Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • March 2023
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    2728293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘St. Michael’

የተአምራትና የይቅርታ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል | አንቀጸ ምሕረት ቅ/ሚካኤል ደብረ ታቦር

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on August 18, 2022

✞ በአክሱም ጽዮን ሳይቀቡ እራሳቸውን አላግባብ “አፄ ምንሊክ ፪ኛ”ብለው የሰየሙት ጋላማራ/ ኦሮማራ ዲቃላ ንጉስ፤ እግዚአብሔር አምላክ ያደረገላቸውን ውለታ ሁሉ በመርሳትና እግዚአብሔር የሚጠላቸውን ተግባራት ሁሉ በመፈጸማቸው ዛሬ የምናየውን እርጉም ትውልድ ለማፍራት በቅተዋል።

  • ☆ አፄ ምኒልክ መጀመሪያ ታላቁን ንጉሠ ነገሥት አፄ ዮሐንስን በተንኮል አስገደሏቸው
  • ☆ አፄ ምኒልክ ጽዮናዊውን ወንድማማች ሕዝብን በመከፋፈልና ለባዕድ አሳልፈው በመስጠት “ትግራይ” እና “ኤርትራ የተሰኙትን ግዛቶች እንዲመሠረቱ አደረጉ።
  • ☆ ከዚህም እኵይ ተግባራቸው የተነሳ የትግራይና ኤርትራ ጽዮናውያን ካለፉት መቶ ሰላሳ ዓመታት እስከ ዛሬ ድረስ እየተጨፈጨፉ፣ በረሃብ እየተቆሉና ለጠላት ተላልፈው በመሸጥ ላይ ናቸው።
  • ☆ ዛሬ የምናያትንና ስጋ-አልባ የዶሮ ቅልጥም የምትመስለዋን “ትግራይ” የተባለችውን ግዛት ካርታ የፈጠሯት ጋላማራው ዲቃላ አፄ ምንሊክ መሆናቸውን ጽዮናውያን መገንዘብ ይኖርብናል።
  • ☆ ሻዕቢያና ሕወሓት የሚያውለበልቧቸው የኤርትራና ትግራይ ካርታዎች ጋላማራው አፄ ምንሊክ የሰጧቸውን ካርታዎች ነው።
  • ☆ ጋላ-ኦሮሞዎች፤ “ኢትዮጵያ የመቶ ሃምሳ/ሰላሳ ዓመት ታሪክ ነው ያላት” ሲሉን፤ “እኛ ጋላዎች ኢትዮጵያን ካፈረስናትና ጽዮናውያንን መጨፍጨፍና ማዋረድ ከጀመርን መቶ ሃምሳ/ሰላሳ ዓመታት ሆነውናል” ማለታቸው ነው። የአህዛብን ነገር ገልብጦ በተቃራኒው ማየት ተገቢ ነው። ሕወሓቶችም ይህን ማስተጋባታቸው የምንሊክ “ብሔር-ብሔረሰብ ተረት ተረት” ትውልድ አካላት መሆናቸውንም ያረጋግጥልናል።
  • ☆ እባቡ ግራኝ አብዮት አህመድ፤ “የምንሊክ ልጆች” ሲል “አማራን” ማለቱ ሳይሆን “ዲቃላ ኦሮማራዎችን” ማለቱ ነው። አማራው በእልህ ከምንሊክ ጋር ሙጭጭ እንዲል። በምንሊክ ቦታ የራሱን ፎቶ የሰቀለውም ለዚህ ነው።

😈 እንግዲህ የጥፋትና የሞት ሥርዓተ አምልኮ ወደ ኢትዮጵያ የገባውና የዲያብሎስ ዙፋን በምድሪቱ ላይ የተተከለው ንጉሥ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዮሐንስን ገድለው ቤተ ክርስቲያንን እና ኢትዮጵያን ለመቆጣጠር ከበቁ በኋላ ነው ማለት ነው። አፄ ምኒልክ በአክሱም ጽዮን ያልተቀቡ ንጉሥ መሆናቸውን በድጋሚ ልብ እንበል።

👉 ከዚህም በመነሳት ከዋቄዮ-አላህ-አቴቴ የአህዛብ ባዕድ አምልኮ ጋር በቀጥታ የተያያዙትና ለዚህም ተጠያቂ የሆኑት አራቱ ትውልዶች እነዚህ ናቸው፦

  • ☆፩ኛ. የሻዕቢያ/ህወሓት/የኢሕአዴግ/ኦነግ/ቄሮ/ብልጽግና/ኢዜማ/አብን/ፋኖ ትውልድ
  • ☆፪ኛ. የደርግ መንግስቱ ኃይለ ማርያም ትውልድ
  • ☆፫ኛ. የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ትውልድ
  • ☆፬ኛ. የአፄ ምኒልክ/አቴቴ ጣይቱ ትውልድ

✞ ፪ኛይቱ የሙሴ ጸሎት [ዘዳግም ፴፪]

“እነርሱ ረከሱ፤ ልጆቹም አይደሉም፤ ነውርም አለባቸው፤ ጠማማና ገልበጥባጣ ትውልድ ናቸው። ደንቆሮ ብልሃተኛም ያልሆንህ ሕዝብ ሆይ፥ ለእግዚአብሔር ይህንን ትመልሳለህ? የገዛህ አባትህ አይደለምን? የፈጠረህና ያጸናህ እርሱ ነው። የዱሮውን ዘመን አስብ፥ የብዙ ትውልድንም ዓመታት አስተውል፤ አባትህን ጠይቅ፥ ያስታውቅህማል፤ ሽማግሌዎችህን ጠይቅ፥ ይነግሩህማል። ልዑል ለአሕዛብ ርስታቸውን ባወረሰ ጊዜ፥ የአዳምን ልጆች በለየ ጊዜ፥ እንደ እስራኤል ልጆች ቍጥር የአሕዛብን ድንበር አቆመ። የእግዚአብሔር እድል ፈንታ ሕዝቡ ነው፤ ያዕቆብም የርስቱ ገምድ ነው። በምድረ በዳ በጥማት፥ የነፋስ ጩኸትም በሞላበት ውድማ አገኘው፤ ከበበው ተጠነቀቀለትም፤ እንደ ዓይን ብሌን ጠበቀው።

ንስር ጫጩቶቹን እንደሚያወጣ፥ በእነርሱም ላይ እንደሚሰፍፍ፥ ክንፎቹን ዘርግቶ ወሰዳቸው፥ በክንፎቹም አዘላቸው። እግዚአብሔር ብቻውን መራው፤ ከእርሱም ጋር ሌላ አምላክ አልነበረም። በምድር ከፍታ ላይ አወጣው፤ የእርሻውን ፍሬ በላ፤ ከዓለትም ድንጋይ በሚገኝ ማር፥ ከጭንጫውም ድንጋይ በሚገኝ ዘይት አጠባው፤ የላሙንም ቅቤ፥ የመንጋውም ወተት፥ ከጠቦት ስብ ጋር፥ የባሳንንም አውራ በግ፥ ፍየሉንም፥ ከስንዴ እሸት ጋር በላህ፤ ከወይኑም ደም ያለውን ጠጅ ጠጣህ። ይሹሩን ወፈረ፥ ረገጠ፤ ወፈረ፥ ደነደነ፥ ሰባ፤ የፈጠረውንም እግዚአብሔርን ተወ፤ የመድኃኒቱንም አምላክ ናቀ። በሌሎች አማልክት አስቀኑት፥ በርኵሰታቸውም አስቈጡት። እግዚአብሔር ላልሆኑ አጋንንት፥ ለማያውቋቸውም አማልክት፥ በቅርብ ጊዜ ለተነሡ ለአዲሶች አባቶቻቸውም ላልፈሩአቸው አማልክት ሠዉ። የወለደህን አምላክ ተውህ፥ ያሳደገህን እግዚአብሔርን ረሳህ። ወንዶችና ሴቶች ልጆችም ስላስቈጡት እግዚአብሔር አይቶ ጣላቸው። እርሱም አለ። ፊቴን እሰውርባቸዋለሁ፤ ፍጻሜያቸው ምን እንደ ሆነ አያለሁ፤ ጠማማ ትውልድ፥ ያልታመኑም ልጆች ናቸው። አምላክ ባልሆነው አስቀኑኝ፤ ፫ ቍ.፲፭፤ በዕብራይስጥ ይሹሩን የሚለውን ግዕዙ ያዕቆብ ይለዋል። በምናምንቴዎቻቸውም አስቈጡኝ፤ እኔም ሕዝብ ባልሆነው አስቀናቸዋለሁ፤ በማያስተውል ሕዝብ አስቈጣቸዋለሁ። እሳት ከቍጣዬ ትነድዳለችና፥ እስከ ሲኦል ድረስ ታቃጥላለች፥ ምድርንም ከፍሬዋ ጋር ትበላለች፥ የተራሮችን መሠረት ታነድዳለች። መከራን እጨምርባቸዋለሁ፤ በፍላጾቼም እወጋቸዋለሁ።”

ይህ ከብዙ ዘመናት በፊት የእስራኤል ልጆች ለእግዚአብሔር የተለዩና የተቀደሱ ተብለው የእርሱን ስምና ክብር የወረሱበት የህይወት ህግና ሥርዓት አሁን ላለን ለእኛ ለኢትዮጵያውያን የሚያስተላልፍልን መለኮታዊ ሀሳብ፤ እግዚአብሔር አምላክ እንደ እስራኤል ልጆች ሁሉ ኢትዮጵያውያንንም የ”እኔ” ብሎ “ልጆቼ” ያላቸው በምድር አፈር በኩል በተግለጠው ህግና ሥርዓት በኩል ነበር።

ኢትዮጵያውያን ልክ እንደ እስራኤል ልጆች ሁሉ ይህን “እግዚአብሔር” ብለው የወረሱትን የተፈጥሮ ህግ ካፈረሱና ከጣሱ እንዲሁም ለእነርሱ ያልሆኑት የአህዛብን አማልክት በምድሪቱ ውስጥ ሲያጥኑና ሲያመልኩ ከተገኙ እነርሱም ለእስራኤል ልጆች እንደተነገራቸው ቃል ሁሉ በሞትና በባርነት ፍርድ ከተቀደሰችው ምድር ይነቀላሉ። እግዚአብሔር አምላክ የእስራኤልን ልጆች በተናገረበት ቃል ሁሉ ደግሞ ኢትዮጵያውያንን ተናግሯልና።

በዚህም መለኮታዊ ቃል መጠን የተገለጠውና ለተቀደሰችው ምድር ለኢትዮጵያ ጥፋትና ሞት የሆነው ትውልድ ደግሞ የአፄ ምኒልክ ትውልድ ይሆናል ማለት ነው። ለዚህ ታላቅ የሕይወትና የነጻነት የበረከትና የገዥነት ኪዳን መፍረስ ዋናው ተጠያቂው ይህ ደካማ ትውልድ ነው። ያን ታላቅና ሊነገር የማይችል ፅኑ ፍቅር በብዙ ተዓምራቶችና በብዙ ድንቆች ያየና የተመለከተ ህዝብ ነው ያን የሕይወት ኪዳን ሽሮ የሊሎችን/የአህዛብን አማልክት ለመተልና ለማምለክ ወደ ኋላው የተመለሰው። የአድዋ የነፃነት ተጋድሎ ብቻ ስለዚህ የህወትና የነጻነት የገዥነትና የበረከት ኪዳን ኃይልና ስልጣን እጅግ ብዙ ነገር ነበረው። አሸናፊ፣ አዳኝ፣ ገዥ እንዳልሆነ በዚያም የጥፋ ህግ ምንም ዓይነት በረከትም ይሁን የነጻነትና ህይወት እንደሌለ እግዚአብሔር አምላክ ሊዋሽ በማይችል ምስክር በዓለም ሁሉ ፊት በምድርና በሰማይ በዚህ ህዝብ ላይ አስመስሮበታል። ይሁን እንጅ ለመመለስ የተጸጸተ ትውልድ አልነበረም።

በኢትዮጵያ ታሪክ ባልታየውና እጅት ታላቅ በተባለለት በዛ ጽኑ የረሀብ ዘመን ኢትዮጵያውያን የሚላስና የሚቀመስ አጥተው ሲቅበዘበዙ ምግብና መጠጥ ሆኖ ያዳናቸውን፣ በምድረ በዳም ተዘግተው በቅኝ ግዛት ሊገዛቸው በፊታቸው ከተገለጠው እጅግ አስፈሪ የሞትና የጥፋት መንግስት የተነሳ የሚታደጋቸው አንድ ሰው አጥተው በሞት ፍርሀት ታስረው ሲታወኩና ሲጨነቁ ሳሉ በሚደነቅ ምህረት በብዙ ፍቅር በመካከላቸው ተገኝቶ ያጽናናቸውን፣ በዘመናዊ የጦር መሳሪያ በእጅጉ የተደራጀውን በወታደራዊ ዕውቀትና ጥበብም የተካነውንና ሊሸነፍ አይችልም የተባለውን ግዙፉን የኢጣልያንን ጦር በተዘረጋች ክንድ በበረታችም እጅግ ፅኑ እጅ ስብርብሩን አውጥቶ በፊታቸው ያባረረላቸውን፣ ገዳዩን ገድሎ፣ አሳሪውን አስሮ ፣ አጥፊውን አጥፍቶ ፣ በዓለም ሁሉ ላይ እጅግ የገነነውን ሁሉን ገዥ ስምና ክብር የሰጣቸውን የአባቶቻቸውን አምላክ የሰራዊት ሁሉ ጌታ እግዚአብሔርን ያ ትውልድ በአይኑ አይቷል፤ ተመልክቷልም። ኢትዮጵያውያንም ብቻ ሳይሆኑ ዓለም ሁሉ አይቶታል ተመልክቶታል። ያ የእግዚአብሔር ድንቅ ፍቅር የቀመሰ ትውልድ ነው እንግዲህ የእግዚአብሔርን ኪዳን አፍርሶ ለእርሱ ላልሆኑ ለአህዛብ አማልክት ሊያጥንና ሊሰግድ ራሱን ለሞትና ለባርነት አሳልፎ የሰጠው። ምንም እንኳ በተደጋጋሚ ቢናገራቸውም መልሰው ለኃጢአት ባሪያ እንደሚሆኑት እንደ እስራኤል ልጆች ሁሉ ኢትዮጵያውያንም የእግዚአብሔርን እጅግ ታላቅ ውለታና ፍቅር ረስተውና አቅልለው በፊቱ ታላቅ ርኩሰትን አደረጉ።

የእግዚአብሔር ቃል ለዚህ ታላቅ ቅሌትና አመጻ ተጠያቂ ያደረገው ደግሞ በዋናነት “ይሹሩን” በማለት የገለጸውን በዚያ ህዝብና መንግስት ላይ ኃይልና ስልጣን ያላውን አለቃ ወይም መሪ ነው። ይሹሩን በማለት ሙሴ የገለጸው በእርግጥ ለአስራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል አባትና አለቃ የሆነውን ያዕቆብን ነው። አስራ ሁለቱ ነገዶች እንደመንግስታን እንደ ሀገር የተመሰረቱት በአባታቸው በያዕቆብ እስራኤል በሚለው ስምና ክብር ነበርና። ይሹሩን የያዕቆብ ሌላው ስም ነው። እንደ ሙሴ አገላለጽም ይሁን እንደ ህጉ አንድ ለእግዚአብሔር ስምና ክብር የተመረጠ ህዝብ ለጥፋት በሚሆን የሞትና የባርነት ህግ የሚያዘው በዚያ ህዝብ ላይ ኃይልና ስልጣን ባለው አንድ ሰው አለመታዘዝ ምክኒያት ነው። የዛ ህዝብ ማንነትና ምንነት በመሪው ማንነትና ምንነት የሚገለጽ ስለሆነ የመሪው ጥፋት ማለት በሌላ አባባል የዚያ ትውልድ/ህዝብ ጥፋት ማለት ይሆናል። ልክ ዛሬ እንደምናየው!

ለተቀደሰችው ምድር ርኩሰት፣ ለታላቋና ለገናናዋ ሀገር ለኢትዮጵያ ጥፋትና ውድቀት በዋናነት ተጠያቂ የሚሆኑት በእግዚአብሔር ስምና ክብር ተመርጠው “ሞዓ አንበሳ እም ዘነገደ ይሁዳ ምኒልክ ስዩመ እግዚአብሔር ንጉሰ ነገስት ዘ-ኢትዮጵያ” ተብለው የነገሱት አፄ ምኒልክ ናቸው። (ልብ እንበል! አፄ ምኒልክ በአክሱም ጽዮን ተቀብተው ያልነገሱ ብቸኛው የኢትዮጵያ ንጉሥ ናቸው)። አፄ ምኒልክ ከአደዋው ድል በኋላ ለድሉ ያበቃቸውን አምላካቸውንና ጽዮን ማርያምን በመካድ ከእግዚአብሔር ጋር የነበራቸውን የህይወት ኪዳን አፍርሰው የጥፋትና የሞት የባርነት አማልክት ማንነትና ምንነት በመትከላቸው ለኢትዮጵያ ጥፋትንና ውድቀትን አስከትለዋል። ውጤቱን ዛሬ እያየነው እኮ ነው!

ጥልቅ በሆነ የጸሎት ጊዜ ውስጥ የሚገኝ ወገን ሁሉ ጋላ-ኦሮሞዎች ላለፉት መቶ ሰላሳ ዓመታት በጽዮናዊው ሕዝባችን ላይ የሠሩትን ግፍና በደል ጭንቅላቱ ውስጥ በተነቀሳቃሽ ምስል መልክ ማየት ይችላል። እንኳን የዛሬውን ቀርቶ የቀደሙት አባቶቻችንና እናቶቻችንን ስቃይ፣ ሰቆቃና ጩኸት እንደ ደወል መስማት ይችላል። ወገኔ ሆይ፤ ዲቃላ የስጋ ማንነትና ምንነት ያላቸው ዋቄዮ-አላህ-ዲያብሎስን አምላኪዎቹ ጋላ-ኦሮሞዎችና ጋላማራዎች በሕዝቤ ላይ ከምንገምተው በላይ አስከፊ የሆነ ግፍና ወንጀል ነው የፈጸሙበት በመፈጸም ላይ ያሉት።

😇 ፈጣኑ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ አስቀድሞ የተጣላህን በቀል ባለመርሳት ጋሻህን በቶሎ አንሣ። ፈጣኑ መልአክ ሆይ ነበልባላዊ ሰይፍህን በጠላታችን በዋቄዮ-አላህ-ዲያብሎስ ላይ መዘህ ተነሣሣበት።

😇 ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ሆይ፤ ከሰማያት በግርማ ወርደህ አሸባሪውን ዲቃላ አብዮት አህመድ አሊን እና ጭፍሮቹን ባፋጣኝና በአንዲት ሌሊት በእሳት ሰይፉ ፈጅተኻቸው እደር።

😇 ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ሆይ፤ ጋላ-ኦሮሞ-አማሌቅ ጠላቶቻችንና ዋቄዮ-አላህ-ሰይጣን አምላካቸውን በሰይፉ ቆራርጦ ከእግራችን ስር ይጣልልን!

😇 የገናናው መልአክ የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃው አይለየን፣ በጸሎቱ ይማረን።

______________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን (ጸበል) ሕንፃ ላይ ነፈሰ = የቅዱስ ያሬድ ጸናጽል ውብ ዜማ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 20, 2022

✞✞✞ብዙ ፈውሶች የተካሄዱባት የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን (ፀበል) አዲስ አበባ ✞✞✞

የተጠመቅኩት፣ በመሰቀል የተሰቀልኩትና የተሰዋኹት ለአመኑኝና ቃሌን ለተቀበሉኝ ሁሉ ለስጋቸው በረከት ለነፍሳቸው ድኽነት ለመስጠት ነው!”

ለእያንዳንዱ ለተጠመቀው ክርስቲያን፣ ስጋው ለተቆረሠለት፣ ደሙ ለፈሰሰለትና እግዚአብሔር ሰው ለሆነለት ክርስቲያን ጠባቂ መላእክት አሉት።

ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ከፍተኛ የትምህርት ተሰጥዎ ያለው በመሆኑ ትምህርቱን በጣም አስደናቂ በሆነ መንገድ ፈጽሞ ዲያቆን ሆነ ፡፡ ከመምህሩ ከአባ ጌዴዎን በተማረው መሠረት የእብራይስጥና የግሪክ ቋንቋዎችን ደህና አድርጉ ያውቅ ነበር ይባላል ፡፡ ስለዚህ በመጽሐፍ ቅዱስና እንዲሁም በውጭ አገር ቋንቋዎች የአጉቱን የመምህር ጌዴዎንን ሙያ አጠናቆ ቻለ ፡፡ ያሬድ አጉቱ ሲሞት የዐሥራ አራት አመት ልጅ ቢሆንም የአጉቱን ሙያና የትምህርት ወንበር ተረክቦ ማስተማር ጀመረ። በግንቦት ፲፩ (11) ቀን ስንክሳር በተባለው የቅዱሳን የሕይወት ታሪክ መጽሐፍ ውስጥ ያሬድ በመንፈስ ቅዱስ ተመርቶና ተነሣሥቶ የዜማ ድርሰቶቹን አዘጋጀይላል።

በዚሁ ስንክሳር እንደ ተጻፈው እግዚአብሔር በዚች ምድር እንዲመስገን በፈለገ ጊዜ ያሬድን በራሱ ቋንቋ ሰማያዊ ዜማ እንዲያስተምሩት በአእዋፍ አምሳል ሦስት መላእክትን ከገነት ላከለት ይላል ፥፡ እነሱም ያሬድ ካለበት ሥፍራ አንጻር ባለው አየር ላይ ረበው(አንዣብበው) ጣዕም ያለውና ልብን የሚመስጥ አዲስ ዜማ አሰሙት ፡፡ ያን ጊዜ ያሬድ በጣዕመ ዜማቸው ተመስጦ ቁሞ ሲያዳምጥ ወዲያውኑ ወፎቹ በግዕዝ ቋንቋ ብጹዕ ወክቡር አንተ ያሬድ ብጽፅት ከርሥ አንተ ጾረተከ ውብጹዓት አጥባት አላ ሐአናከብለው በአንድነት አመስግኑት። ትርጉሙ የተመሰገንክና የተክበርክ ያሬድ ሆይ ፡ አንተን የተሸከመች ማኅፀን የተመስገነች ናት ፡፡ አንተን ያሳደጉ ጡቶችም የተመሰገኑ ናቸውብለው አመሰገኑት፡፡

ከዚያም ሐያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ዜማ ወደ ሚዘምሩበት ወጋ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም አሳረጉት ፡፡ ቅዱስ ያሬድም በመንበረ ጸባዖት ፊጓ ቁሞ ከሐያ አራቱ ካህናተ ሰማይ በፍጥነት የሰማው ማኀሌት ሁቦ በመንፈስ እግዚአብሔር ተገለጸለትና በልቦናው የተሣለበትን ጰዋትዜ ዜማ በቃሉ ያዜም ጀመር ፡፡ ከዚያም ወደ ቀድሞ ቦታው ወደ አክሱም በተመለሰ ጊዜ ክጥዋቱ በ፫ ሰዓት ወደ አክሱም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብቶ በታቦተ ጽዮን አንጻር ቆሞ እጆቹን ወደ ሰማይ ዘርግቶ ፡ በከፍተኛ ድምፅ በአራራይ ዜማ ሃሌ ሉያ ለአብ ፡ ሃሌ ሉያ ለወልድ ፡ ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ ቅዳሜሃ ለጽዮን ሰማየ ሳረረ ወዳግም አርአዮ ለሙሴ ዘክመ ይገብር ግብራ ለደብተራብሉ ሥነፍጥረቱንና ሰማያዊት ጽዮንን አሰመልክቶ ዘመረ ይህችንም ማኅሌት አርያም ብሎ ጠራት ዞ አርያምም ማለት ልዕልና ሰባተኛ ሰማይ መንበረ እግዚአብሔር ማለት ነው ፡፡ ያሬድ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተመርቶ መላእክት እንደ ከበሮ እንቢልታ፣ ጸናጽል ፣ ማሲንቆና በገና በመሳሰሉት የማኅሌት መሣሪያዎች እየዘመሩ አምላካቸውን እግዚአብሔርን ሊያመሰግኑ ስለስማ እነዚህን መሣሪያዎች በሥራ ላይ እንዲውሉ አደረጋቸው ፡፡

✞✞✞[ፈጥኖ የሚረዳን የቅዱስ ሚካኤል ክብር በሊቁ በቅዱስ ያሬድ ድጓ]✞✞✞

  • 😇 የ፺፱/99ኙ ነገደ መላእክት አለቃ ስለኾነው ስለ ቅዱስ ሚካኤል ክብር፣ ውበት፣ ምልጃ ማሕቶተ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ያሬድ በመጽሐፈ ድጓው እንዲኽ ይላል፦
  • ክብረ ሚካኤል ናሁ ተዐውቀ
  • በትሕትናሁ ዐብየ ወልሕቀ
  • ዲበ አእላፍ ዘተሰምየ ሊቀ
  • ዘይትዐፀፍ መብረቀ ይተነብል ጽድቀ”

(የሚካኤል ክብረ እነሆ አኹን ታወቀ፤ በትሕናውም ፈጽሞ ላቀ ከፍ ከፍ አለ፤ በአእላፍ ነገደ መላእክት ላይ አለቃን የተባለ መብረቅን የሚጐናፀፍ ርሱ ጽድቅን ይለምናል) ይላል፡

የ፺፱/99ኙ ነገደ መላእክት አለቃ ከመኾኑ ጋር ይልቁኑ ዮሐንስ በራእዩ በምዕራፍ ፰፥፪ ላይ “በእግዚአብሔርም ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ” ካላቸው፤ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት በመዠመሪያ የሚጠቀሰው ቅዱስ ሚካኤል ነውና ሊቁ ያሬድ፡

❖ “እስመ እምአፉሁ ይወጽዕ ነጐድጓድ

  • ሕብረ ክነፊሁ ያንበለብል ነድ
  • እምሊቃነ መላእክት የዐቢ በዐውድ
  • ሚካኤል ውእቱ መልአኩ ለወልድ”

(የወልድ አገልጋዩ ሚካኤል ነው፤ በዙሪያው ኹሉ ካሉት ከሊቃነ መላእክት ይበልጣል፤ የክንፉ መልክ ነባልባላዊ እሳትን ያቃጥላል፤ ከአንደበቱ ነጐድጓድ ይወጣልና) ይላል፨

❖ “አዕበዮ ንጉሠ ስብሐት

  • ለሚካኤል ሊቀ መላእክት
  • ዘይስእል በእንተ ምሕረት
  • መልአከ ሥረዊሆሙ ለመላእክት”

(የምስጋና ባለቤት ክርስቶስ ለመላእክት ጭፍሮች አለቃቸው የኾነ ስለ ምሕረት የሚማልድ የመላእክት አለቃ ሚካኤልን ከፍ ከፍ አደረገው) በማለት ይጠቅሰዋል፡፡

የስሙ ትርጓሜንም ስንመለከት ሚካኤል ማለት ቃሉ የዕብራይስጥ ሲኾን ሚማለት “ማን”፤ ካ– “እንደ”፤ ኤል– “አምላክ” ማለት ነውና ሚካኤል ማለት “መኑ ከመ አምላክ” (ማን እንደ አምላክ) ማለት ነው፡፡

የመልክአ ሚካኤል ደራሲም ይኽነን ይዞ

❖ “ሰላም ለዝክረ ስምከ ምስለ ስመ ልዑል ዘተሳተፈ

  • ወልደ ያሬድ ሄኖክ በከመ ጸሐፈ”

(የያሬድ ልጅ ሄኖክ እንደጻፈው ከልዑል ስም ጋር ለተባበረ ስም አጠራርኽ ሰላምታ ይገባል) ይለዋል፡፡

😇 ቅዱስ ያሬድም፡

❖ “መልአከ ፍሥሐ ሚካኤል ስሙ

  • ለመላእክት ውእቱ ሊቆሙ
  • መልአኮሙ ሥዩሞሙ
  • የሐውር ቅድሜሆሙ እንዘ ይመርሆሙ”

(ስሙ ሚካኤል የተባለ የደስታ መልአክ ለነገደ መላእክት አለቃቸው ነው፤ የተሾመላቸው አለቃቸው ርሱ እየመራቸው በፊት በፊታቸው ይኼዳል) ይላል

በብሉይ ኪዳን ለአበው ነቢያት እየተገለጠ፤ ለሐዋርያትም በስብከት አገልግሎታቸው እየተራዳ፤ ለሰማዕታት፣ ለቅዱሳን አበው በተጋድሏቸው እየተገለጠላቸው አስደሳች መልኩን ያዩት ነበር።

ይኽነን የቅዱስ ሚካኤልን ውበት ቅዱስ ያሬድ እንዲኽ ይገልጠዋል፡

❖ “መልአከ ፍሥሐ ዘዐጽፉ መብረቅ

  • ሐመልማለ ወርቅ ሚካኤል ሊቅ”

(መጐናጸፊያው መብረቅ የኾነ የደስታ መልአክ፤ አለቃ ሚካኤል የወርቅ ዐመልማሎ ነው)

የመልክአ ሚካኤል ደራሲም ይኽነን ውበቱን ሲገልጠው፡

❖ “ሰላም ለአክናፊከ እለ በሰማያት ያንበለብሉ

  • ከመ ሠርቀ ፀሓይ ሥነ ጸዳሉ”

(የጸዳሉ ውበት እንደ ፀሓይ አወጣጥ የኾነ በሰማያት ለሚያንበለብሉ ክንፎችኽ ሰላምታ ይገባል) ይለዋል፡፡

ቅዱስ ያሬድ ደግሞ፡

❖ “ውእቱ ሊቆሙ ወመልአኮሙ ሚካኤል ስሙ

  • ዐይኑ ዘርግብ ልብሱ ዘመብረቅ
  • ሐመልማለ ወርቅ”

(ዐይኑ የርግብ (እንደ ርግብ የዋህ፣ ጽሩይ) የኾነ ልብሱ የመብረቅ መጐናጸፊያ የኾነለት የወርቅ ዐመልማሎ ስሙ ሚካኤል የተባለ ርሱ የመላእክት አለቃቸው መሪያቸው ነው) ይላል፡፡

የቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነትና አማላጅነት ቅዱስ ያሬድ እንዲኽ ይገልጠዋል፡

በ፲ወ፬ቱ ትንብልናከ ዐቢይ ልዕልናከ

  • በመንክር ትሕትናከ
  • አስተምህር ለነ ሰአልናከ”

(በዐሥራ አራቱ ልመናኽ ምልጃኽ፤ በታላቅ ልዕልናኽ በሚያስደንቅም ትሕትናኽ ሚካኤል ትለምንልን ዘንድ ማለድንኽ)

❖ “ዘወሀበ ትንቢተ ለኤልዳድ ወሙዳድ

  • አመ ምጽአቱ ይምሐረነ ወልድ
  • ሰአል ለነ ሚካኤል መንፈሳዊ ነገድ
  • ከመ ንክሃል አምስጦ እምሲኦል ሞገድ”

(ለኤልዳድና ለሙዳድ የትንቢትን ጸጋ የሰጠ የሚኾን ወልድ በሚመጣ ጊዜ ይምረን ዘንድ ከረቂቅ ነገድ ወገን የኾንኸው ሚካኤል ከሲኦል እሳታዊ ሞገድ ማምለጥ እንችል ዘንድ ለእኛ ለምንልን) ይላል፡፡

❖ “ከናፍሪሁ ነድ ዘእሳት አልባሲሁ ዘመብረቅ ሚካኤል ሊቀ መላእክት ውእቱ ይዕቀብክሙ ነግሀ ወሠርከ ሌሊተ ወመዐልተ” (ከናፍሮቹ የእሳት ልብሶቹ የመብረቅ የኾነ የመላእክት አለቃ ሚካኤል በተራኢነቱ በጠዋትም፤ በሠርክም፤ በቀንም በሌሊትም ይጠብቃችኊ) አለ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ፨

😇 ፈጣኑ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ አስቀድሞ የተጣላህን በቀል ባለመርሳት ጋሻህን አንሣ። ፈጣኑ መልአክ ሆይ ነበልባላዊ ሰይፍህን በጠላታችን በዲያብሎስ ላይ መዘህ ተነሣሣበት።

______________

Posted in Ethiopia, Faith, Saints/ቅዱሳን, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ፈጣኑ መልአክ ሆይ ነበልባላዊ ሰይፍህን በጠላታችን በዲያብሎስ ላይ መዘህ ተነሣሣበት

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 21, 2020

እንኳን ለሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤል አመታዊ የንግስ በዓል አደረሳችሁ። በዓሉን የበረከት በዓል ያድርግልን።

_______________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የተአምረኛው ቅዱስ ሚካኤል ፀበል | የተጠመቅኩት ለአመኑኝ ሁሉ በረከትና ድኽነት ለመስጠት ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 23, 2019

የተጠመቅኩት፣ በመሰቀል የተሰቀልኩትና የተሰዋኹት ለአመኑኝና ቃሌን ለተቀበሉኝ ሁሉ ለስጋቸው በረከት ለነፍሳቸው ድኽነት ለመስጠት ነው!”

ለእያንዳንዱ ለተጠመቀው ክርስቲያን፣ ስጋው ለተቆረሠለት፣ ደሙ ለፈሰሰለትና እግዚአብሔር ሰው ለሆነለት ክርስቲያን ጠባቂ መላእክት አሉት።

_____________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ዛሬ፡ ቅዱስ ሚካኤል፡ ድል በተነሳውና በወደቀው በዲያብሎስ ምትክ፡ ሊቀ መላእክት ሆኖ የተሾመበት ዕለት ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 19, 2019

እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል አመታዊ በዓል አደረሰን

ላፍቶ ቅዱስ ሚካኤል ፥ ፳፻፲ ወ ፩ ዓ.

መንፍሰን የሚያድስ ሌላ ልዩና ውብ የቤተክርስቲያን ግቢቤተክርስቲያኗን እና ሕፃናት ልጆቿን እንዲህ በትዕግሥት፣ በትጋትና ፍቅር ለሚንከባከቧቸው አባቶች፣ እናቶች፣ ወንድሞች እና እህቶች ምስጋና ይገባል። በእውነት አዲስ አበባ የተዋሕዶ ዓብያተክርስቲያናት ባይኖሩ ኖሮ ከተማዋ አዲስ በረሃ ትባል ነበር።

ይትዐየን መልአከ እግዚአብሔር ዐውዶሙ ለእለ ይፈርህዎ ወያድኅኖም ጣዕሙ ወታእምሩ ከመኄር እግዚአብሔር። መዝ.፴፫ (፴፬)

መላእክት የሚለው ቃል መልእክተኞች ተላላኪዎችየእግዚአብሔር ይቅርታ ወደ ሰው የሰውን ልመና ወደእግዚአብሔር የሚያደርሱየእግዚአብሔር ልዩ ወዳጆች ማለት ነው፡፡ በሌላ መልኩ አለቆች ገዥዎች ወይም የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪዎች ማለት ይሆናል፡፡ ሚካኤል ማለት መኑ ከመ እግዚአብሔር እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው?” ማለት ነው፡፡ ሚካኤል በስም ተለይቶ መጠቀስ የተጀመረው በመጽሐፈ ዳንኤል /ዳን.፲፥፲፫፪፥፩/ ውስጥ ነው፡፡ በመጽሐፈ ሄኖክም ለበርካታ ጊዜያት ተጠቅሷል፡፡ከዚህ ሌላ በብሉይ ኪዳን አዋልድ መጽሐፍት በኪዳነ አብርሃም ውስጥ ተጠቅሶም ይገኛል፡፡

ቅዱስ ሚካኤል ለፍጥረታት ሁሉ የሚራዳና የሚያዝን የምሕረትና የመዳኛ፤ የሰላም መልአክ ነው፡፡ በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል” /ዳን.፲፪፥፩/ በማለት በነቢዩ ዳንኤል የተነገረ ሲሆን በሌላ ቦታ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ” /ዳን. ፲፥፲፫/ በማለት ያስረዳል፡፡ በዚህ ቃል ላይ ከዋንኞቹ አለቆች አንዱ የሚለውን በመያዝ ሚካኤል ብቻ የመላእክት አለቃ አይደለም የሚሉ አሉ፡፡ ነገር ግን የሌሎች አለቅነት የተወሰነ ወይም ዝቅተኛ ሲሆን በአንድ ነገድ ላይ በአንድ የመላእክት ከተማ ላይ ነው፡፡ የቅዱስ ሚካኤል አለቅነት ግን በመላእክት ሁሉ ላይከሆነ ከሌሎቹ ይለያል፡፡ በድርሳነ ሩፋኤል ላይ እንደተገለጸው ሰባት ሊቃነ መላእክት ቢኖሩም አለቃቸው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡

ቅዱስ ሚካኤል አርምሞ ትዕግሥትን የሚወድ መልአክ ነው፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ ስለ ሙሴ ሥጋ ሲነጋገር ጌታ ይገሥጽህ አለው እንጂ የስድብን ፍርድ ሊናገረው አልደፈረምቅዱስ ሚካኤል ከእግዚአብሔር በተሰጠው ኃይል ዲያብሎስን ድል የነሣ መልአክ ነው፡፡ በሰማይ ጦርነት ተነሣ ሚካኤልና እርሱ መላእክት ከዘንዶው ከመላእክቱም ጋር ተዋጉ” /ራእ. ፲፪፥፯/ ይላል፡፡

የቅዱስ ሚካኤል በዓል ሰኔ ፲፪ የሚከበርበት ምክንያት ዲያብሎስን በፈቃደ እግዚአብሔር ተዋግቶ ያሸነፈበት አምላክነትን ሽቶ በወደቀው በዲያብሎስ ምትክ ሊቀ መላእክት ሆኖ የተሾመበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡ ክብር ይግባውና እግዚአብሔር በዚህች ዕለት የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን ከወገኞቹ ከመላእክት ሁሉ በላይ አክብሮ ሹሞታልይላል ድርሳነ ሚካኤል

ከዚህ በተጨማሪ ይህ ዕለት ቅዱስ ሚካኤል አፎምያን ያዳነበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡ በአንዲት አገር ሃይማኖቱ የቀና ታላቅ መኮንን ከሙ አስተራኒቆስ የሚባል ሰው ነበር፡፡ ሚስቱም አፎምያ ትባላለች፡፡አፎምያ ባልዋ አስተራኒቆስ ታሞ እያለ የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አስሎ እንዲሰጣት ለመነችው፤ እንዳለችው አደረገላትና ባልዋ ሞተ፡፡ ከዚህ በኋላ አፎምያ ባልዋ ያሠራላትን ሥዕል ይዛ በሃይማኖት ጻንታ ስትኖር ዲያብሎስ በተለያየ መልኩ ይፈትናት ጀመር፡፡ አንድ ጊዜ ባልቴት እየመሰለ ሌላጊዜ ሌላ እየሆነ ባል ማግባት እንዳለባት መከራት፡፡ መጽሐፍም ጠቀሰላት፡፡ ከንጉሡ ጋር ማጋባት እንዳሰበ ነገራት እርሷ ግን ማግባት እንደማትሻ እግዚአብሔርን እያገለገለች ኖራ ማለፍ እንደምትፈልግ ነገረችው፡፡ ዲያብሎስ ግን ፈተናውን እያባሰ እያባሰ መጣ፡፡ በመጨረሻ ግን በቅዱስ ሚካኤል ሥዕል አሳፍራ አዋረደችው፡፡

የሰኔ ሚካኤል ዕለት ዲያብሎስ ዳግመኛ ሊፈትናት መጣ፡፡ ሚካኤል ነኝ አላት፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ሰይጣን ራሱ የብርሃን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣል“/፪ቆሮ.፲፩፥፲፫/ እንዳለ በዚህን ዕለት የቀረባት ራሱን ለውጦ የብርሃን መልአክ መስሎ ነበር፡፡ አፎምያ ግን አስተዋይ ስለነበረች የብርሃን መልአክ ከሆንክ የመስቀል ምልክት ያለበት በትርህ ወዴት አለ?“ አለችው፡፡ በኛ በመላእክት ዘንድ የመስቀል ምልክት አይደረግም አላት፡፡ እርሷም ስለተጠራጠረችው የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ልታመጣ ወደ ሥዕል ቤቷ ስትገባ ዘለለና አነቃት፡፡ አፎምያ ጮኸች፤ ቅዱስ ሚካኤልም ፈጥኖ ደርሶ አዳናት ዲያብሎስንም አዋረደላት፡፡

ዲያብሎስ አፎምያ ያሰበችውን ጸጋ ሆኖ የተሰጣትን ኑሮ ትታ በተለየ ዓለም እንድትኖር እንደ መከራት በእኛም ሕይወት እንዲህ ሊያደርግ ይችላል፡፡ በጋብቻ ወቅት ምንኵስናን እንድናስብበዕርቅ ሰዓት ጥላቻ እንዲሰማንበሰላም ጊዜ ጦርነትንበጾም ጊዜ ምግብንበትዕግሥት ጊዜ ቁጣን በመረጋጋት ጊዜ አድመኝነትን በውስጣችን ሊያኖር ይችላል፡፡ ስለዚህ እንደ አፎምያ በእምነትና በምግባር ጸንተን በማስተዋል ልንኖር ይገባል፡፡

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት የቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት አይለየን፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ምንጭ፡ሐመር ፲፻፺፭ ግንቦት/ሰኔ

…………ሚካኤል ሆይ! የችግረኛውን ሁሉ ጸሎት ፈጥነው ለሚሰሙ አዕዛኖችህ ሰላምታ ይገባል። የይቅርታ መልአክ ሆይ! ችግሬን አቃልልኝ፤ ጭንቀቴንም አስወግድልኝ። ምክርን ትለግሰኝ ጥበብንም ታስተምረኝ ዘንድ አባት እንዳደረግሁህ አንተም ልጅ አድርገኝ።…………

ሚካኤል ሆይ ! ዳንኤል በአምሳለ አናብስት ምሳሌ ያየውን ሥውሩን ራእይ አብራርቶና ግልጥልጥ አድርጎ ለተረጎመለት አንደበትህ ሰላምታ ይገባል። የሰላም መልአክ ሆይ የምስጋናን መሥዋዕት የምታዘጋጅ አንተ ነህና ጠላት ዲያብሎስ ተረማምዶ በእደ ፃዕረ ሞት እንዳያፍነኝ በአፌ ላይ ጥበቃህን አጠንክር።…………

የቅዱስ ሚካኤል አምላክ ሆይ! በአርአያህ በአምሣልህ የፈጠርከን ሕዝቦችህን ሁሉ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ሠውረን ለዘላለሙ አሜን።

ቅዱስ ሚካኤል ወዳጅ ነህ ለሁሉ
ዛሬም ቆመሃል በኪዳንህ ላሉ
ክንፍህን ዘርጋ ሚካኤል ቅደም ከፍቴ
ምራኝ መንገዱን እንዳይመሽ ልድረስ አባቴ
እንደት ይገፋል ጎዳናው ያላንተ እርዳታ
ጥመን ቁረጠው በቤትርህ ጭንጫውን ምታ“()

ተጠመጠመ ጠላ በሳት ሰንሰለት
የጌታ መላአክ ካኤል በሰይፍ ወድቆበት
የለም በቦታው ስመለስ አጥቸዋለሁ
የምረዳኝን ተሹሞ አይቸዋለሁ“()

ከመቃብሩ ድንጋዩን አንከባለሃል
ስለረዳህው ዳንኤል እጅግ ወዶሃል
ይነዋወጣል ባህሩ አንተ ስትመጣ
እግዚአብሔር ይንገስ ድያብሎስ መድረሻ ይጣ“()

አለኝ ትዝታ በቤትህ ከልጅነቴ
ስትራራልኝ እያየው ጸንቷል ጉልበቴ
ልዘምር እንጅ ላመስግን ታላቁን ጌታ
አንተን የሰጠኝ ጠባቅ በቀን በማታ“()

ቅዱስ ሚካኤል ወዳጅ ነህ ለሁሉ፤ ዛሬም ቆመሃል በኪዳንህ ላሉ። አሜን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ ስለ እኛ ስለሰው ልጆች በጌታ ፊት ቁምልን ምልጃና ጸሎትህ ተራዳእነትህ ጥበቃህ ለዘወትር አይለየን!! አሜንንንንንን።

__________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ቅ/ሚካኤል የአሥር ዓመት ዓይነ-ሥውር አበራ — Miracles of Archangel Michael

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 20, 2011

የአገራችንን ዓብያተ ክርስቲያናት ልዩና ቅዱሳዊ ከሚያደርጓቸው ነገሮች መካከል የቤተክርስቲያኖቹ ሕንፃዎች ዛፎችንና አእፅዋታትን ከተፈጥሮ ጋር በተስማማ መልክ አብቀለው ለምዕመናኑ አመች የሆነ ሁኔታ መፍጠር መቻላቸው ነው።

እላይ ቪዲዮው ላይ በከፊል እንደሚታየው ምዕመናኑ የቤተክርስቲያኖቹ ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኙት ውብ የተፈጥሮ ሣሮች፡ አበቦች ወይም ዛፎች አጠገብ በመሆን እንዲሁም ቀዝቀዝ ያለውንና ነፋሻማውን ንጹህ አየር እየተቀበለ ለፈጣሪው ጸሎቱን ያደርሳል።

ብዙ ዓብያተ ክርስቲያናትን በመላው ዓለም ተዘዋውሬ ለማየት በቅቻለሁ፡ ነገር ግን ከእግዚአብሔር ጋር በቀላሉ ሊያገናኙ የሚችሉትና ለመንፈሳዊ ሕይወት በጣም አመቺ የሆኑ ዓብያተ ክርስቲያናት በኢትዮጵያ እንደሚገኙ አሁን ለመገንዘብ በቅቻለሁ። ይህን ለመሰለው ጸጋ እግዚአብሔርን ልናመሰግነው ይገባል። ምናልባት ይህ እድል አሁን በእጃችን ስላለ ላንገነዘበው እንችል ይሆናል፡ ሆኖም ግን በመልክአምድር እንደ አዲስ አበባ ከፍ ብለው በሚገኙ ቦታዎች ላይ የቤተክርስቲያኖች ቁጥር በዓለም በብዛት የሚገኘው በኢትዮጵያ ነው። ይህ እራሱ እንደ አንድ ትልቅ ምልክት ሊሆነን ይገባል፡ ቤተክርስቲያን ልጆቿን ለመጭው ጊዜ እያዘጋጀች ነውና!

በዘመኑም ፍጻሜ የእግዚአብሔር ቤት ተራራ በተራሮች ራስ ላይ ጸንቶ ይቆማል፥ ከኮረብቶችም በላይ ከፍ ከፍ ይላል፥ አሕዛብም ሁሉ ወደ እርሱ ይሰበሰባሉ።” {ኢሳያስ 22}

/ሚካኤል የአሥር ዓመት ዓይነሥውር አበራ

የደወሌ ቅ/ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ከድሬዳዋ ማሥራቃዊ ክፍል በኢትዮጵያና በጅቡቲ ወሰን አቅራቢያ በረሃማ በሆነችው ከተማ ነው።

በደወሌ በረሃማ ሥፍራ ላይ በተመሠረተው የቅ/ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ልዩ ልዩ ተአምራት ታይቷል።

ከነዚህም አንድ ዓይነሥውር ከማየቱም በላይ ሁለተኛው ሊቀ መላእክት ቅ/ሚካኤል የተወሰደበትን ቆርቆሮ በተአምር ወደ ቤተ መቅደሱ መመለሱ ነው።

ዓያናቸው የበራው ግለሰብ አቶ ጥላሁን ታደሰ የሚባሉ የድሬዳዋ ከተማ ነዋሪ ለዓይናቸው መታወር መነሻው በውሃና ፍሳሽ አገልግሎት የቦኖ ውሃ አስቀጂ ሆነው በሚሠሩበት ወቅት ቢርካውን ሲከፍቱ እንደ ደም ያለ ነገር ይታያቸዋል ከዚህም ጋር የጋዜጣ ንባብ ሱስ ስለነበራቸው አዘውትረው ጋዜጣ ያነቡ ነበር። በእነዚህ ሁለቱ ምክንያቶች በየትኛው ዓይናቸው እንደጠፉ በትክክል ባይታወቅም ዓይናቸው ደም ካየበት ጀምሮ እየደከመ መምጣቱን በዝርዝር ገልጸዋል።

አቶ ጥላሁን እንዳስገነዘቡት ከልጅነቴ ጀምሮ ቅ/ሚካኤልን እወደዋለሁ አከብረዋለሁ እዘክረዋለሁ ግን ዓይኔ በመታወሩ ምክንያት ከሥራ ተወገድኩ ለመኖር ስል አንድ መሪ ልጅ ይዤ ከድሬዳዋ ደወሌ በመመላለስ የጫት ንግድ ጀመርኩ በዚህም ምክንያት በሄድኩ ቁጥር በረኸኛው ቅ/ሚካኤል በድርሳንህ እንደሚነገረው ብዙ ተዓምር ሠርተሃል በእኔም ላይ ተአምርህን አሳይ እለው ነበር። በንግዱ የዕለት ጉርሴን የዓመት ልብሴን በሚገባ እያገኘሁ የደወሌን ቅ/ሚካኤል አጥብቄ እማፀነው ነበር። ዕለቱ ማክሰኞ ሐምሌ 12 በዚሁ ዕለት የደወሌው ቅ/ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተባርኮ እንደሚገባ ባለቤቴ ነገረችኝ እኔ ግን እጄም እግሬም በመተሣሠሩ ምክንያት አንቺ ሄደሽ አክባሪ አልኳት ሄዳ አክብራ ተመለሰች።

በዚሁ የቅ/ሚካኤል ዕለት ልጄን ይዤ ዳቦዬን አቅርቤ ከዘከርኩ በኋላ ከጐረቤቶቼ ጋር ጠበሉን ጸዲቁን ቀምሰን ቅ/ሚካኤልን አመስግነን ጐረቤቶቼ ሲወጡ ጋደም አልኩ እንቅልፍ ያዘኝ በእንቅልፍ ላይ እንዳለሁ አንተ አንተ የሚል የጥሪ ድምፅ ሰማሁ ድምፁም ተደጋግሞ መጣ ብድግ አልኩ ልጁን ብጠራው የለም ነገሩ ግራ አጋባኝ በቤቴ ወለል ላይ በመተከዝ እንዳለሁ አንተ አንተ አታየኝም እንዴ? አለኝ እኔም መልሼ እኔ እኮ ዓይን የሌለኝ በመሆኔ ላይህ አልችልም አልኩ፤ መልሶም እኔ የደወሌው የመቶ አለቃ ኃይለ ሚካኤል ነኝ እንዴት አታውቀኝም አለኝ እኔም በደወሌ የማውቀው መቶ አለቃ ገበየሁን ነው አልኩት ዕለቱ ቅ/ሚካኤል በመሆኑ ከልጅነት የምማፀነው ቅ/ሚካኤል ይሆናል በዬ አስብ ነበር።

ሆኖም የደወሌው መቶ አለቃ ኃይለ ሚካኤል ነኝ ሲለኝ ልቤ በደስታ እየመላ መጣ እሱም በመቀጠል የለበስኩት ምንድር ነው? የእኔስ መልክ ምን ይመስላል? ሲል ጠየቀኝ፤ እኔም የለበሰው ልብስ በኮከብ የተጥለቀለቀ መሆኑንና መልኩም ቀይ እንደሆነ ነገርኩት ከዚህ በኋላ ለ10 ዓመታት ብርሃን አጥቶ የኖረው ዓይኔ ለማየት በመታደሉ በደስታ ተመላሁ ከዚሁም ቀጥሎ መሉ እንደ ብርሃን የሚያበራው ይኽ ሰው በቀጥታ እያየሁት የወርቅ ኃብል በአንገቴ ላይ አጠለቀልኝ የዓይኔን ብርሃን አረጋግጦ የድሮውን የወታደሮች ካኪ ልብስ አለበሰኝ ወርቁንም ሆነ ልብሱን ለማንም እንዳትሰጥ በማለት አስጠነቀቀኝ ከእኔ ተሠወረ።

ከተሠወረ በኋላ ለእኔም ሆነ ለጐረቤቶቼ ነገሩ እውነት አልመሰለም ባለ 50 ባለ 25 ባለ 10 ሳንቲም ገንዘብ በእግሬ ሥር እየጣሉ ይኽ ምንድር ነው? እያሉ ፈተኑኝ ሁሉንም ነገርኳቸው ይህን ሲያረጋግጡ ደስታው ልዩ ሆነ።

እግዚአብሔር ይመስገን የቅ/ሚካኤል ተረዳኢነት አማላጅነት በሁሉም ሰዎች ዘንድ ለዘለዓለም ይኑር” ማለታቸውን የሀ/ስብከቱ ጽ/ቤት በወቅቱ ገልጿል።

ከዚህም ሌላ ከባድ ነፋስ የተቀላቀለ ኃይለኛ ዝናብ ጥሎ በከተማ ውስጥ የሚገኙ ታላላቅ ሕንፃዎች ተሰነጣጠቁ፥ በላያቸው የነበረው የጣራ ቆርቆሮ የነፋሱ ኃይል ተገነጣጠሎ ሲወስድ ቀደም ሲል ከቤተ መቅደሱ ላይ ተወስዶ የነበረውና ግለሰቦች በራስ ወዳድነት ይጠቀሙበት የነበረው ቆርቆሮ በዚሁ ከባድ ነፋስ ተጭኖ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ በመምጣት በቅጽረ ግቢው ውስጥ ተቀመጠ፤ የተወሰደው ቆርቆሮ ተመልሶ በቅጽረ ቤተ ክርስቲያኑ በመገኘቱ ቅ/ሚካኤል የሠራውን ገቢረ ተአምር ሕዝበ ክርስቲያኑ በአድናቆት ተመልክቶታል።

___________________________________________

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: