቀርቦ ክ8 ዓመት ጥናት በኋላ በ1881 የጆርዳን መንግስት ለኢትዮጵያን ወሰነ። በውሳኔው መሰረት ኢትዮጵያውን መነኮሳት ለ40 ቀን ብቻ ቁልፉን ከያዙ በኋላ በግብጽ መንግስት ጣልቃ ገብነት ውሳኔው ተቀልብሶ ኮፕቶች መረጃ ያቀርባሉ በሚል ሰበብ ቁልፉን እንዲመልሱ ተደረገ።ነገር ግን የኢትዮጵያውያን መነኮሳት ተገቢውን ምላሽ እንዲሰጡም ሆን ተጨማሪ መረጃ እንዲያቀርቡ ዕድል ሳይሰጣቸው እስከ 1871 ዓ ም ድረስ ጉዳዩ ተዘግቶ ቆየ።

· በ1971 ዓ ም የእስራኤል የሚኒስትሮች ምክር ቤት እንደገና አይቶት ችግሩ እስኪፈታ ድረስ አሁን ባለው መልኩ ኢትዮጵያውያን ገዳሙን እንዲያስተዳድሩ ሲል ወሰነ።ኢትዮጵያውያውያንም የቤተመቅደሶቹን ቁልፎች እጅ እደረጉ።

✞ The Ethiopian Orthodox Church has maintained a quiet presence in Jerusalem for more than 1,500 years, with some people claiming that there has been an Ethiopian delegacy in the Holy Land ever since the famed meeting of the Queen of Sheba and King Solomon some 3,000 years ago.

For many centuries, the center of the Ethiopian Church in Jerusalem was a small courtyard with several structures behind the Church of the Holy Sepulcher in the Christian Quarter of the Old City. Today, however, the Church has to a large extent relocated outside the walls to the western city. The move began in the 19th century, when a succession of powerful Ethiopian monarchs decided to establish a strong presence outside Africa. In 1888, Ethiopian Emperor Yohanes bought a large plot of land and began construction of a new church and monastery. The complex eventually lent its name to the road on which it is situated – Ethiopia Street.

The new church is an impressive structure in a secluded courtyard, built in the circular style reminiscent of other Ethiopian churches. The complex is usually a haven of tranquility in the heart of downtown Jerusalem, but during Easter things pick up, and it is recommended to visit and witness the lively services. Remember to take off your shoes at the entrance as this is a requirement of the Ethiopian rite.

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የጌታችን ስቅለት | በዚያን ዕለት የከርስቶስ ልጆች ክርስቲያን፤ የክርስቶስ ተቃዋሚው ልጆች እስላም ተባሉ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 3, 2024

ጌታችን ሲሰቅል የሚከተሉት ሰባት ተአምራት ተፈጽመዋል፤

  • ፩. ፀሐይ ጨለመ፤
  • ፪. ጨረቃ ደም ኾነ፤
  • ፫. ከዋክብት ረገፉ፤
  • ፬. የቤተ መቅደስ መጋረጃ ተቀደደ፤
  • ፭. አለቶች ተፈረካከሱ፤
  • ፮. መቃብራት ተከፈቱ፤
  • ፯. ሙታን ተነሡ (ማቴ. ፳፯፥፶፩-፶፬)፡፡

ጌታም ቆላተ ዮሳፍጭ ከሚባል በረሀ አውርዶ መናውን ውሀውን ከወትሮ አብልጦ አወረደላቸውና ኃይሉን ከሂሎቱን አሳይቶ ወእንዘ ዓዲ መብልዖሙ ውስተ አፋሆሙ ነዘር እባብ አስንቶ ጐዳናቸውን እየስቀደደ አስፈጃቸው። ሙሴም አቤቱ ጌታዬ አሕዛብ ፳ኤልን የሚመግባቸው ቢያጣ ከበረሀ አውርዶ አስፈጃቸው እንዳይሉህ መድኃኒት ፈልግላቸው ብሎ ጸለየ። ጌታም የወዳጁን ጸሎት ፈጥኖ ይሰማልና ብርቱን እባብ አስመስለህ በተራራ ላይ ተራዳ ተክለህ ብርቱን በዚያ ላይ ሰቅለህ አሳያቸው ያን አይቶ ሰምቶ ያመነ ይዳን ያላመነ ይፈጸም አለው። ተራራው በቀራንዮ አምሳል ነው፤ ተራዳው የመስቀል ብርቱ የወልደ እግዚአብሔር እባብ የዲያብሎስ ቍስሉ የኃጢአት መርዙ የመርገመ ሥጋ የመርገመ ነፍስ በረኃው የገሃነም እሳት አምሳል ነው።

ያን አይተው ሰምተው ይዳኑ ማለት ስቅለተ ክርስቶስን አይተው ያመኑ ሐዋርያት፣ ሰምተው ያመኑ ምዕመናን የመዳናቸው አምሳል ነው። ያላመኑ ይፈጸሙ ማለቱ፡ ስቅለተ ክርስቶስን አይተው ያላመኑ አይሁድ ሰምተው ያላመኑ አይሁድ፣ ሰምተው ያላመኑ አሕዛብ ያለመዳናቸው አምሳል ነው።

ነፍስ ያለው እባብ የገደላቸውን ሰዎች ነፍስ የሌለው ብርት እንዳዳናቸው በባሕርዩ ሞት የሌለበት አምላክ ዲያብሎስ ያስገራቸውን ነፍሳት ተሰቅሎ ሞቶ የማዳኑ አምሳል ነው።

ጽዮን የተባለች ማኅፀነ ማርያም ደብረ መቅደሱ የተባለ አካሏ ነው

ጌታም እነዚያ አላወቁም እንጂ እኔስ በማኅፀነ ማርያም አድሬ ለጻድቃን ለሰማዕታት ነገሥሁላቸው በአይሁድ በመናፍቃን ነገሥሁባቸው ሲል ነው። አንድም ጽዮን የተባለ መሰቀሉ ደብረ መቅደሱ የተባለ አካሉ ነው

እነዚያ አላወቁም እንጂ እኔስ በመስቀል ተሰቅዬ ለጻድቃን ለሰማዕታት ነገሥሁላቸው በአይሁድ በመናፍቃን ነገሥሁባቸው ሲል ነው።

እንዲህ ፯ት ተአምራት ሲሠሩ አይተው የባሕርይ አምላክ ነው እንጂ የባሕርይ አምላክማ ካልሆነ እንዲህ ያሉ ተአምራት ባልተሠሩ ነበር ያሉ ክርስቲያን ተባሉ።

አምላክ አይደለም፣ አልተወለደም፣ አልተሰቀለም፤ የአምላክ ወዳጅ ደግ ሰው ነብይ ብቻ እንጂ ያሉት እስላም ተባሉ። እስላምና ክርስቲያን የተባለበት ያን ዕለት ነው።

መናፍቃን ካህናት አላውያን መኳንንት ከሀድያን ነገሥታት ሃይማኖታችሁን ጣሉ ፈጣሪያችሁን ካዱ ለጣኦት ስገዱ ብለው እንደ እኔ እራሳችሁን እየመቱ አክሊለ ሦክ ግንድ አሸክመው በብረት ቢቸነክሯችሁ መራር ሐሞት ቢያጠጧችሁ ዋጋችሁን በመንግሥት ተቀበሉት እንጂ ሃይማኖታችሁን አትጣሉ፤ ፈጣሪያችሁን አትካዱ፤ ለጣኦት አትስገዱ!” በማለት ጌታችን አስተምሮናል።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር።

Crucifixion | On That Day, Children of Christ Became Christians & Children of the Antichrist Muslims

✞ Today millions of Orthodox Christians commemorate Good Friday, also known as “Great Friday” to remember the events leading up to Jesus’ Crucifixion.

In Ethiopia, Good Friday is known locally as Siklet which translates to Crucifixion of the Lord Jesus Christ. It is a day of fasting, intense prayer and prostrations.

Followers of Ethiopian Orthodox Churches share the religious tradition with other Orthodox Churches. In Ethiopia, churches outside the Ethiopian Orthodox Church including Catholic celebrate the good Friday along with the Ethiopian Church.

Good Friday is the holiday that Lord and Savior Jesus Christ was crucified for the salvation of human race. He was beaten hard, spited on and dragged with a robe all the way through to Calvary.

After His capture betrayed by Judas on Thursday eve subsequent to His prayer in Gethsemane, the Jews took Him and started their torture. Early morning on this Holy Friday, Lord Jesus Christ was brought to trial in front of the Jewish leader Pilate. Convicted for a crime He did not commit, Lord Jesus was tortured and tormented until He reached to the Calvary for crucifixion. Upon it was revealed miracles including the darkening of the sun, the bleeding of the moon and the falling of the stars whilst Lord Jesus Christ separated His divine soul from His body at the ninth hour. Then after, Joseph and Nicodimus took His holy body and buried it.

✞ A chapter in one of the Prayer books (The Passion of Cross or Himamat Meskel) of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church teaches us the following very important lesson:

“They did not know, but I was crucified and reigned over the righteous and the martyrs, so the Jews who saw those 7 miracles being done, were called Christians because they said that it could only be a God of nature who is showing us these miracles, and if He was not a God of nature, such miracles would not have been done.„

And,

☪ “Those who deny the divinity of Jesus by saying, „He is not God, He was not born, He is not The Son of God, God doesn’t have a son, He was not crucified, He is only a friend of God, a good man and just a prophet; They are called Muslims, or followers of Islam. It was on that very day that Islam and Christianity were called as such.”

May God accept our prayer, fasting and all our endeavors on the great lent and redeem us; Amen!

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ከፍኖተ መስቀሉ ከህያው ቅዱስ ቃሉ በረከት ይክፈለን

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 3, 2024

❖ ዓርብ ስቅለት የዕዳ ደብዳቤያችን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ለመጨረሻ ጊዜ የተደመሰሰበት፤ ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ የወጣንበት ዕለት ስለኾነ “የድኅነት ቀን” ይባላል። ❖

✞ ፲፫ቱ ሕማማተ መስቀል

  • ፩ኛ. ተአስሮ ድኅሪት (ወደኋላ መታሰር)
  • ፪ኛ. ተስሕቦ በሐብል (በገመድ መሳብ)
  • ፫ኛ. ወዲቅ ውስተ ምድር (በምድር ላይ መውደቅ)
  • ፬ኛ. ተከይዶ በእግረ አይሁድ (በእግረ አይሁድ መረገጥ)
  • ፭ኛ. ተገፍዖ ማዕከለ ዓምድ (ከምሶሶ ጋር መላተም)
  • ፮ኛ. ተጽፍዖ መልታሕት (በጥፊ መመታት)
  • ፯ኛ. ተቀስፎ ዘባን (ጀርባን በጅራፍ መገረፍ)
  • ፰ኛ. ተኰርዖተ ርእስ (ራስን በዱላ መመታት)
  • ፱ኛ. አክሊለ ሦክ (የሾህ አክሊል መድፋት)
  • ፲ኛ. ፀዊረ መስቀል (መስቀል መሸከም)
  • ፲፩ኛ. ተቀንዎ በቅንዎት (በችንካር መቸንከር)
  • ፲፪ኛ. ተሰቅሎ በዕፅ (በመስቀል ላይ መሰቀል)
  • ፲፫ኛ. ሰሪበ ሐሞት (መራራ ሐሞትን መጠጣት)

✞ ጌታችን ሲሰቅል የሚከተሉት ሰባት ተአምራት ተፈጽመዋል፤

  • ፩. ፀሐይ ጨለመ፤
  • ፪. ጨረቃ ደም ኾነ፤
  • ፫. ከዋክብት ረገፉ፤
  • ፬. የቤተ መቅደስ መጋረጃ ተቀደደ፤
  • ፭. አለቶች ተፈረካከሱ፤
  • ፮. መቃብራት ተከፈቱ፤
  • ፯. ሙታን ተነሡ (ማቴ. ፳፯፥፶፩-፶፬)፡፡

✞ ጌታችን በመስቀል ላይ ሳለ የሚከተሉትን ሰባት ዐበይት ቃላት አሰምቶ ተናግሯል፤

  • ፩. “ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ (አምላኪየ አምላኪየ ለምን ተውኸኝ?)”፤
  • ፪. “እውነት እውነት እልሃለሁ፤ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትኖራለህ”፤
  • ፫. “አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁትምና ይቅር በላቸው”፤
  • ፬. እመቤታችንን “ሴትዮ ሆይ፣ እነሆ ልጅሽ”፤ ደቀ መዝሙሩንም “እናትህ እነኋት” በማለት የቃል ኪዳን እናትነትና ልጅነት ማከናወኑ፤
  • ፭. “አባት ሆይ በአንተ እጅ ነፍሴን አደራ እሰጣለሁ”
  • ፮. ተጠማሁ”፤
  • ፯. ዅሉ ተፈጸመ (ማቴ. ፳፯፥፵፭-፵፮፤ ሉቃ. ፳፫፥፵፫-፵፮፤ ዮሐ. ፲፱፥፲-፴)፡፡

ከሰድስት ሰዓት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ጨለማ ኾኖ ከቈየ በኋላ ከዘጠኝ እስከ ማታ እንደ ተለመደው ብርሃን ሁኖአል፡፡ “ወፍና ሠርክ ይበርህ ብርሃነ ፀሐይእንዲል (ዘካ. ፲፬፥፯)፡፡ በዚህ ዕለት ሰባት መስተፃርራን (ጠበኞች) ታረቁ፤ ተስማሙ፡፡ እነዚህም፡- ሰውና እግዚአብሔር፣ ሰውና መላእክት፣ ሕዝብና አሕዛብ፣ ነፍስና ሥጋ ናቸው (ኤፌ. ፪፥፲፤ ቈላ. ፩፥፳)፡፡ ጌታችን ጠዋት በሦስት ሰዓት ተገረፈ፤ በስድስት ሰዓት ተሰቀለ (ማቴ. ፳፯፥፩-፴፯፤ ሉቃ. ፳፫፥፩-፵፬፤ ዮሐ. ፲፱፥፩)፡፡

ጌታችን በውኃው ተጠምቀን፣ ደሙን ተቀብለን የእግዚአብሔር ልጆች እንኾን ዘንድ ከቀኝ ጎድኑ ጥሩ ውኃ፣ ትኩስ ደም አፈሰሰልን (ዮሐ. ፲፱፥፴፬)፡፡ በዐሥራ አንድ ሰዓት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከመስቀል አውርደው ሽቶ እየረበረቡ በድርብ በፍታ ገንዘው ቀበሩት (ሉቃ. ፳፫፥፶-፶፬፤ ዮሐ. ፲፱፥፴፰-፵፪)፡፡ ነፍሱ ወደ ሲኦል ወርዳ ነፍሳትን ነጻ አወጣች (፩ኛ ጴጥ. ፫፥፲፱)፡፡ በዚህ ጊዜ በርሃነ መለኮቱ በሲኦል ተገለጠ፡፡ ስለዚህም “ንሴብሖ ለ እግዚአብሔር እየተባለ ይዘመራል፡፡ ከሆሣዕና አንሥቶ ተከልክሎ የነበረው ኑዛዜ ይናዘዛል፤ ጸሎተ ፍትሐት ይደረጋል፡፡

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ረቡዕ የምክር ቀን፤ ይሑዳ ጌታችንን አሳልፎ ሰጠ | የዘመኑ ይሑዳዎች ዛሬም ጌታቸውን፣ ሀይማኖታቸውን፣ ሕዝባቸውን እና ሃገራቸውን ለገንዘብና ለስጋዊ ጥቅም ብለው እየሸጡ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 1, 2024

ሰሙነ ሕማማት – ረቡዕ ፤ የይሁዳ ክህደት፥ ምክረ አይሁድ፥ የዕንባ ቀን፥ የመልካም መዓዛ ቀን

ለምን የምክር ቀን ተባለ?

ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር ያጠናቀቁበት ቀን ነውና፡፡ በዚህ ምክራቸው ላይ በጣም ትልቅ ጭንቀት ነበር፡፡ ምክንያቱም ወቅቱ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት ቀን የተቃረበ በመሆኑ፣ ብዙው ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረኩ፣ ተአምራቱንም የሚያደንቁ ስለ ነበር ሁከት እንዳይፈጠር ነው፡፡ በዚህ ጭንቀት ሳሉ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ፣ በመካከላቸው በመገኘት የምክራቸው ተባባሪ ሆኖ ጭንቀታቸውን አስወግዶላቸዋል፡፡ [ማቴ. ፳፮፥፩፡፲፬ ፣ ማር. ፲፬፥፩፡፪ ቁ ፲.፲፩፣ ሉቃ. ፳፪፥ ፩፡፮]

የመልካም መዓዛ ቀንም ይባላል

ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ፣ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት፣ /ባለሽቱዋ ማርያም/፤ “ከእንግዲህ ወዲህ በኃጢአት ተበላሽቶ ይኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚህ መልካም ሽቱ የሚያጣፍጥ፣ ኃጢአትን ይቅር የሚል አምላክ መጣ” ስትል ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ፣ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ፣ በአልባስጥሮስ ብልቃጥ የተሞላ ሽቱ ይዛ በመሔድ በጠጉሩ /በራሱ/ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባችው ነው ረቡዕ የመዓዛ ቀን የተባለው፡፡

የእንባ ቀንም ይባላል

ይህም ይህቸው ሴት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ፣ መላ ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት በዕንባዋ እግሩን አጥባዋለችና፣ በጠጉሯም በእንባዋ ያጠበችውን እግሩን አብሳዋለችና፡፡ [ማቴ.፳፮፥፮፡፲፫ ፣ ማር.፲፬፥፫፡፱፣ ዮሐ.፲፪፥፩፡፰] ከዚህ ልንማር የሚገባው ነገር አለ፤ ይኸውም የራስን ኃጢአት በማሰብ ማልቀስና የተወደደ መሥዋዕት አድርጐ ለእግዚአብሔር ማቅረብን ነው፡፡ የማርያም እንተ ዕፍረትን ኃጢአት ይቅር ብሎ መብዓዋን የተቀበለ አምላክ ዛሬም በመካከላችን አለና፡፡

የአስቆሮቱ ይሁዳ ጌታችንን አሳልፎ ሰጠው። ምህሩንና ጌታውን ክዶ፣ ስሞ ለግርፋት እና ለመስቀል ሞት ተስማማ። ይህንን የጌታን ሕማማት፣ ስቅላት፣ ሞትና ትንሣኤ በምናስብበት በአሁኑ ወቅት የትግራይ ሕዝብ ለሕማም፣ ለስቅላት እና ለሞት አሳልፎ ተስጥቷል። ይሁዳ ለ፴/30 ዲናር ጌታችንን አሳልፎ ሰጠው፤ ከዚያም ዲናሩን መልሶ እራሱን አጠፋ። የዘመናችን ሰቃልያን የሆኑት ኦሮማራዎቹ የዋቄዮ-አላህ ጭፍሮች ደግሞ “አክሱም ጽዮን ለብዙ ሺህ ዓመታት ያፈራችውን እውቀት፣ ስልጣኔና ሀብት በሙሉ ለመዝረፍ፣ አሳልፎ ለመስጠትና ለማውደም ጊዜው አሁን ነው” ብለው የዓለማችን ፈላጭ ቆራጮች ከሆኑት አህዛብ፣ መናፍቃንና ግብረ-ሰዶማውያን ጋር ተባበሩ። በዚህም በዚያም ትልቅ ክህደት እና ስቅለት። በተለይ ተዋሕዶ ክርስትናን የተቀብሉትና ማሕተብ ያጠለቁት አማራ ወገኖች ክህደት ታሪክ የማይረሳው ነው፤ ብዙ ዋጋም የሚያስከፍላቸውና ከሌሎቹ ሁሉ የከፋው ክህደት ነው። ከይሁዳ ይልቅ የጴጥሮስ ዓይነት ክህደት ያድርግላቸው።

😈 የአስቆሮቱ ይሁዳ ክህደት + የቃኤል ቅናት = ሞት 💀

አወቁትም አላወቁትም፤ ዛሬ በአማራዎችና ኦሮሞዎች ህብረት በትግራይ ሕዝብ ላይ እየተካሄደ ያለው ጂሃዳዊ የጭፍጨፋ ዘመቻ የመጨረሻው ግብ፤ ተዋሕዶ ክርስቲያኖች ትግራዋያንን ከአኩም ጽዮን አጽድቶ የሕይወት ዛፍ እና ጽላተ ሙሴ የሚገኙበትን ቅድስት ምድር ለተለከፉት ባዕዳውያኑ ውሾች ማስረከብ ነው። አዎ! ኢትዮጵያን/አክሱም ጽዮንን ለባዕዳውያኑ ሉሲፈራውያን ለማስረከብ በትግራይ ሕዝብ ላይ ጦርነት ከፈቱ። እስኪ እናስበው! ዋው!

በሰባዎቹ ዓመታት ሉሲፈራውያኑ ድርቅና ረሃብ ፈጥረው በዚህ አካባቢ የምዕራባውያኑ ኔቶ ሃገራት፤ በተለይ ብሪታኒያ፣ ጀርመን እና ፈረንሳይ ሰራዊቶቻቸውን በእርዳታ ስም አስፍረው እንደነበር እናስታውስ። ከዚያ በሰማኒያዎቹ እና በባድሜው ጦርነት የተባበሩት መንግስታት “ሰላም አስከባሪዎች” እንዲገቡ ተደርጎ ነበር። ዛሬም ዓለም የተራቡ የትግራይን ሕፃናት ምስሎች በበቂ እንድታይ ከተደረገች በኋላና የተረፉትንም ትግራይ ወገኖቼንም በስደት የተቀደሰችውን ምድር እየለቀቁ እንዲወጡ (የአውሮፓን እና አሜሪካን ድንበሮች ይከፍቱላቸዋል፤ ከጥቂት ከፍተኛ ቦታ ላይ ከሚገኙት የዓለማችን ቦታዎች በቀር አውሮፓና አሜሪካ ሌሎችም አኅጉራት ይጠፋሉ የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል) ከተደረጉ በኋላ የምዕራባውያኑ ኔቶ ሠራዊቶች በትግራይ ይሰፍራሉ።

ገና ከአሥራ አምስት ዓመታት በፊት “ኔቶ በአፍጋኒስታን የሚገኘው ለኢትዮጵያ ለመለማመድ ነው፤ ተመሳሳይ የመልከዓ ምድር አቀማመጥ ስላላቸው…” በማለጥ ጽፌ ነበር። ምዕራባውያኑ እዚያ መስፈር ከጀመሩ በኋላ ቀስ በቀስ ዜጎቻቸውን ማስገባት ይጀምሩና በመጨረሻም “ኢትዮጵያውያኑም ተዋሕዶ ክርስቲያኖቹም እኛ ነን” በማለት እያታለሉና ደማቸውን እያፈሰሱ ለብዙ ሺህ ዓመታት ጠብቀውት የነበረውን ብኩርናቸውን በምስር ወጥ እንዲሸጡ ብሎም የመንፈስ ማንነታቸውንና ምንነታቸውን እየተነጠቁ “ኢትዮጵያዊነትንና ተዋሕዶ ክርስትናን” ቀስበቀስ እንዲከዱ ይደረጓቸውን “የቀድሞ ኢትዮጵያውያን” “አናስገባም!” ብለው ከኢትዮጵያ ድንብር ይመልሷቸዋል። ይህ ትንቢት ሳይሆን የሉሲፈራውያኑ ግልጽ የሆነ ተልዕኮ ነው። እግዚአብሔር ይህን ተልዕኳቸውን እንደሚያጨናግፈው አልጠራጠረም፤ ነገር ግን በኢትዮጵያውያኑ ደንቆሮነት፣ ስንፍና እና እንደ ግራኝ ያሉትን የውስጥ ጠላታቸውን በሰዓቱ ለማስወገድ ባለመድፈራቸው ብሎም አክሱም ጽዮንን ለመከላከል ባለመሻታቸው ብዙ መስዋዕት ይከፍሉ ዘንድ ግድ ይሆናል። በተለይ ከሃዲዎቹ ኦሮማራዎች!

የተከዱትንና የተገፉትን የአክሱም ጽዮን ልጆችን፤ በፈተና፣ በመከራ፣ በድካምና በስቃይ ላይ ያሉትን ወገኖቻችንን ሁሉ ያለ ደዌና ያለ ከፋ ሕማም ለክርስቶስ ትንሣኤ ያድርሰልን ፤ ቀናተኞችና አረመኔዎች የሆኑትን እርጉም ጠላቶቻቸውን/ጠላቶቻችንን ሁሉ በቶሎ ያንበርክክልን!!! አሜን።

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

Orthodox Christians in Ethiopia celebrate Palm Sunday

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 29, 2024

🌴 ሆሣዕና በአርያም፤ በርዕሰ አድባራት እንጦጦ መንበረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን 🌴

♱ Ethiopian Orthodox Christians celebrated Palm Sunday with prayers and a ceremony at the ornate Entoto Maryam Church outside Addis Ababa.

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

Russell Brand Announces Baptism: Many Returning To Christianity As World Crumbles

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 28, 2024

✞ ራስል ብራንድ ጥምቀትን አስታወቀ፡ ብዙዎች ወደ ክርስትና እንደ ዓለም ፍርፋሪ ይመለሳሉ

ታዋቂው የብሪታኒያ ተዋናይ እና ኮሜዲያን ራስል ብራንድ ለወራት ከዘለቀው መንፈሳዊ ጉዞ በኋላ በዛሬው የሆሣዕና እሑድ ዕለት እንደሚጠመቅ አስታወቀ

ዓለም እየፈራረስች ባለችበት በዚህ ወቅት ብዙዎች ወደ ክርስትና እየተመለሱ መሆናቸውን ራሰል የአርባ ስምንት/48 አመቱ ብራንድ በ X ላይ በለጠፈው ቪዲዮ ላይ ይናገራል።

ተዋናይ እና ኮሜዲያን ራስል ብራንድ በዚህ ቅዳሜና እሁድ እንደሚጠመቅ አሳውቋል ይህም ከክርስትና እምነት አስተምህሮ ጋር ለወራት በዘለቀ ተጋድሎ ካደረገ በኋላ ነው።

ብራንድ ጥምቀት ሲገለጽለት እንደሰማው እንዲህ ሲል ተናግሯል፤ “ለመሞት እና ለመወለድ እድል፤ ያለፈውን ትተን በገላትያ ውስጥ እንደተገለጸው በክርስቶስ ስም እንደገና ለመወለድ – እንደ ብሩህ እና የነቃ ሰው መኖር ትችላለህ፤ ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና”።

✞ Russell Brand announces baptism after months-long spiritual journey: ‘Taking the plunge’

Brand says many returning to Christianity as world crumbles

Actor and comedian Russell Brand announced Friday that he is going to be baptized this weekend, the culmination of his months-long public wrestling with the tenets of Christianity.

“This Sunday, I’m taking the plunge,” Brand, 48, said in a video he posted to X. “I’m getting baptized.”

Brand said he had heard baptism explained to him as “an opportunity to die and be reborn; an opportunity to leave the past behind and be reborn in Christ’s name like it says in Galatians — that you can live as an enlightened and awakened person.”

He also referenced what he suggested were non-Christian reflections on the same theme of embracing death for the sake of life, quoting Stoic philosopher and Roman emperor Marcus Aurelius and the Buddha.

“All of these things seem so inviting and beautiful,” he said.

Brand also suggested that increasing numbers are turning back to Christianity as the empty value system of modernity disintegrates and leaves them wanting more.

“I know a lot of people are sort of cynical about the increasing interest in Christianity and the return to God, but to me, it’s obvious,” he said. “As meaning deteriorates in the modern world, as our value systems and institutions crumble, all of us become increasingly aware that there is this eerily familiar awakening and beckoning figure that we’ve all known all of our lives, within us and around us. And for me, it’s very exciting.”

Brand added that he intends to get baptized in the heavily polluted River Thames, joking that he might be also getting baptized in toxoplasmosis and E. coli.

“I may be leaving behind the sins, but I might be picking up some pretty serious viruses,” he said.

Brand’s baptism comes after other videos he has been making in recent months about his spiritual journey to the Christian faith.

In December, he told followers he was reading the Bible and The Problem of Pain, a 1940 book by C.S. Lewis that explores the role of suffering in the Christian life.

In January, he noted that he was reading Rick Warren’s The Purpose-Driven Life, and that he desired a “personal relationship with God” as he found Jesus Christ increasingly important as he grows older, despite once seeing many churches as either too “old-fashioned” or too modernized.

“The reason I wear a cross is because Christianity and, in particular, the figure of Christ, are, it seems to me, inevitably becoming more important as I become more familiar with suffering, purpose, self, and not-self,” he said at the time.

In March, he posted a video explaining that he had been visiting churches of various denominations with the intention of possibly getting baptized, and asked his followers their opinions on the sacrament.

During an interview with Tucker Carlson last year, Brand said, “Like many desperate people, I need spirituality. I need God, or I cannot cope in this world. I need to believe in the best in people.”

Acknowledging he “didn’t have enough self-discipline to resist the allure of stardom,” he said he “fell face-first into the glitter, and I’m only just pulling myself out now.”

Brand faces multiple allegations of sexual misconduct going back years, including one report that claims he assaulted a 16-year-old girl after pulling her into an “emotionally and sexually abusive” relationship.

Brand has denied the “very serious criminal allegations” and maintained that while he was “very, very promiscuous” in the past, all of his sexual relationships were “always consensual.”

Source

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ሆሣዕና በአርያም፤ ኢትዮጵያ ዘ-ስጋ እና አህዛብ አጋሮቻቸው በሰቀሏት የኢትዮጵያ ዘ-ነፍስ እናት በአክሱም ጽዮን

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 28, 2024

🌴 ሰውን ከወደቀበት የበደል ጉድጓድ ያወጣው ዘንድ እግዚአብሔር ክንዱን ወደ ዓለም ላከ፡፡ ሰው ሆኖ የተገለጠው የእግዚአብሔር ክንድ በጉድጓድ ተጥሎ የነበረን በዚያም በሥጋ በነፍስ፤ በውስጥ በአፍአ ቆስሎ የነበረ አዳምን በትህትና ሁለተኛ አዳም ሆኖ በሥጋ የቆሰለውን በለበሰው ሥጋ ቆስሎ;በነፍስ የታመመውን በትምህርት አዳነ፡፡ ከእርሱ አስቀድሞ ሰውን ከሞት ወደ ሕይወት፤ ከባርነት ወደ ነፃነት የሚያመጣ ባለመኖሩ እርሱ ሁሉን የፈጠረ ሁሉን የሚያኖር እግዚአብሔር ሰው ሆኖ ለሰው መድኃኒት ሆነ፡፡ በሞቱም መድኃኒትነትን አሣየ፡፡ በነቢይ መድኃኒተ ፈነወ እግዚአብሔር ለሕዝቡ፤ እግዚአብሔር ለሕዝቡ መድኃኒትን ሰደደ፡፡ (መዝ.፻፲፥፱) ተብሎ የተነገረው ተፈጸመ፡፡

ክርስቶስ ባለ መድኃኒት ሆኖ በኃጢአት ለታመሙ ደቂቀ አዳም ሁሉ ሕይወትን ይሰጥ ዘንድ ወደዚህኛው ዓለም መጣ፡፡ በምድራዊ ሥርዓት እንደምናየው መድኃኒትና ባለ መድኃኒት እንደሚለያዩ አይደለም፡፡ ሁለቱንም እርሱ በመምጣቱ (ሰው በመሆኑ) ፈጸመ እንጂ፡፡ መድኃኒት አድርጎ ሥጋውን ደሙን የሰጠ እርሱ ነው፡፡ በካህናት አድሮ ሰው በንስሐ ሲመለስ መድኃኒት ወደሆነው ወደ ራሱ የሚመራ እርሱ ነው፡፡

ክርስቶስ መድኃኒት መሆኑ በሕማሙ እና በሞቱ ነው፡፡ በእመቤታችን ማኅፀን የተጀመረው የእርሱ መድኃኒትነት እና ፍቅሩ ፍፃሜውን ያገኘው በሕማሙ እና በሞቱ ነው፡፡ መሐሪ ንጉሥ እርሱ መሆኑን ይገልጥ ዘንድ በፈቃዱ ወደ ኢየሩሳሌም መጣ፡፡ ጌታ ወደ ኢየሩሳሌም ከመግባቱ አስቀድሞ ከኢየሩሳሌም ፲፮ ያህል ምዕራፍ በምትርቀው በቤተፋጌ ከደቀመዛሙርቱ ጋር ነበር፡፡

ከደቀ መዛሙርቱም ሁለቱን (ማለትም ጴጥሮስን እና ዮሐንስን) በፊታችሁ ወዳለችው መንደር ሂዱ ወዲያውም ወደ እርሷ ገብታችሁ ከሰው ማንም ገና ያልተቀመጠበትን ውርንጫ ታስሮ ታገኛላችሁ ፈትታችሁ አምጡልኝ፡፡ (ማር ፲፩፡፪) በማለት አዘዛቸው፡፡ ዳግመኛም ሰው ወዳልገባባት የተዘጋች የምሥራቅ ደጅ ወደ ምትባል ወደ ድንግል መጥቶ ዘጠኝ ወር ማኅፀኗን ከተማ አድርጎ እንደኖረ፤ ማኅየዊት ከምትሆን ሕማሙ በኋላም ሰው ባልተቀበረበት መቃብር እንደተቀበረ፤ አሁንም ጌታ ወደ ኢየሩሳሌም ለመግባት ማንም ሰው ያልተቀመጠባቸውን በሌላ መንደር የሚገኙ አህያንና ውርንጫን እንዲያመጡ ደቀመዛሙርቱን አዘዘ፡፡

የፍጥረት ሁሉ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በልደቱ እስትንፋሷን የገበረችለትን አህያ አሁን ደግሞ በፈቃዱ ስለ ሰው ሁሉ ሊሞት ሲል ንጉሥነቱን ሊያስመሰክርባት ወደደ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ካለው ፲፮ ምዕራፍ አሥራ አራቱን በአህያ ላይ ሳይቀመጥ በእግሩ ሄደ፡፡ ከዚያም ሁለቱን ምዕራፍ በአህያ ላይ በመቀመጥ ከተጓዘ በኋላ የኢየሩሳሌምን መቅደስ ሦስት ጊዜ በውርጫዋ ላይ በመሆን ዞረ፡፡ በዚህም ለሰው ሁሉ ያለው ቸርነቱ፣ ሕግ የተሰጣቸው አይሁድ እና ሕግ ያልተሰጣቸው አሕዛብ ላይ እኩል ቀንበርን መጫን እንዳይገባ አጠየቀ፡፡

ወደ ኢየሩሳሌምም ሲሄድ ብዙ ሰዎች ልብሳቸውን በመንገድ ላይ አነጠፉ፣ ሌሎችም ከዛፍ ቅጠሎችን እየቆረጡ ያነጥፉ ነበር፡፡ (ማር. ፲፩፡፰)፡፡ ከዚያም ሰዎች ሆሣዕና በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው (ማር. ፲፩፡፱) በማለት አመሰገኑ፡፡ ይህም ዛሬ ለቤተ ክርስቲያን እኛ ክርስቲያኖች ቡሩክ ስሙ ለእግዚብሔር ወቡሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር፤ የእግዚአብሔር ስሙ ምስጉን ነው፡፡ እግዚአብሔር ነኝ ብሎ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ እርሱ ክርስቶስም ምስጉን ነው በማለት የአብ እና የወልድን መስተካከልን ገልጸን ጌታን እናመሰግናለን፡፡ ጌታን የሚከተሉት ሰዎች ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር (ማር.11፲፩፡፲) ይኸውም በልዕልና፣ በሰማይ ያለ መድኃኒት፣ ከሰማይ የመጣ መድኃኒት ማለት ነው፡፡

የእግዚአብሔር ፍቅር እና መሓሪ መሆን በክርስቶስ ሕማም እና ሞት ከመቼውም ጊዜ በላይ ተገልጧል፡፡ ክርስቶስ የተቀበለው ሕማም እና ሞት የእርሱን አምላክነት እና ንጉሥነት አልሸሸገውም፡፡ እንደውም ዙፋኑን መስቀል በማድረግ ንጉሥነቱን በመድኃኒትነቱ ገልጿል እንጂ፡፡ በነቢይ እግዚአብሔርሰ ንጉሥ ውእቱ እምቅድመ ዓለም ወገብረ መድኃኒተ በማዕከለ ምድር፣ እግዚአብሔር ከዓለም አስቀድሞ ንጉሥ ነው፤ በምድር መካከልም መድኃኒትን አደረገ መዝ. ፸፫፤፲፪ ተብሎ የተነገረው እግዚአሔብር ድኅነትን በፈጸመበት ማዕከለ ምድር ሲሰቀል በመድኀኒትነቱ ንጉሥነቱን መግለጡን ያመለክታል፡፡ ዳግመኛም አንሰ ተሰየምኩ ንጉሠ በላዕሌሆሙ በጽዮን በደብረ መቅደሱ፤ እኔ ንጉሥ ሆኜ ተሸምኩ በተቀደሰው ተራራ ላይ(መዝ.፪፡፮) ተብሎ የተነገረው ኦርቶዶክሳውያን አበው እነርሱ (አይሁድ) ሰቅለነው ገድለነው ኋላ ፈርሶ በስብሶ ይቀራል ይሉኛል እንጂ እኔ ደብረ መቅደስ በምትባል በመስቀል ላይ ነግሻለሁ በማለት ይተረጉሙታል፡፡

ጌታ ንግሥናው ክብሩ የተገለጠበት ሆነ እንጂ መታመሙ እና መሞቱ ውርደት ክብሩንም የሚሸሽግ አይደለም፡፡ ሊቁ ዮሐንስ አፈወርቅ ይትባረክ እግዚአብሔር ዘሰመየ ሕማማት ወልዱ ክብረ ወስብሐት፣ የልጁን ሕማማት ክብርና ምስጋና አድርጎ የሰየመ እግዚአብሔር ይመስገን አለ፡፡ እኛን ያከበረበት በመሆኑ ሕማሙ ክብር እንደተባለ እናስተውል፡፡ በመስቀል ላይ ሆኖም በቀኝ የተሠቀለው ወንበዴ አቤቱ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ (ሉቃ ፳፬ )በማለት ንጉሥነቱ መስክሮለታል፡፡ ለዚህ ነው ጌታ ወደ ኢየሩሳሌም በምስጋና መግባቱ መድኃኒትነቱን እና ንጉሥነቱን ያሳያል ያልነው፡፡ ዳግመኛም ሁሉን የያዘ ጌታ በአህያ ላይ መቀመጡ ትህትናው ያስረዳል፡፡ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ዘይነብር ዲበ ኪሩቤል ዲባ ዕዋለ አድግ ነበረ፡፡ በማለት ሰማያዊ ልዑል አምላክ ትሑት ሆኖ እንደተገለጠ ተናገረ፡፡

ጌታ ከመድኃኒትነቱ የተነሣ ድንቅ የሆኑ እና ተአምራትን ለሰዎች አሳየ (ገለጠ)፡፡ እም ሆሳዕናሁ አርአያ ተአምረ ወመንክረ (ቅዳ. ጎርጎ.ዘኑሲስ) እንዲል፡፡ ይኸውም በአህያ ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ አእምሮ ጠባይዕ ያልቀናላቸው ሕፃናት ዕውቀት ተገልጾላቸው ሆሳዕና በአርያም እያሉ ጌታ በማመስገናቸው ነው፡፡ ዳግመኛም በከሃሊነቱ መናገር ለማይችሉ ዕውቀት ለሌላቸው ድንጋዮች ዕውቀት ተሰጥቷቸው መናገር ችለው ጌታን አመስግነዋል፡፡ እርሱ የባሕርይ አምላክ መሆኑ በሰውነቱም ቀድሞ በበደል ምክንያት ለሰው ከመገዛት ውጪ የሆኑ ፍጥረታት ዳግመኛ በሥጋዌ ለሰው እንደተገዙ ከዚህ ሁሉ ማስተዋል ይገባል፡፡

ጌታ ከመድኃኒትነቱ የተነሣ ልጅነት እና ተአምራት ማድረግን ገለጸ፡፡ እም ሆሳዕናሁ አርአያ ጸጋ ወኅይለ እንዲል (ቅዳሴ ጎርጎ. ዘኑሲስ)፡፡ የእርሱ ማዳን ከሰው ተወስዶበት የነበረ የጸጋ ልጅነት እንዲመለስለት አድርጋ በልጅነት ላይ ገቢረ ተአምራት (ተአምራትን ማድረግ) ገልጿል፡፡ ይኸውም እርሱ በረድኤት አድሮባቸው ድንቅ ተአምራትን ለሚያደርጉ ቅዱሳን መሠረት ነው፡፡ በተጨማሪም ልጅነትን ካገኙ በኋላ በበደል ሲገኙ ለንስሓ የሚሆን እንባን ሠጠ፡፡ እምሆሳዕናሁ ወሀበ ፈልፈለ አንብዕ ለኅጥአን እንዲል (ቅዳሴ ጎርጎ. ዘኑሲስ) ይኸውም የበደሉትን ያከብራቸው ዘንድ፣ ኀጥአንን ከኃጢአታቸው ያነጻቸው ዘንድ እንዲሁም የሳቱትን በንስሐ ይመልሳቸው ዘንድ ነው፡፡

ዳግመኛም ጌታ መድኀኒት ከመሆኑ የተነሣ ለዕውራን ዳግመኛ ብርሃንን ሰጠ፡፡ ይኸውም ለጊዜው በተፈጥሮ ዐይን ተሰጥቷቸው የታወሩትን ፈውሶ በሥጋ ብርሃን መስጠቱ ሲሆን፤ ፍጻሜው ግን በነፍስ ዕውቀትን ከማጣት የተነሣ ዕውራን የነበሩትን ትምህርትን; ዕውቀትን ገለጸላቸው፡፡ ይኸውም የእርሱ ገንዘቡ ስለሚሆን አንድነት ሦስትነት፣ አምላክነቱን መድኃኒት መሆኑን ገለጠላቸው ማለት ነው፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

Horses of The Apocalypse in London – The Scourge of Ishmael – Big Ben Clock Stops at 9am

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 25, 2024

🐎 በለንደን የአፖካሊፕስ ፈረሶች እና የእስማኤል መቅሰፍት – የለንደኑ ታሪካዊ የሰዓቶች ንጉሥቢግ ቤን ልክ በ9 ሰዓት ላይ ቆመ። ልብ እንበል፤ ሦስት ሰዓት ነው።

ባለፈው ረቡዕ ዕለት የለንደን ከተማ ጎዳናዎች ላይ ፈርጥጠው ሲሮጡ የነበሩት ሁለት ፈረሶች በከባድየተጎዱ ፈረሶች (ነጩ ደም በደም ሆኗል) ቀዶ ጥገና ክፍል ገብተው በቅርብ ክትትልእያገኙ መሆናቸው የብሪታኒያ ሰራዊት ገልጿል።

በከተማዋ ቤልግራቪያ አካባቢ በሚገኘው ዊልተን ክሪሰንት (ጨረቃ) መንገድ ከሚገነባው ህንጻ ላይ የሚንቀሳቀሰው ፍርስራሽን የያዙ ግንበኞች ተጓዥ የሚጠቀሙበት ፈረሶችን እንደነጠቁ ይታመናል።

🐎 በጎዳናዎች ላይ የሚሮጠው ነጭ ፈረስ ምስል በደም ተሸፍኖ ሲታይ ከአንዳንድ የምጽዓት ፊልም የተወሰደ ይመስላል

ኖሮ ቫይረስበጀርመን ተገኘ፤ ከሽቱትጋርት ከተማ የህዝብ ፌስቲቫል በኋላ ፬፻፴/430 ሰዎች በሆድ ሕመም ተጠቅተዋል። የፌስቲቫሉ ድንኳን ጣራ በዮሐንስ ራእይ ላይ ከተጠቆሙት አራት/ 4 ፈረሶች ቀለማት ጋር ተመሳሳይነ አለው።

ንጉስ ቻርለስ III. በባህላዊ የሳውዲ ሰይፍ ዳንስ (የክርስቶስ ተቃዋሚ)

ፕሬዝደንት ትራምፕ በባህላዊ የሳውዲ ሰይፍ ዳንስ (ፀረክርስቶስ)

እስማኤልም የበዳ አህያ እንደሚሆን አስቀድሞ ተነግሮ ነበር፡

[ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ ፲፮፥፲፪]❖

እርሱም የበዳ አህያን የሚመስል ሰው ይሆናል፤ እጁ በሁሉ ላይ ይሆናል፥ የሁሉም እጅ ደግሞ በእርሱ ላይ ይሆናል፤ እርሱም በወንድሞቹ ሁሉ ፊት ይኖራል።”

🐎 እና የፍልስጤም ባንዲራ….ነጭ፣ ቀይ፣ ጥቁር እና አረንጓዴ በራዕይ መጽሐፍ ውስጥ ካሉት 4 ፈረሶች ጋር ተመሳሳይ ቀለሞች።

ልክ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ዮሐንስ እንደገለጸለት፤

❖❖❖[የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ ፮፥፰]❖❖❖

“አየሁም፥ እነሆም፥ ሐመር ፈረስ ወጣ፥ በእርሱም ላይ የተቀመጠው ስሙ ሞት ነበረ። ሲኦልም ተከተለው፤ በሰይፍና በራብም በሞትም በምድርም አራዊት ይገድሉ ዘንድ ከምድር በአራተኛዋ እጅ ላይ ሥልጣን ተሰጣቸው።”

🛑 በሌላ በኩል፤ ፬/ 4 ቍጥር የሚቆመው በሰዎች እና ኃጢአቶቻቸው ላይ ለመፍረድ ነው፤

  • ☠ ነጭ ሽብር እና ጦርነት
  • 😡 ቀይ-ግርግር እና ግድያ
  • 🌚 ጥቁር – ረሃብ እና በሽታ
  • 🤢 የመጨረሻው የታመመ ፈዛዛ አረንጓዴ – ሞት እና ሲኦል ነው።

🐎 የአራቱ ምጽአት ፈረሰኞች

  • መሀመድ (ነጭ ፈረስ)
  • 😡 አቡባከር (ቀይ ፈረስ)
  • 🌚 ኦማር (ጥቁር ፈረስ)
  • 🤢 ኡትማን/ኡስማን(አረንጓዴ ፈረስ)

🐎 Two ‘SERIOUSLY’ Injured Runaway Household Cavalry Horses undergo operations and are being ‘closely observed’, Army reveals – as it emerges white runaway ‘Vida’ has history of being spooked and ‘kicked soldier in head during King’s coronation’

Rubble Being Moved From A Building On Wilton CRESCENT, a street in the Belgravia area, where builders using a travelator with concrete are believed to have spooked the horses.

The image of the white horse running through the streets covered in blood looks as though it was taken from some apocalypse movie.

The Big Ben Clock Stopped On Wednesday Morning, with the hands stuck at 9am and the wrong number of bongs sounded.

The Elizabeth Tower clock appeared to stop for about an hour, before showing the correct time again at 10:15am. Big Ben’s bongs also sounded 11am at 10:06am, despite the hands of at least two of the clock faces showing 9am.

Norovirus Detected In Germany: 430 people are now sick after the Stuttgart folk festival – The Festival Tent: Same Colors as The 4 Horses in The Book of Revelation

Numerous guests at the Stuttgart Spring Festival suffered from vomiting, diarrhea and nausea after visiting a festival tent. More than 400 visitors are said to be affected, and norovirus was detected in three cases. Now the operator speaks out.

Over the weekend, several hundred people were infected with a gastrointestinal virus in a festival tent on the Cannstatter Wasen. So far, 430 people have reported gastrointestinal complaints. A spokesman for the municipality announced this on Thursday. There were 400 cases last Saturday and 30 on Sunday.

All those affected visited the same festival tent at the weekend and then complained of vomiting, nausea and diarrhea. The spokesman said that there is a high number of unreported cases among those affected because the infection is certainly passed on within the family. So far, norovirus has been detected in three sick people.

King Charles III. in Traditional Saudi Sword Dance (Antichrist)

President Trump in Traditional Saudi Sword Dance (Antichrist)

It Was Foretold That Lshmael Would Be:

❖[Genesis 16:12]❖

“He shall be a wild donkey of a man, his hand against everyone and everyone’s hand against him, and he shall dwell over against all his kinsmen.”

🐎 And the Palestinian Flag….White, Red, Black and Green – Same Colors as The 4 Horses in The Book of Revelation

😈 THE FOUR HORSEMEN OF THE APOCALYPSE & Colored Flags of Islamic Countries & Oromos of Ethiopia

The Ishmaelites hate everyone and everything – specially 3/ Three, like in The HOLY TRINITY.

  • 🐎 THE FOUR HORSEMEN OF THE APOCALYPSE (Revelation Chapter 6)
  • ☠ White – Mohammed / Baphomet
  • 😡 Red – Abu Bakar
  • 🌚 Black – Umar
  • 🤢 Pale Green – Uthman

🔥 4 stands for judgment of men and their sins.

  • ☠ White – terror and war
  • 😡 Red – chaos and murder
  • 🌚 Black – famine and disease
  • 🤢 Pale sickly green is DEATH and HELL

This is exactly what’s taking place in Northern Ethiopia. The Islamic Oromos of Abiy Ahmed Ali starving ancient Christians of Tigray, Ethiopia to death.

❖❖❖ [Revelation Chapter 6:8] ❖❖❖

“And I looked, and behold a pale horse: and his name that sat on him was Death, and Hell followed with him. And power was given unto them over the fourth part of the earth, to kill with sword, and with hunger, and with death, and with the beasts of the earth.”

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »