ወደ ቤተክርስቲያን መሄድ የሚያዘወትሩ ሰዎች ደስተኞች፣ ጤናማዎች እና ታማኞች ናቸው | አዲስ የ’PEW’ ጥናት
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 6, 2019
አሜሪካዊው የ ‘PEW’ ሉላዊ ጥናት አዲስ ባወጣው መረጃ መሠረት፤ እምነት ያላቸው ሰዎች ወይም ክርስቲያኖች ኢ–አማናያን እና አህዛብ ከሆኑ ሕዝቦች ጋር ሲነፃጸሩ፤
-
+ በጣም ደስተኞች ናቸው፣
-
+ ረዘም ላለ ጊዜ ነው የሚኖሩት፣
-
+ ለመንፈሳዊ ጭንቀት እና ራስን ማጥፋትን አደጋ አይጋለጡም፣
-
+ በግኑኝነቶች ያላቸው ታማኝነት ከፍ ያለ ነው፣
-
+ በቤተሰባዊ ህይወታቸው የበለጠ እርካታ አላቸው፣
-
+ በይበልጥ ደስተኛ የሆኑ ልጆች አሏቸው።
ጥናቱን ያካሄዱት አለማውያኑ እራሳቸው ይህን ሲመሰክሩ ማየቱ ደስ ይላል!
ምንም የሚያጠራጥር ነገር አይደለም፤ በመካከላችን በየቀኑ የምናየው ነው። ኢትዮጵያ በጥናቱ ባትካተትም፤ በኢትዮጵያውያን መካከል እንኳ አማኝ የሆኑት ካልሆኑት በደንብ ይለያሉ። ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ!
አማኝ ያልሆኑት ወገኖች፣ መሀመዳውያኑንም ጨምሮ፤ ሙሉ ሕይወታቸውን ከመንፈሳዊው ሕይወት በመራቅ፡ እራሳቸውን እያታለሉ ሥጋዊ እና ዓለማዊ በሆኑ ነገሮች ላይ ብቻ ደስታቸውን ለመግዛት ሲታገሉ እናያለን። እነዚህ ወገኖቻችን ደስተኞች፣ ጤናማዎችና ታማኞች አይደሉም። ክርስቲያኑ ግን፡ ምንም እንኳን እነዚህ ደስተኛ ያልሆኑ ወገኖቹ ሊበክሉት፣ ሊያሥሩት፣ ሊጎትቱት እና እያታለሉ ደስታውን ሊነጥቁት ቢሞክሩም ክርስቲያኑ ግን በእግዚብሔር ኃይል፣ በቅዱሳን እርዳታና በ ቤተክርስቲያን ሞግዚትነት ከእነዚህ ነጣቂዎች ይድናል። ክርስቲያኑ ከቡና፣ ጥምባሆና ጫት ከመሳሰሉት አታላይ ጉርብትናዎች ከራቀ ሁሌ ደስተኛና ጤናማ የሆነ እንዲሁም ታማኝነት የተሞላበትን ስኬታማ ኑሮ መኖር ይችላል።
አንድ የሚገረም ገጠመኝ፤ በመስቀል ዕለት፤ ከአክስቴ ልጆች ጋር ሆነን ወደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ሄድን፤ በጣም ደስ ይል ከነበረው ዓመታዊ ክብረ በዓል በኋላ፡ አምቦ ውሃ ነገር እንጠጣ ብለን ከቤተክርስቲያኑ ፊት ለፊት በምትገኘው “ቡና” / ምግብ ቤት በረንዳ ላይ ወንበሮች ያዝን (ቢዲዮው ላይ በከፊል ይታያል)። ከጎናችን አንዲት የተሸፋፈንች ሙስሊም ወገናችን ብቻዋን ቁጭ ብላለች፤ ቁና ቋና እየተነፈሰች እግሮቿንና እጆቿን እያንቀሳቀሰች ትቁነጠነጣለች፤ ደስተኛ አትመስልም። ለማንም ሳልናነገር፡ ምን ይሆን ብዬ፡ በጥሞና እከታተላት ጀመር፤ በጣም ያዘኑ የሚመስሉት አይኖቿ ወደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ላይ ነው ያተኮሩት፦ ምን ታስብ እንደሆነ ለማወቅ ያዳግታል፤ ነገር ግን የተዋሕዶ ልጆች በደስታና በፍቅር የቤተክርስቲያኑን ደረጃ ሲወጡና ሲወርዱ ማየቷ አስከፍቷታል…አንዴ ወደ ቤተክርስቲያኑ ላለማየት ወደ ጎን ዘወር ትላለች…አላስችል ሲላት መሀል ግንባሮቿን ሰብሰብ ታደርጋለች… ሁኔታውን በቃላት ለመሳል አይቻልም፤ ግን እኔ እርግጠኛ ነበርኩ፤ ለዘመዶቼም ቀስ ብዬ ይህን እንዲያረጋግጡ ሹክ አልኳቸው…በአምስት ደቂቅ ውስጥ እነርሱም የተገነዘቡት ነገር ይህን ነበር።
— Pew: Actively Religious People More Likely to Be ‘Very Happy’
Leave a comment