Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • January 2013
    M T W T F S S
     123456
    78910111213
    14151617181920
    21222324252627
    28293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Archive for January 13th, 2013

አዲስ አበባ / Addis – ሳሪስ አቦ / Saris Abo

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 13, 2013

ሳሪስ አቦ – የምዕራፈ ቅዱሳን ፈለገ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ እና አቡነ አረጋዊ ቤ/ክርስቲያን

ቀኑ መጋቢት 5 ዕለቱ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ሰዓቱ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ሆኗል፤ አሁንም ህማሙን እየታገለ እያላበው በድካም ለፍጥረቱ ሁሉ ይለምናል፤ “አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህን ኢትዮጰያንም ባርክ” ይላል። ህመም የጀመረው መጋቢት 3 ዓርብ ቀን ነው፤መታመሙን የሰሙ እንደርሱ ቅዱሳን የሆኑት ዘርአ ቡሩክ፤ ፍሬ ቅዱስ፤ያዕቆብ፤ብንያምና ዮሴፍ እንዲሁም በወቅቱ የኢትዮጰያ ንጉስ የነበረው እንድርያስ ሊጠይቁት ተሰብስበዋል ወደ አጠገቡ መድረስ ግን አልተቻላቸውም አባታችን ገብረመንፈስ ቅዱስ የሚጋርደው እንጨት ዛፍ በሌለበት በርሃ እንደ አንበሳ ተኝቶ አዩት በላዩ ያረፈው የእግዚአብሔር ጸጋ ከፊቱ የሚወጣው ብርሃን ቀይ መልኩ ረዥም የራስ ጠጉሩ እንደ ነጭ ሐር የሚሆን ጽሕሙ አስደነቃቸው።

ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ሲሆን ከሰማይ ታላቅ ነጎድጓድ ድምጽ ተሰማ ጌታችን መላአክትን አስከትሎ ወደ አባታችን ወረደ፤ ከሰማይ ወደ ምድር ህብሩ አምሳያው ልዩ ልዩ የሆነ እንደ ጸሐይና እንደ ጨረቃ የሚያበራ እንደ ወንጪፍ ድንጋይ ይወረወር ነበር ከዚያ የነበሩ ሁሉ ፈሩ ወደ ኃላም ሸሹ ምድር ራደች ተራሮች ኮረብቶች ተናወጡ ብርቱ ጩኸት ንውጽውጽታ ሆነ።

ወዳጄ ገብረመንፈስ ቅዱስ ሰላም ላንተ ይሁን” እነሆ የማይታበል ቃል ኪዳን እገባልኃለው ስምህን የጠራ መታሰቢያህን ያደረገውን፤ እጣን ቋጥሮ ግብር ሰፍሮ መባ ይዞ ቤትህ የመጣውን እምርልኃለው አንተ ከገባህበት ገነት መንግስተ ሰማያት አገባዋለሁ አለው፤ አባታችንም “አቤቱ ጌታ ሆይ የኢትዮጰያን ህዝብ ማርልኝ” አለው፤ እነሆ ምሬልኃለው አስራት በኩራት አድርጌም ሰጥቼሃለው፤ ከመጋቢት አምስት ቀን ጀምሮ ዝክርህን ያድርጉ በአማላጅነትህም ይማጸኑ አለው።

ከዚህ በኃላ ሰባቱ ሊቃነ መላክት የአባታችንን ነፍስ ሊቀበሉ ወረዱ በታላቅ ምስጋናም ወደ ሰማይ አሳረጉት ስጋውንም ይዘውት ሄዱ የት እንደተቀበረ ግን እስካሁን አይታወቅም አንዳንዱ በእየሩሳሌም ነው ይላሉ፤ ሌላው በምድረ ከብድ ነው ይላል ግን እስካሁን ልክ እንደ ሊቀ ነብያት ሙሴ ስጋ የት እንደተቀበረ አይታወቅም።

ገድሉ ትሩፋቱ ከሰማይ ከዋክብት ከምድር አሸዋ ይበዛል ኢትዮጰያን አብዝቶ ይወዳታል፤ ምድራዊ ምግብ አልተመገበም የእናቱን ጡት እንኳን አልጠባም፤ ልብስ፤ መጠለያ አልፈለገም፤ የክረምት ቁር የበጋ ሐሩር እየተፈራረቀበት በተጋድሎ 562 ዓመት ኖረ፤ በዛሬዋ ቀን ሩጫውን ጨረሰ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ከአባታችን በረከት ያሳትፈን።

ቢዲዮው ላይ በሚታየው የአዲስ አበባ ሳሪስ አቦ ቤተክርስቲያን ከዕለታት በአንዱ ቀን ጻደቁ አባታችን አቡነ መንፈስ ቅዱስ ወደ ዝቋላ ሲጓዙ ለጥቂት ቀናት ቦታው ላይ አርፈውበት እንደነበር ይነገራል። ከቤተክርስቲያኗ ወረድ ብሎ ሸለቋማ ቦታ ላይ በጣም የምትማርክ አነስተኛ ቤተክርስቲያን በ አቡነ አረጋዊ ስም እየተጠራች መንፍሳዊ ግልጋሎትን ትሰጣለች።

_

Posted in Ethiopia, Ethnicity, Genetics & Anthropology | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

ቅኝ አገዛዝ 2.0

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 13, 2013

Gebezenetበአውሮፓው ህብረት የአፍሪቃ ሞግዚት የሆነችው ፈረንሳይ፡ በመጀመሪያ ወደ አይቮሪኮስት ሰርጋ በመግባት የክርስቲያኑ ፕሬዚደንት ባግቦ መንግሥት ተገልብጦ በእስላሙ የዋታራ መንግሥት እንዲተካ አደረገች፤ ከዚያ ወደ ሊቢያ ከፍ ብላ ኮሎኔል ቀጣፊን ደብድባ ከገደለች በኋላ የእስላሞች መንግስት በትሪፖሊና ቤንጋዚ በጥቂት ሣምንታት ልዩነት እንዲቋቋም አስተዋጽኦ አበረከተች። ከዚያም ከአልጀሪያ ጋር በመተባበር፡ የአልጀሪያ፣ ሊቢያና ማሊ ትዋሬጎችን አሰባስባ ለረጅም ጊዜ ያዘጋጃቸውን አክራሪ እስላሞች ወደ ማሊ እንዲገቡ በማድረግ መሣሪያ እስከ አፍንጫቸው እያስታጠቀች ላከቻቸው። አክራሪ እስላሞቹ ልክ እንደ ባርነቱ ዘመን ለአፍሪቃውያኑ የአረብን የበላይነት ለማሳየት የማሊን ቀበለኛ አፍሪቃዊ የእስላም ሥልጣኔ የሚያንጸባርቁትን የሥነ ሕንፃ መታሰቢያዎቻቸውን አንድ ባንድ አፈራረሱ፡ የነበሩትንም ጥቂት ክርስቲያኖች ጨረሷቸው።  ፈረንሳይና ተባባሪዎቿ አረቦች በመቶ ዓመት ሊደረግ የማይቻለውን ጥፋት በአንድ ዓመት ውስጥ ለማድረስ ከተቻላቸው በኋላ፤ አሁን ፈረንሳይ እሳት አጥፊና የማሊ አዳኝ መስላ ወደ በረሃው ሠራዊቷን ላከች። ፕሮግራም የተደረጉት አፍሪቃውያንም ፈረንሳይ ከአክራሪ እስላሞች እንዳዳነቻቸው አድርገው በመውሰድ ‘ሲሳም ተከፈት!’ እያሉ በጭብጨባ ወደቦቻቸውን ለአውሮፓውያን መንግሥታት ክፍት ማድረግ ይጀምራሉ። ሌሎች አውሮፓውያን እንዲሁም አሜሪካ የኮምፒውተር ጨዋታዎቻቸውን ለመቀጠል አብረው ወደ ማሊ ይገባሉ፡ የዜና ማሰራጫዎቻቸውም የማታላል ቅመማቸውን እንደ ተለመደው ይነሰንሳሉ።

ከሁሉ የሚገርመው ግን፡ ወደ ሶማሊያ ሠራዊቶቻቸውን እንዲልኩ የኢትዮጵያን ተደጋጋሚ ጥሪ ለመቀበል ለዓመታት አሻፈረኝ ሲሉ የነበሩት ከንቱ ምዕራብ አፍሪቃውያን የፈረንሳይንና የአውሮፓውን ሕብረት ጥሪ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በመቀበል ሠራዊቶቻቸውን ወደ ማሊ ለመላክ ዝግጁ ማድረጋቸው ነው።

ይህ የአውሮፓውያን ጣልቃ ገብነት የሚያሳየን “ቅኝ አገዛዝ 2.0” መጀመሩን ነው፡ በባህሉና ስነልቦናው መስክ አፍሪቃውያኑን ለዘመናት ካሹ በኋላ እንደገና አፍሪቃን ለመጫረት በመዘጋጀት ላይ መሆናቸውን ነው። ይህንም ተልዕኳቸውን ስኬታማ ለማድረግ እንደ ቀድሞው ብዙም መልፋት አይኖርባቸውም፡ በ እስልምና እና አክራሪ እስላሞች ዘንድ አንድ ጥሩ መሣሪያ አግኝተዋል፡ አሁን የፈልጉትን አፍሪቃዊት አገር ጽንፈኞቹን በመጠቀም ውስጣዊ ሁከት፣ የሕብረተሰብ መናጋት ወይም የእርስ በርስ መተላለቅን በቀላሉ መፍጠር ይችላሉ። ከዚያም የውጥንቅጥ ሊቆቹ ሰላማዊ አፍሪቃውያንን እናድናለን በማለት ሰተት ብለው በመግባት፤ የሚሰረቀውን እያታለሉ ይሰርቃሉ።

ይህን መሰሉን ስልት በአገራችን በኢትዮጵያም ሊጠቀሙ እንደሚችሉ ዒላማዋቸውም ወደዚያ እንደሆነ እየተመለከትን ነው። በአፍሪቃው ቀንድ ሁኔታዎችን በማመቻቸት ላይ ናቸው። ቀደም ሲል ከኤርትራ ጋር የድንበር ግጭት እንዲፈጠር ተደርጎ በተባበሩ መንግሥታት ሥም ቁልፍ የሆኑ ቦታዎችን በመውሰድ በኢትዮጵያና/ኢትዮጵያ (‘ኤርትራ‘ አልልም) ግዛቶች ውስጥ የሉሲፈር ኃይሎች ሠፈሩ። ምን ሠርተው እንደሆነ እግዚአብሔር ብቻ ነው የሚያውቀው። ምንም እንኳን ኢ-ዓማንያን ቢሆኑም፡ “ኢትዮጵያ የዳዊትና የሰለሞን ዝርያዎች የሚኖሩባት ምድር ነች፡ እርሷን እንዳትደፍሩ!” የሚለውን ታሪካዊ የማስጠንቀቂያ ትዕዛዝ በፍራቻ በመጠበቅ፣ የሰለሞን ዝርያ ሳይሆኑ አይቀሩም፣ ሕያው የሙሴን ጽላት በውስጣቸው ሳይሸከሙ አይቀሩም ብለው የሚገምቷቸውን ቤተ-እስራኤላውያን አንድ ባንድ ከኢትዮጵያ በማስወጣት ኢትዮጵያን ለመድፈር በመዘጋጀት ላይ ይገኛሉ፤ ለዚህም አሁንም፡ አውቀውም ሆነ ሳያውቁ ኢትዮጵያዊነታቸውን በመካድ የወደቁትን ወገኖች እንዲሁም ጭንፈኛ አክራሪ እስላሞቹን እየተጠቀሙ ነው። መጨረሻ ጦርነቱና መተላለቁ በሁለቱ ከዳተኞች ጸረ-ክርስቶስ ኃይሎች መካከል እንደሚሆን እናያለን።

ሁሉ ነገር አለን፣ ሁሉንም እናውቃለን፣ ከጥቁር ሕዝቦች እንሻላለን የበላዮች ነን በማለት ራሳቸውን እንደ አምላክ እየቆጠሩ ያለአግባብ የሚክቡት እነዚህ ኃይሎች ቤታቸው ሞልቶ፡ ሆዳቸው ጠግቦ የሌላውን ነጥቆ ለመውሰድ ወደ ሩቅ አገራት እየሄዱ የስርቆት ልምዳቸውን ቀጥለውበታል። እንደ ኢትዮጵያ ያሉት አገሮች ግን የራሳቸውን አፈር አልምተው እንዳይመገቡ፣ እግዚአብሔር ያፈለቀላቸውን ውሃ ጠጥተው እንዳይኖሩ ይከለክላሉ።

የሆነ ሆኖ፡ ባፈለጋቸው መንገድ መልካቸውን እንደ እስስት እየቀያየሩ ቢመጡም ኢትዮጵያን ለማንበርከክ አይቻላቸውም፡ ዕቅዳቸውም ግቡን አይመታም ፣ የኢትዮጵያ አምላክ ይህችን ምስኪን አገር፡ ይህን እንደ በግ ሞኝ የሆነ ሕዝብ ይጠብቃልና። አምላካችን ጽላቱን በተናቁት በብዙ ሚሊየን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ውስጥ ስለቀበረው፤ አውቀዋል፣ መጥቀዋል፣ ተራቀዋል የሚባሉት ግብዝ ሊቃውንቶቻቸው እንኳ ፈልፍለው ሊያገኙት አይቻላቸውም። እንዲያውም፣ በታሪክ፡ ከጥንት ጊዜ አንስቶ ከኢትዮጵያ (በአባይ በኩል?) እየተነሱ መላው አውሮፓን ሲያጥለቀልቁ የነበሩትን እንደ ወረርሽኝ የመሳሰሉትን የበሽታ መቅሰፍቶች እንደገና ይልክባቸዋል። አንማርም፣ ንስሐ አንገባም፡ አሻፈረን ከራስ በላይ ነፋስ በማለት ያለ ቅጥ የጠገቡትን የእግዚአብሔር ጠላቶች ሲቀጣ በኛ ትውልድ ለማየት እንደሚያበቃን አንጠራጠር፤ ጊዜው ሩቅ አይደለም።

በውኑ በኃጢአተኛ ቤት የኃጢአት መዝገብ፥ የተጸየፈም ውሽተኛ መስፈሪያ ገና አለ ይሆን? በአባይ ሚዛንና በከረጢት ባለ በተንኰል መመዘኛ ንጹሕ እሆናለሁን? ባለ ጠጎችዋን ግፍ ሞልቶባቸዋል፤ በእርስዋም የሚኖሩ በሐሰት ተናግረዋል፥ ምላሳቸውም በአፋቸው ውስጥ ተንኰለኛ ነው። ስለዚህ እኔ ደግሞ በክፉ ቍስል መታሁህ፤ ስለ ኃጢአትህም አፈርስሁህ። ትበላለህ፥ ነገር ግን አትጠግብም፥ ችጋርህም በመካከልህ ይሆናል፤ ትወስዳለህ፥ ነገር ግን አታድንም፤ የምታድነውንም ለሰይፍ እሰጣለሁ። [ሚካ ምዕራፍ 6፥11-14]

_

Posted in Curiosity, Ethiopia | Leave a Comment »

Stop, Look, Listen to Your Heart

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 13, 2013

One of my all-time favorite love ballads, originally by “The Stylistics”, covered by many artists, Johnny Mathis’ hypnotizing version and this wonderful performance by Toni & Mike must be the best.

You’re alone all time

Does it ever puzzle you, have you asked why

You seem to fall in love, out again

Do you ever really love or just pretend

 

Why fool yourself

Don’t be afraid to help yourself

It’s never too late, too late to

 

Stop, look

Listen to your heart, hear what it’s saying

Stop, look

Listen to your heart, hear what it’s saying

Love, love, love

 

Though you try, you can’t hide

All the things you really feel, this time decide

That you will open up, let it in

There’s no shame in sharing love you keep within

 

So jump on in

Head over heels, and fall right in

It’s never too late too late to

 

Stop, look

Listen to your heart, hear what it’s saying

Stop, look

Listen to your heart, hear what it’s saying

Love, love, love

 

Stop, look

Listen to your heart, hear what it’s saying (Listen to your heart, can’t

you see it’s not too late)

Stop, look

Listen to your heart, hear what it’s saying (La, la, la, la, la, la, la)

 

Stop, look

Listen to your heart, hear what it’s saying (Listen to your heart, can’t

you see it’s not too late)

Stop, look

Listen to your heart, hear what it’s saying

__

Posted in Infotainment, Love | Tagged: , , , , , | Leave a Comment »

27 Interesting Questions to Contemplate on…

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 13, 2013

QuestionOfBalance

  1. How old would you be if you didn’t know how old you are?

  2. Which is worse, failing or never trying?

  3. What is the one thing you’d most like to change about the world?

  4. If happiness was the national currency, what kind of work would make you rich?

  5. Are you doing what you believe in, or are you settling for what you are doing?

  6. Are you more worried about doing things right, or doing the right things?

  7. Would you break the law to save a loved one?

  8. What’s something you know you do differently than most people?

  9. How come the things that make you happy don’t make everyone happy?

  10. What one thing have you not done that you really want to do? What’s holding you back?

  11. If you had to move to a state or country besides the one you currently live in, where would you move and why?

  12. Do you push the elevator button more than once? Do you really believe it makes the elevator faster?

  13. Why are you, you?

  14. Would you rather be a worried genius or a joyful simpleton?

  15. Which is worse, when a good friend moves away, or losing touch with a good friend who lives right near you?

  16. What are you most grateful for?

  17. Is is possible to know the truth without challenging it first?

  18. What is your happiest childhood memory? What makes it so special?

  19. At what time in your recent past have you felt most passionate and alive?

  20. Have you ever been with someone, said nothing, and walked away feeling like you just had the best conversation ever?

  21. Is it possible to know, without a doubt, what is good and what is evil?

  22. If you just won a million dollars, would you quit your job?

  23. Would you rather have less work to do, or more work you actually enjoy doing?

  24. Do you feel like you’ve lived this day a hundred times before?

  25. If we learn from our mistakes, why are we always so afraid to make a mistake?

  26. Decisions are being made right now. The question is: Are you making them for yourself, or are you letting others make them for you?

  27. What do you love? Have any of your recent actions openly expressed this love?

Additional questions…

__

Posted in Curiosity, Life, Love | 1 Comment »