ከትናንትና ወዲያ እሑድ ምዕራብ ቨርጅኒያ በሚገኘው አንድ የ ቤተ ክርስቲያን ሕንፃ ላይ መንስዔው ባልታወቀ ኃይለኛ እሳት ሁሉም ነገር አመድ ሆኖ ሲወድም በውስጡ የነበሩት መስቀሎች እና ብዙ መጽሐፍ ቅዱሶች ምንም ሳይሆኑ ተርፈዋል።
እኩለ ሌሊት ላይ የተቀሰቀሰው እሳት ቤተ ክርስቲያኑን ሙሉ በሙሉ ለማውደም ተቃርቦ ነበር። በቦታው ተገኘተው የነበሩት የእሳት አደጋ መከላከያ ሰራተኞች በማግሥቱ ጠዋት ላይ የፈራረሰው ሕንጻ ውስጥ ሲገቡ ተዓምር የሆነ ነገር ገጠማቸው፤ ከመስቀሎቹና መጽሐፍ ቅዱሶቹ መካከል አንዱም አልተቃጠለም፤ በዚህም ዓይናቸውን ማመን ነበር ያቃታቸው፤ ምክኒያቱም የእሳቱ ኃይለኛነት ምንም ነገር የማያተርፍ ነበርና፤ የእሳት ቃጠሎ በጣም ኃይለኛ ከመሆኑ የተነሳ ከቅርብ ሆነው ለመዋጋት እንዳልተቻላቸውና ባንድ ወቅት ከህንጻው ወደ ኋላ መመለስ እንደነበረባቸው ገልጸዋል።