Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘Yohannes’

Emperor Yohannes IV | ዐፄ ዮሐንስ ፬ኛ ንጉሠ ነገሥት ዘ ኢትዮጵያ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 28, 2022

💭 “የኢትዮጵያ ልጅ ሆይ ልብ አድርገህ ተመልከት።ኢትዮጵያ የተባለችው አንደኛ እናትህ ናት፤ ሁለተኛ ክብርህ ናት፤ ሶስተኛም ሚስትህ ናት፤ አራተኛም ልጅህ ናት፤ አምስተኛም መቃብርህ ናት። እንግዲህ የእናት ፍቅር፤ የዘውድ ክብር፤ የሚስት ደግነት፤ የልጅ ደስታ፤ የመቃብር ከባቲነት እንደዚህ መሆኑን አውቀህ ተነሳ።” አፄ ዮሐንስ ፬ኛ

💭 የአፄ ዮሐንስ እና የንጉሥ ምኒልክ ዕርቅ

________________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ዘመነ ዮሐንስ | የሉሲፈር ዘመዶች በኢትዮጵያ ተገኙ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on August 28, 2019

የሉሲፈር ጉዳይ ነውና የአውሮፓውያኑን ቀን አቆጣጠር ልጠቀም። በ 2016 (...) በ ናይትድ ስቴትስ ውስጥ በሚገኘው ክሊቨላንድ የተፈጥሮ ሣይንስ ቤተመዘክር፥ በሰው ዘር አመጣጥ ጥናት ክፍል ኃላፊ የሆኑት /ር ዮሐንስ ኃይለ ሥላሴ “በሚያስደንቅ ሁኔታ የተሟላ” ቅሪተአካላት፡ ሉሲ/ ድንቅ ነሽ ተገችታበት በነበረበት የአፋር ቦታ አካባቢ አገኘን ይላሉ። እድሜውም ሶስት ሚሊየን ስምንት መቶ ሽህ ዓመት ነው ተብሏል። መጠሪያው ላኪ/ Lucky ሆኗል። Lucy – Lucky, „k“ ሲነሳ Lucy ይሆናል።

በቅድመታሪክ ጥናት የመስክና የቤተመኩራ መስክ ሰፊ ምርም ያደረጉት ዶ/ር ዮሐንስ ኃይለሥላሴ እስካሁን በተገኙ መረጃዎች እና ጥናቶች መሰረት ኢትዮጵያ የዘመናዊው ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ የሰው ዘር መገኛ መሆኗን ይገልጣሉ።

ኢትዮጵያዊው “ሉሲ” (እድሜዋ 3.2 ሚሊየን ዓመት) ..አ በኅዳር 24 / 1974 .ም ነበር የተገኘችው። እንግዲህ ሉሲ በተገኘችበት ዓመት ሦስት ወራት ቀደም ሲል እ..አ በመስከረም 12 / 1974 .ም፤ ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ ከኤርትራ በመጣው ጴንጤ ጄነራል አማን አንዶም ተተኩ። ያውም በዕለተ ቅዱስ ዮሐንስ። ዶ/ር ሀይሌ ላሬቦ በቀደም ዕለት ከአፄ ኃይለ ሥላሴ መስተዳደር በኋላ ኢትዮጵያ ጠንካራ አገር እንዳትሆን መንግስቷ ከጦርነት እንዳይላቀቅ ማድረግ አለብን” ማለታቸው ትክክል ነው። ነጠብጣቦቹን እናገናኝ፦ ቅዱስ ዮሐንስ + አፄ ኃይለ ሥላሴ + /ር ዮሐንስ ኃይለ ሥላሴ

በነገራችን ላይ፡ ሉሲየሚለው ስያሜ የተሰጠው፡ አግኝቷል የተባለው አሜሪካዊ ተመራማሪ፡ ዶናልድ ዮሃንሰን Donald Johanson (ስሙ የ ዮሐንስ ልጅ ማለት ነው) ቅሪተአካላቱን ባገኘበት ወቅት “ሉሲ ከአልማዝ ጋር በሰማይ” / “Lucy in the Sky with Diamondsበመባል የሚታወቀውን የእንግሊዝ የሙዚቃ ቡድን ቢትልስ/ Beatles ዘፈን እያዳመጥኩት ስለነበር ነው ብሏል። የሙዚቃ ቡድኑ ደግሞ ይህን ዘፈን ያወጣው ለሉሲፈር ነው። ሰይጣን አምላኪዎች ይህን የቢትልስ ዝማሬ በጣም ይወዱታል፤ በሰይጣናዊ ሥነ ሥርዓቶቻቸው ላይ ዛሬም ሲዘምሩት ይሰማሉ። በድብቅ ሉሲፈር ከአጋንንት ጋር በሰማይ / Lucifer In The Sky With Demons” መሆኑ ነው።

[ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ ፲፬፥ ፲፪፡፲፭]

አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ፥ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! አሕዛብንም ያዋረድህ አንተ ሆይ፥ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቈረጥህ! አንተን በልብህ። ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ፥ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፥ በሰሜንም ዳርቻ በመሰብሰቢያ ተራራ ላይ እቀመጣለሁ፤ ከዳመናዎች ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፥ በልዑልም እመሰላለሁ አልህ። ነገር ግን ወደ ሲኦል ወደ ጕድጓዱም ጥልቅ ትወርዳለህ።

[ንቢተ ሕዝቅኤል ምዕራፍ ፳፰፥፲፫ ]

በእግዚአብሔር ገነት በዔድን ነበርህ፤ የከበረ ዕንቍስ ሁሉ፥ ሰርድዮን፥ ቶጳዝዮን፥ አልማዝ፥ ቢረሌ፥ መረግድ፥ ኢያስጲድ፥ ሰንፔር፥ በሉር፥ የሚያብረቀርቅ ዕንቍ፥ ወርቅ፥ ልብስህ ነበረ፤ የከበሮህና የእንቢልታህ ሥራ በአንተ ዘንድ ነበረ፤ በተፈጠርህበት ቀን ተዘጋጅተው ነበር።

ከአምስት አመት በፊት ሉሲ / Lucy“ የተባለና ከኢትዮጵያዋ ሉሲ/ Lucy ጋር የተያያዘ ፊልም ተሠርቶ ነበር። የፊልሙ ዋና ተዋናይት ታዋቂዋ ስካርሌት ዮህናሰን / Scarlett Johansson ( ዮሐንስ ልጅ) ናት። ከዶናልድ ዮህንሰን ጋር ስጋዊ ዝምድና የላትም። ዮሐንስ + የዮሐንስ ልጅ + /ር ዮሐንስ ኃይለ ሥላሴ።

መጭው ዘመነ ዮሐንስ ነው፤ ብዙ ተዓምራትን የምናይበት ድንቅ ዘመን ነው የሚሆነው

_____________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Ethnicity, Genetics & Anthropology, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የአፄ ዮሐንስ እና የንጉሥ ምኒልክ ዕርቅ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on July 27, 2011


*ከማሞ ውድነህ*

የእስበሳችን ነገር ያለ ማክረሩ ነው የሚሻለው። ጠንካራ ክንድና ብርቱ ትኩረት የሚገባው ግን እንደ አዞ ከውሀ ውስጥ ብቅ የሚለው ነው (አሉላ አባነጋ)

አፄ ዮሐንስ ከጉራዕ ጦርነት በኋላ ሐማሴን ውስጥ ሰነባብተው ወደ ዐደዋ ከመመለሳቸው በፊት የሰሜን ኢትዮጵያ በር የተከበረና የታፈረም እንዲሆን ሲሉ ደጃዝማች ኃይሉ ተወልደ መድኅንና ራስ ባርያውን በገዥነት ሲሾሙ፡ ስመጥሩውን አዋጊያቸውን ሊጋባ አሉላን በራስነት ማዕረግ አስኮፍውሰና አስጊጠው ከመረብ ማዶ ያለውን አገር በጦር አበጋዝነት እንዲጠብቁ ሾሙዋቸው። ከዚያ በኋላም የአፄ ዮሐንስ ትልቁ የሥራ ምዕራፍ የኢትዮጵያን የውስጥ ጉዳይ ማደላደልና ማለሳለስ አንድነቷን ማጽናትና ሕዝቡ ፍትሕ አግኝቶ አርሶና ነግዶ እንዲተዳደር የማድረጉ ጉዳይ ነበር።

ይህን ዓላማቸውን ሊያደናቅፉባቸው እንደሚችሉ አሥግተዋቸው ከነበሩት ሁኔታዎችም ጋር መፋጠጡን ተያያዙት። በሰሜን ኢትዮጵያ በኩል የውስጡን ተቀናቃኝ ቀርቶ የውጭውንም ወራሪ ጠላት ከአንዴም ሁለቴ ኃያሉ ክንዳቸውን ስለአሳረፉበት ለጊዜው ረጭ ብሎላቸዋል። በምዕራብና በመካከል ኢትዮጵያም በኩል የቤገምድር የወሎና የጐጃም ሁኔታ ጋብ ብሎላቸዋል። የጥርጣሬና የሥጋት ትኩረታቸውን የሳበባቸው ግን ሸዋ ሆነ። የወጣትነት ጓደኛቸውና ምስጢረኛቸው ምኒልክ አፄተብለው ቁጥሩ እስከ ሰባ ሺህ በሚደርስ ሠራዊት ጐልብተው፡ ከሸዋም አልፈው ወሎንና ጐጃምን ለመደረብ ከሚያስፈራሩበት ደረጃ ላይ ወጥተዋል።

አፄ ዮሐንስ ግን፡ የምኒልክን ሁኔታ አንሥተው ከመኳንንቶቻቸውና ከጦር አበጋዞቻቸው ጋር በሚወያዩበት ሰዓት ሁሉ ደጋግመው የሚያነሡት ጉዳይ ነበራቸው።

ዋናው ሥጋቱና ችግሬ የሠራዊቱ ብዛት አይደለም። ለዚህ ለዚህስ እኔም ላቅ ያለ እንጅ ከእርሱ ዝቅ ያለ ሠራዊት የለኝም። ግን እንደዚያ ማሳያ እንደሚሉት የሰይጣን መልእክተኛ የመሰለ ፈረንጅ ከአጠገቡ አስቀምጦ፡ ከነሙንዚንገር ጋርም የሚያደርገው መላላክና መስማማት ነው።

ከዚያ ሌላ ደግሞ እነዚህ ሚሲዮኖችም በዚያ በኩል ገብተዋል፡. ዋናው ዓላማቸውም ምኒልክን አሳስተውና ጦር አስመዝዘው ከኔ ጋር ለማጋጨት መሆኑን አላጣሁትም። ግዴለም የማደርገውን ዐውቃለሁእያሉ ዛቻ አዘልና ትካዜለበስ አነጋገር ያሰሙ ነበር። እርግጥም ነው በዚያ ዘመን ፒዬር አርኖ የተባለ ፈረንሳዊ በዘይላ በኩል ወደ ሸዋ ገብቶ የምኒልክ ባለሟል ሆኖ የእርሳቸውንም መልእክት ይዞ ወደ ግብጽና ፈረንሣይ እየሔደ ዮሐንስን ለመጣል ትልቅ መሣሪያ ይሆናችኋልእያለ ያሽቃብጥ ነበር። ከእርሱም ሌላ ደግሞ በምሕጻረ ቃል አባ ማስያስእየተባለ የሚጠራው ሎሬንዞ ጉልየሞ ማሳያ የሚባለው የሮማ ካቶሊክ ሚሲዮን አባል በሸዋና በከፋ ውስጥ ድርጅቱን አቋቁሞ የምኒልክን ባለሟልነትም አትርፎ ከሚሲዮናዊነቱ ይልቅ በዲፕሎማቲክና በስለላው ሙያ ተሠማርቶ ዮሐንስንና ምኒልክን ለማራራቅና ለማጋጨት በመካከላቸው ገብቶ ነበር።

እነዚሁ ሁለቱ አውሮጳውያን የምኒልክን ጉልበት ከዮሐንስ ጉልበት የጠነከረ ለማድረግ ሲያደርጉት የነበረውን ጥረት ሲከታተሉት የነበሩት ዮሐንስም ክንዳቸውን በቀላሉ የማይታጠፍ ለማድረግና ምኒልክንም ለማስገበር ሲሉ የሠራዊታቸውን ቁጥር እስከ አንድ መቶ ሺህ ከአደረሱት በኋላ፥ ክዚሁ ውስጥ እስከ ዐርባ ሰባት ሺህ

የሚደርሰውን ልዩ ልዩ መሣሪያዎች አስታጠቁት። ከጉንደትና ጉራዕ ጦርነቶች የተገኘው ቀላል መካከለኛና ከባድ መሣሪያም የበላይነታቸውን ያረጋገጡበት ዋናው ትጥቃቸው ነበር።

ከመሣሪያው ጥራትና ብዛትም ሌላ በአጼ ተክለ ጊዮርጊስና በግብጾች ላይ ያገኙት ድል ዝናቸውንና ጥንካሬያቸውን አበሻ መሬት አውጥቶ በአፍሪቃ፡ በእስያና በአውሮጳ ውስጥ አስተጋብቶላቸው ነበር። በአሜሪካም ውስጥ ቢሆን፡ የኛ የጦር መኮንኖች ያዘመቱትን የግብጽን ጦር ድል ያደረገ ብርቱ ንጉሥየሚል ጸጸትለበስ ታዋቂነት አትሮላቸው ነበር።

ታዲያ እንደዚያ ሆኖ ስሙ የገነነ ሠራዊት ሸዋ የገባ እንደሆነ ሊያደርስ የሚችለውን ብርቱ ጉዳት አስቀድመው የተረዱትና የተጠነቀቁበት ከጐልማሳው ምኒልክ ይልቅ አዛውንቱ አጐታቸው ዳርጌ ንበሩ። ጉዳዩን በቀላሉ አትዩት፤ በየልቦናችሁ ምከሩበትና በእርቅ ይለቅሲሉ አዛውንቱ ጦር ጠማኝይሉ የንበሩት የምኒልክ የጦር አበጋዝ ግን፤

ወይ እሳቸው መጥተው፥ ያለዚያ እኛ ዘምተንባቸው ሳንሞካከር እንዴት አስቀድመን እንገብራለንእያሉ ምኒልክን ይወተዉቱ ነበር።

በዮሐንስ ቤተ መንግሥት እንደአባት ይታዩ የንበሩት ራስ አርአያም በበኩላቸው፤

የሁለት ወንድማማች ጠብ ማንን ጐድቶ ማንን ይጠቅም ይመስላችሁ? ኢትዮጵያን እኮ ነው የሚያዳክማት! ኢትዮጵያን እኮነው የሚያሳንሳት! ኢትዮጵያን እኮ ነው የጠላቶቿ መሳቂያ የሚያደርጋት! ታሪክ ይወቅሰናል፤ ትውልድ ያፍርብናል፤ ታቦትና መስቀል አስይዘን ካህናትን ወደ ምኒልክ እንስደድ እንጂ ጦር መምዘዙን አልስማማበትምእያሉ የእህታቸውን ልጅ ከነጦር አበጋዞቻቸው ይቆጡ ነበር።

 

 

Continue reading…AtseYohannesNegusMenilik

 

 

 

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: