Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘The Crucifixion’

10 scary Things Happening (or Possibly Happening) in SEPTEMBER 2015

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on August 31, 2015

CrucifixionBloodMoon

1- The Day of Atonement happens to be on the 23rd of September.


2- The Pope’s visit to the USA which happens on the 23rd.
(coincidence?)


3- Jade Helm’s conclusion which falls on the 15th.


4- Jewish Shmitah. (Claims that economic termoil always follows the Shmitah)


5- There’s a guy in Puerto Rico called Efrain Rodriguez who’s saying that a huge meteor will fall near Puerto Rico this September.


6- The date September 23rd appears in tons and I mean tons of movies and TV shows.


7- Some french politician or scientist said in 2013 that we have 500 days to avoid climate chaos. Coincidentally these 500 days end on September 24.


8- Rabbi Kanievsky, A very revered Jewish Rabbi has been recently announcing that the return of the Messiah (which we know as the Antichrist) is imminent, and he’s calling all the Jews to migrate to the land of Israel.


9- Obama the Mahdi??? Look into that, you’ll be surprised what you read.


10- The Blood Moon tetrad which started in 2014 will end with the final Blood Moon on September 28th 2015.


Continue reading…

 

Key events in September

— Ethiopian New Year’s Celebration: September 11/12

— Ethiopian Christian Feast of The Cross, “Meskel”: September 27

(H. H. Pope Tawadros ll, Head of the Coptic Orthodox Church of Egypt will be in Addis for the celebration – while the Roman Catholic Pope travels to Washington D.C)

__

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , | Leave a Comment »

የፍኖተ መስቀል ምዕራፍ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 10, 2015

004siklet3ጲላጦስ ዐደባባይ /ገበታ/

የመጀመሪያው ምዕራፍ፤ ጌታ ከጲላጦስ ፊት ለፍርድ የቆመበት ዐደባባይ ነው፡፡ ስሙም በዕብራይስጥ ገበታ፣ በግሪክ ሊቶስጥራ ይባላል፡፡

ጌታ የተገረፈበት

ሁለተኛው ምዕራፍ፤ ከሊቶስጥራ ወጥቶ ወደ ጌቴ ሴማኒ የሚወስደውን መንገድ ተሻግሮ ጲላጦስ ጌታን ገርፎ ያ ሰው ያውላችሁ ያለበት ነው፡፡ የቦታው ስም እስከ ዛሬ ጌታ የተገረፈበት ይባላል፡፡ በቦታው ላቲኖች ገዳም ሠርተውበታል፡፡

ጌታ በመጀመሪያ የወደቀበት ቦታ

ሦስተኛው ምዕራፍ፤ የቀደመውን ሥፍራ ወደኋላ ትቶ ወደ ምዕራብ የሚወስደውን መንገድ ይዞ በደማስቆ በር መግቢያ የአርመን ቤተ ክርስቲያን ያለበት በሩ በብረት የታጠረ ትንሽ ክፍል ነው፡፡ ጌታ ከዚህ ሲደርስ ከግርፋቱ ጽናት እና ከመስቀሉ ክብደት የተነሣ የወደቀበት ነው፡፡ ስለዚህ ቦታው ጌታ በመጀመሪያ የወደቀበት ይባላል፡፡

እመቤታችን እያለቀሰች ልጇን ያገኘችበት ቦታ

አራተኛው ምዕራፍ፤ ከሦስተኛ ምዕራፍ ትንሽ ዝቅ ብሎ ከአርመን ገዳም በስተግራ ካለው ማዕዘን ሲደርሱ እናቱ ድንግል ማርያም እያለቀሰች ከልጅዋ ጋር የተገናኘችበት ቦታ ነው፡፡009siklet6

ቀሬናዊ ስምዖን የጌታን መስቀል የተሸከመበት ቦታ

አምስተኛው ምዕራፍ፤ ከአራተኛው ሃያ ሜትር ያህል ወደ ደቡብ አቅጣጫ ከተጓዙ በኋላ ወደ ቀኝ የሚታጠፈው መንገድ ነው፡፡ በዚህ ቦታ ላይ ስምዖን ቀሬናዊ የሚባል ሰው ከእርሻ ውሎ ወደ ቤቱ ሲመለስ ወታደሮች አግኝተውት አስገድደው እየጎተቱ ወስደው የጌታን መስቀል ያሸከሙበት ቦታ ነው፡፡ እንዲህ ያለ ተግባር በወታደሮቹ ዘንድ የተለመደ ነበርና፤ በዚህ ቦታ ላቲኖች ትንሽ መቅደስ ሠርተውበታል፤ የስምዖን መቅደስ ይባላል፡፡

ይህ ስምዖን የተባለው ሰው የእስክንድሮስና የሩፎን አባት ነው፡፡ ማር. 1521፡፡ ጳውሎስም በሮሜ መልእክቱ 1613 በሰላምታው ውስጥ ሩፎን ያነሣዋል፡፡ እነዚህ ሁለቱ ልጆቹ ቁጥራቸው ከሰባ ሁለት አርድእት ነው፡፡ ይህ ሰው ምንም እንኳን ተገድዶ ቢሆንም የጌታን መስቀል በመሸከሙ የበረከተ መስቀሉ ተሳታፊ ሆኗል፡፡ ስለ ሆነም ዕድለኛ ሰው ነው፡፡

ቤሮና /ስራጵታ/ በመሐረብ የጌታን ፊት የጠረገችበት ቦታ

ስድስተኛው ምዕራፍ፤ ቤሮና /ስራጵታ/ የምትባል ሴት ከግርፋቱ ጽናት፣ ከመስቀሉ ክብደት የተነሣ ፊቱን የደም ወዝ አልብሶት ስታየው አዝና ፊቱን በነጭ መሐረብ ስትጠርግለት ወዲያውኑ አምላክነቱን የሚገልጥ፣ ለበጎ ሥራዋም ተስፋ የሚሰጥ፣ ሃይማኖቷን የሚያበረታታ የፊቱ መልክ 008siklet5በመሐረቡ ላይ ተገኘ፡፡ እሷም በዚህ ምክንያት እምነቷ እጅግ የጸና ሆነ፡፡

ታሪኳን ወይም በጎ ሥራዋን የሚናገር ወንጌላውያን በጻፉት ወንጌል አይገኝም፡፡ ነገር ግን ታሪኳን የተለያዩ የቤተ ክርስቲያናችን መጻሕፍት ይናገሩላታል፡፡ አንዳንድ አባቶችም ስለዚች ሴት ሲናገሩ ለዐሥራ ሁለት ዓመታት ያህል ደም ሲፈሳት ቆይታ የጌታን ልብስ ጫፍ በመዳሰሷ የዳነችው ሴት ናት ይላሉ፡፡ በዚህ በስድስተኛው ምዕራፍ ላይ ግሪኮች መቅደስ ሠርተውበታል፣ ዓርብ ዓርብ በየሳምንቱ ይከፈታል፡፡

የጎልጎታ መቃረቢያ

ሰባተኛው ምዕራፍ፣ ከስድስተኛው በግምት አንድ መቶ ሜትር ያህል ተጉዞ ወደ ምዕራብ አቅጣጫ በሚወስደው መንገድ ከሰሜን አቅጣጫ መጥቶ ወደ ጽርሐ ጽዮን በሚያሳልፈው መካከለኛ መንገድ ላይ ይገኛል፡፡ በጌታችን ዘመን የከተማው መጨረሻ የምዕራቡ በር ይህ ነበር ይባላል፡፡ በዚህም ቦታ ትንሽ መቅደስ አለበት፡፡ በውስጡ በቀድሞ ዘመን የነበሩ አዕማድ ናቸው እያሉ ያሳያሉ፡፡ መቅደሱ የላቲኖች ነው፡፡ እንደ ታሪኩ ቦታው ጥንት የከተማው በር ነበረ ይባላል፣ እንደዚህ ከሆነ ጎልጎታ ከከተማው በጣም ሩቅ አልነበረም፡፡

የጌታችንን ሥቃይ ሴቶች አይተው ያለቀሱበት ቦታ005siklet4

ስምንተኛው ምዕራፍ፣ ከሰባተኛው ምዕራፍ በዐሥራ አምስት ሜትር ያህል ወደ ላይ ወጣ ብሎ ይገኛል፡፡ ጌታ መስቀሉን ተሸክሞ መከራ መስቀልን እየተቀበለ ሲሔድ ሴቶች አይተው እያለቀሱ ይከተሉት ነበር፡፡ በዚያን ጊዜ ጌታችን ወደነሱ መለስ ብሎ፣ እናንተ የኢየሩሳሌም ልጆች ለኔ ማልቀሳችሁ ቀርቶ ለራሳችሁ አልቅሱ ያለበት ቦታ ነው፡፡ ሉቃ.ሉቃ.23;27:: ጌታ ይህን ማለቱ ከአርባ ዘመን በኋላ የሚመጣባቸውን መከራ በትንቢት ሲነግራቸው ነው፡፡ በዚህ ቦታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሆኑ የመነኮሳት መኖሪያ አራት ቤቶች አሉ፡፡

መስቀል ይዞ የወደቀበት

በዘጠነኛው ምዕራፍ አንድ የቆመ የድንጋይ ዓምድ አለበት፡፡ በዚህ ቦታ ጌታ መስቀል ይዞ ወድቆበታል፡፡ ይህ ቦታ ወደ ጎልጎታ መውጪያ በር ሲሆን፣ ቦታው የኢትዮጵያ ገዳማት መግቢያ በር ነው፡፡

ልብሱን የገፈፉበት

ዐሥረኛው ምዕራፍ፣ የጌታችን ልብስ የገፈፉበት ቦታ ነው፡፡

ጌታን የቸነከሩበት

ዐሥራ አንደኛው ምዕራፍ ጌታን ልብሱን ገፍፈው ዕርቃኑን ካስቀሩት በኋላ እጆቹንና እግሮቹን በምስማር የቸነከሩበት ቦታ ነው፡፡

ቅዱስ ሥጋውን ያወረዱበት ቦታ010siklet7

ዐሥራ ሦስተኛ ምዕራፍ እነ ኒቆዲሞስ ጌታን ከመስቀል ያወረዱበት እና ያሳረፉበት ቦታ ነው፡፡

ቅዱስ ሥጋውን የገነዙበት ቦታ

ዐሥራ አራተኛው ምዕራፍ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ የጌታን ቅዱስ ሥጋ የገነዙበት ቦታ ነው፡፡

ቅዱስ ሥጋው የተቀበረበት ቦታ

ዐሥራ አምስተኛው ምዕራፍ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ የጌታን ቅዱስ ሥጋውን በአዲስ መቃብር ያሳረፉበት ቦታ ነው፡፡ በአጠቃላይ የፍኖተ መስቀል ምዕራፎች እነዚህ ናቸው፡፡

ምንጭ

__

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , | 1 Comment »

“God Is With Us”: Oklahoma Teen Tweets Hanging Cross Amid Tornado Debris

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 29, 2015

Viral tornado photo a sign from God?

Cross-name-storm

A tornado ripped through parts of Oklahoma, destroying homes and leaving at least one person dead. But amid the destruction, one image is being shared across social media that is bringing hope in the affected community.

A high schooler, named Chase Rhodes, in Moore, Oklahoma took a picture of power pole Wednesday that was left hanging in the form of a cross surrounded by destruction. He captioned the tweet “God is with us,” and it has been retweeted and shared thousands of times.

Source

የልጃምበራ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ተቃጠለ

በምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት በሰከላ ወረዳ ከግሽ አባይ ከተማ 21 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው የልጃምበረ ደብረ መድኀኒት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን መንስኤው ባልታወቀ ምክንያት ጥር 16 ቀን 2007 .. ከቅዳሴ በኋላ በእሳት መቃጠሉ ተገለጠ፡፡

በቃጠሎው ቤተ ክርስቲያኑ ሙሉ ለሙሉ የወደመ ሲሆን፤ ጽላቱን ግን በምእመናን እርዳታና ርብርብ ከቃጠሎው ለማዳን ተችሏል፡፡ ነገር ግን ከ15 እስከ 20 ሰዎች የሚሸከሙት በቀደምት አባቶቻችን የተሠራው የሥነ ስቅለቱ ሥዕል የተሳለበት የእንጨት መስቀል ከቃጠሎው ለማትረፍ ሳይቻል ቀርቷል፡፡ በዚህም አገልጋይ ካህናቱና ምእመናን በቅርሱ መቃጠል በእጅጉ አዝነዋል ሲሉ የቤተ ክርስቲያኑ አገልገይ የሆኑት ቄስ አዳሙ አግማሴ ገልጸዋል፡፡

ምንጭ

— ባሕር ዛፍ ፍሬ ላይ መስቀል

— Stealing The Rainbow

__

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

ሞተ ወልደ እግዚአብሔር

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 3, 2013

ፈጣሪዋ በዕንጨት መስቀል ላይ ተዘርግቶ ተሰቅሎ በአየችው ጊዜ ፀሐይ ጨለመች እርሱም ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የነሣትን ለባዊት ነባቢት የሆነች ነፍሱን ከሥጋው ለያት ሐዋርያ ጴጥሮስ በሥጋ ምውት ሲሆን በመለኮት ሕያው ነው እንዳለ ነፍሱ ከመለኮት ሳትለይ ከሥጋ ተለየች በዚያ ጊዜ ሥጋ ከመለኮት ሳይለይ በዕንጨት መስቀል ላይ ተሰቅሎ ነበር፡፡

እንዲሁም ነፍስ ከመለኮት ጋራ አንድ ሁና እሥረኞች ነፍሳትን ትፈታቸው ዘንድ ወደ ሲኦል ወረደች፡፡

እርሱ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ ያለ ልዑለ ባሕርይ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ በጌትነቱ ዙፋን ተቀምጦ ያለ ለእርሱም ምስጋና የክብር ክብር ገንዘቡ የሆነ ራሱን ሠውቶ አዳነን፣ የመንግስቱን ደጆች በፈሳሽ ደሙ ከፈተልን፡፡

ሐዋርያዊ ቅዱስ አትናቴዎስ እንዳለ የእግዚአብሔር ታላቅ የማዳን ሥራ ለባሕርያዊ ደግነቱ የተገባ ነው፡፡ አንድ ንጉሥ የመሠረተው ከተማ ወይም የሠራው ቤት ከጠባቂዎቹ ስንፍና የተነሣ በሽፍታ ቢጠቃና ቢወረር ሽፍታውን ተበቅሎ ይዞታነቱን ያጸናል እንጂ በጠላት በመወረሩ ምክንያት አይተወውም፡፡ የአብ አካላዊ ቃልም የእጁ ሥራ የሆነውን የሰው ዘር ጠፍቶ እንዲቀር አልተወውም፤ ሞትን የራሱን ሰውነት ለሞት አሳልፎ በመስጠት ሲያስወግድ፣ ለሰው ተሰጥቶት፣ ነገር ግን ሕጉን በመተላለፉ ምክንያት አጥቶት የነበረውን ሁሉ በኃይሉና በሥልጣኑ መለሰ፡፡

ይህንንም በመንፈሰ እግዚአብሔር የተቃኙት የመድኀኒታችን አገልጋዮች የጻፏቸው ቅዱሳን መጻሕፍት እንዲህ በማለት ያረጋግጡልናል፡፡ ‹‹ይህን ስለ ቆረጥን የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናል፤ አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ፣ እንግዲያስ ሁሉ ሞቱ፣ በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ፡፡›› 2 ቆሮ 5÷14-15

EthioIconCrucifixionበመቀጠልም ሌላ ማንም ሳይሆን ራሱ የእግዚአብሔር ቃል ለምን ሰው መሆን እንዳስፈለገው ምክንያቱን ይነግረናል፡– ‹‹ሁሉ ለእርሱ የሆነና ሁሉም በእርሱ ለሆነ ለርእሱ ብዙ ልጆችን ወደ ክብር ሲያመጣ የመዳናቸውን ራስ በመከራ ይፈጽም ዘንድ ተገብቶታልና፡፡›› ዕብ. 2÷9 ይህም ማለት ሰውን ከጀመረው ጥፋት መልሶ ሕይወትን መስጠት ጥንቱን ከፈጠረው ከእግዚአብሔር ቃል በስተቀር ለሌላ ለማንም ተገቢ አይደለምና፡፡

አካላዊ ቃል ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋን የተዋሐደው እንደ እርሱ ሰዎች ለሆኑ ሥጋውያን ሁሉ ቤዛ ይሆን ዘንድ ነበር፡፡ ሐዋርያው ‹‹ልጆቹ በሥጋና በደም እንደሚካፈሉ እርሱም እንዲሁ በሥጋና በደም ተካፈለ፤ በሞቱ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን ይሽረው ዘንድ፣ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፤ በሕይወታቸው ዘመን ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ ያወጣ ዘንድ›› ዕብ. 2÷14-15 በማለት እንደገለጸው፡፡ የራሱን ሰውነት በመሰዋት በእኛ ላይ የነበረውን ሕግ (ትሞታለህ የሚለውን) በመፈጸም አስወገደልን፡፡

እርሱ ራሱ በእኛ ላይ የነበረውን እርግማን ሊያስወግድ ከመጣ ለእርግማን የተቀመጠውን ሞት ካልተቀበለ በስተቀር እርግማናችንን እንዴት አድርጎ ይሸምልን ነበር? ይኸውም መስቀል ነው፡፡ ሰውም ሕጉን በተላለፈ ጊዜ ስለ ተረገመ የዚህ ርግመት ካሣ ሊከፈል የሚችለው የርግመት መገለጫ የሆነውን የመስቀል ሞት በመቀበል በመሆኑ ጌታችን የመስቀል ሞተ ተቀበለልን፡፡ ‹‹በእንጨት ላይ የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፏልና ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማን ሆኖ ከሕግ እርግማን ዋጀን፡፡›› ገላ. 3÷13 ተብሎ እንደተጻፈ፡፡

የሁላችን መድኀኒት ስለ እኛ ሞቶልናልና በእርሱ የምናምን እኛ በሕግ መልክ በማስጠንቀቂያ በተነገረውና ባጠፋን ጊዜም በተግባር በደረሰብን (በተፈጸመብን) የሞት ፍርድ እንደ ቀድሞው በኩነኔ ሞት አንሞትም፡፡ ክርስቶስ ስለ እኛ ሞትን ተቀብሎ የሕግ አፍራሽነት ዕዳችንን ከከፈለልን በኋላ ይህ ፍርድ ተፈጽሞ አልቋልና፡፡ እንዲሁም ሙስናና ጥፋት በጌታችን የትንሣኤ ኃይል ስለ ተወገደ ዛሬ እኛ እግዚአብሔር በወሰነው ጊዜ የምንሞተው ለሰውነታችን ተፈጥሮ እንደሞስማማ ሞተን የበለጠውን ትንሣኤ እናገኝ ዘንድ ነው፡፡

ደግሞም የጌታችን ሞት ለሁሉም ቤዛ ለመሆንና ሁሉንም ለመቤዠት እስከሆነ ድረስና በሞቱም የጥል ግድግዳን ያፈርስ ዘንድ፣ አሕዛብን ይጠራ ዘንድ እንደመሆኑ መጠን በመስቀል ላይ ባይሰቀል ኖሮ እንዴት ወደ እርሱ ይጠራን ነበር? ሰው እጆቹ ተዘርግተው ሊሞት የሚችለው በመስቀል ላይ ብቻ ነውና፡፡ በአንድ እጁ ቀደምት ሕዝቡን (አይሁድን)፣ በሌላው እጁ ደግሞ አሕዛብን ይጠራ ዘንድ ሁለቱንም በእርሱ አንድ አድረጎ ያዋሕዳቸው ዘንድ ጌታችን እጆቹን ዘርግቶ በመስቀል ላይ ሊሞት ተገባው፡፡ በምን ዓይነት ሞት ዓለሙን እንደሚቤዥ ሲያመለክት እርሱ ራሱ ያለው እንዲህ ነውና፡-‹‹እኔ ከምድር ከፍ ባልሁ ጊዜ ሁሉንም ወደ እኔ እስባለሁ››፡፡ እንዲሁም ጌታችን የመጣው ሰይጣንን ድል ለማድረግና ዕንቅፋትነቱን ከመንገዳችን ለማስወገድ፣ አየራትን ለማዘጋጀት ነውና፡፡ ይህስ ከምድር ከፍ ብሎ በአየር ላይ ከሚፈጸም ሞት ማለትም ከመስቀል ሞት በስተቀር በምን ዓይነት ሞት ሊፈጸም ይችል ነበር? በአየር ላይ ሊሞት የሚችለው በመስቀል ላይ የተሰቀለ ብቻ ነውና፡፡


ሰላም ለሕማማቲከ በተጸፍዖ መልታሕት ከመ እቡስ፡፡ በተቀሥፎ ዘባን ዓዲ ወተኰርዖ ርእስ፡፡ እንዘ መላኪሆሙ አንተ እግዚአብሔር ንጉሥ፡፡ ኢያፍርሁኒ ቀታልያኒሃ ለነፍስ፡፡ እስመ ማኅተምየ ደምከ ቅዱስ፡፡

Source

__

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , | Leave a Comment »

Fasika (Easter) In Ethiopia

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 12, 2012

GOOD FRIDAY

Church of St Mary of Zion , Axum – photo by M.Torres, via Travel-Images.com

The solemn liturgical service of Good Friday is attended by thousands of believers. There is a sense of sorrow and desolation. All the symbols, images and instruments used in the passion of the Saviour are publicly exhibited in the church.

Men and women go to church to prostrate themselves, remaining there from early morning till 3 p.m. the hour of the death of Jesus Christ. Believers confess their greater and lesser offenses to the confessor or sit reading their Psalter. It is believed that on

Good Friday blood fell from Christ on the cross and dripped into the grave of Adam beneath and there rose up from the dead about 500 people; the thief on the left was sent into darkness but the one on the right went before Adam into Paradise.

On this Friday the Devil was bound with cords and Christ descending to purgatory (seol) sent forth to paradise all the souls that were in darkness (Seol). Good Friday is a special day for confession.

Why The Good Thief Was Pardoned

__

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | 1 Comment »

 
%d bloggers like this: