ምስሉ ላይ እንደሚታየው፡ በመስከረም ፩ በኒው ዮርክ ከተማ የፈረሱት መንትያ–ህንጻዎች፡ በሳዑዲዋ መካ የሚገኘውን መስጊድ ተመስለው ነበር እንዲሠሩ የተደረጉት። ይገርማል፡ ታዲያ አክራሪ እስላሞቹ አውሮፕላን አብራሪዎች መስጊዳቸውን የሚመስሉትን ህንጻዎች ለምን አፈረሱ? የኒው ዮርክ ከተማ መንትያ–ህንጻዎች፡ በሌላ ቀን ሳይሆን፡ በአገራችን አዲስ ዓመት፡ መስከረም ፩ ቀን ነው በአውሮፕላን ለመመታት የበቁት። ይህም አጋጣሚ አይደለም። ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያውያን ሯጮች በተሳተፉበት የቦስተን ማራቶን የዓለምን ትኩረት እንዲስብ የተደረገው የሽብር ጥቃትም እንደዚሁ በምክኒያት ነበር።
በሁለቱ ጽንፈኛ ድርጊቶች ላይ ከፍተኛ ሚና የተጫወተችው ሳዑዲ አረቢያ መሆኗን የዓለም ማሕበረሰብ አሁን የደረሰበት ይመስላል። ኒው ዮርክን በአውሮፕላን ያጠቁት 15 ግለሰቦች የሳዑዲ ዜግነት ያላቸው ነበሩ። አሁን እንደምንሰማው ደግሞ የሳዑዲ ንጉ‘ሳ‘ውያን ቤተሰቦች የፕሬዚደንት ኦባማን ስቲፔንዲ/ስኮላርሺፕ በሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ከፍለዋል። ምናልባትም ኦባማን ሥልጣን ላይ እንዲወጡ አድርገዋቸዋል የሚባሉት ሳዑዲዎች፡ የመስከረም ፩ን ጥቃት ከጅምሩ እስከ ዒላማው ድረስ አዘጋጅተወታል፡ አቀነባብረውታል። ለዚህም ከ ‘ቅል እና አጥንቶች“/ስካል & ቦንስ/ የ ጆርጅ ቡሽ ቤተሰቦች የቅርብ እርዳታ አግኝተዋል ይባላል። ይህን በተመለከተ፡ አንዳንድ የአሜሪካ ሴነተሮች አሁን ድምጾቻቸውን በማሰማት ላይ ናቸው። በጣም የሚገርመው፡ በቡሽና ኦባማ መስተዳደር ቁልፍ ሥልጣን የነበራቸው እንደ ‘ዌስሊ ክላርክ‘ እና ‘ሮበርት ጌትስ‘ የመሳሰሉት ፖለቲከኞች የ‘ከዳተኛነት‘ መንፈስ በተሞላበት መልክ ፕሬዚደንቶቻቸውን ሲወቅሱ አሁን መሰማታቸው ነው።
የሳዑዲ ንጉሳውያን እንዲሁም የቢላንድን ቤተሰቦች በአሜሪካ ላይ ጥቃት በተካሄደበት የ መስከረም ፩ ማግስት አሜሪካን ያለምንም ችግር ለቀው እንዲወጡ ፈቃድ ማግኘታቸው (ለሌላው በረራ በተከለከለበት ወቅት) እንዲሁም በቦስተን ማራቶን ላይ ጥቃት እንዳደረሱ የሚጠረጠሩት የሳዑዲ ዜጎች ወዳገራቸው በቀላሉ እንዲመለሱ መደረጋቸው፤ ሳዑዲ የመስከረም ፩ን ጥቃት በሚመለከት የምታውቀው ከባድ ምስጢር መኖሩን ነው የሚያሳየን።
ታዲያ ሳዑዲ ይህንን ምስጢር እንደማስፈራሪያ አድርጋ በመጠቀም ሰይጣናዊውን የዋሃቢ እስልምና አጀንዳ በመላው ዓለም በግልጽ በማራመድ ላይ ትገኛለች።
ሳዑዲዎች ከሁለት ዓመታት በፊት ‘ግራውንድ ዜሮ‘ ተብሎ በተሰየመውና መንትዮቹ የኒው ዮርክ ህንጻዎች በፈራረሱበት ቦታ ላይ የ300 ሚሊየን ዶላር መስጊድ ለመስራት ከ ከንቲባ ብሉምበርግ ፈቃድ አግኝተው ለከፍተኛ ውዝግብ መብቃታቸውና ዕቅዳቸውም እንድተጨናገፈባቸው የሚታወስ ነው።
የነፃነት ግንብ
አሁን በመንትዮቹ ህንፃዎች ምትክ ‘የአንድ ዓለም ገበያ ማዕከል ህንጻ‘ ተብሎ የተሰየመው ሰማይ ጠቀስ ፎቅ ተሠርቷል። በዚህም የኒዮርክ አንጋፋ ህንፃ ጫፍ ላይ የ መስጊድ ሚናሬት ቅርጽ ያለው የአንቴና ብረት ተሰክቷል። ፕሬዚደንት ቡሽ ከሥልጣን ወርደው ጣጣቸውን ሁሉ ለአፍሪቃ–አሜሪካዊው ኦባማ እንዳስረከቡት ሁሉ ከንቲባ ብሉምበርግም የመስጊድ ሚናሬት የተሰካበትን ህንፃ ከአፍሪቃዊ አሜሪካዊት ጋር በትዳር ለሚኖሩት አዲሱ ከንቲባ አስረክበው ሄደዋል። ይህ ሚናሬት በሳዑዲዎች ተጽዕኖ የተሠራ ሊሆን ይችላል። ሰሞኑን ደግሞ ከዚህ አንቴና የሚፈነጥቅ አስገራሚ ድምጽ እየተሰማ ነው። የቪዲዮው መጨረሻ ላይ በጥሞና ካዳመጥን ‘አልላህ” የሚል ተርገብጋቢ ድምጽ ሲያፏጭ እንሰማለን። በዝቅተኛ ሞገድ እስላማዊ ድምጾችን እንደ ጮራ በማፈንጠቅ አእምሮ ውስጥ ለመትከል የተራቀቀ መንገድ ያገኙ ይመስላል። እኛ አገር እንደሚታየው በአሜሪካና አውሮፓ የሚገኙ መስጊዶች መውዚኖች የሚለፍፉባቸው ሚናሬቶች እንዲኖሯቸው አይፈቀድም። ይህ ሊገርመን/ሊያስደነግጠን ይችላል፡ ሆኖም፡ እነዚህ ሚናሬቶች የሚሠሩት አደንዛዥ የሆነውን “የአላህ ወአክበር!” ድምጽ ለማፈንጠቅ ነው። ይህ ልዩ ውዝዋዜ ያለው ድምጽ የታችኛውን የአንጎላችንን ክፍል፡ በተለይ በምንተኛበት ወቅት፡ ለመፈታተን/ለማደንዘዝ ይበቃል። ለዚህ ሕሊና–አጣቢ ተግባር በተለይ ህፃናት እና ሴቶች ናቸው በይበልጥ የሚጋለጡት።
ይህን ድብቅ የሆነ አጋንንታዊ የጣልቃ–ገብነት ተግባር (Subliminal message) ቸል ሳንል አስፈላጊ በሆነ የመንፈሳዊ ጋሻ ልንመክት ይገባናል። ለምሳሌ፡ አረብ አገር ጥቂት ዓመታት ቆይተው የሚመጡ ‘ክርስቲያን‘ ወገኖች፡ ልክ እንደ አረቡ፡ “አላህ” ወይም “ምሽ አላህ” የሚሉትን ክርስቲያናዊ ያልሆኑ ቃላቶች ሲጠቀሙ ይሰማሉ፤ ክርስቲያናዊ ስነምግባራቸውን / አለባበሳቸውን በቀላሉ እንዲተውና እንዲረሱ ሲደረጉ ይታያሉ። በሌላ በኩል ግን ሁልጊዜ ኑሯቸውን በኢትዮጵያ የሚገፉትና ኢትዮጵያኛ ቋንቋዎችን እንደ መጀመሪያ ቋንቋዎቻቸው አድርገው የሚናገሩት ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ወገኖች፡ “እግዚአብሔር / አምላክ ይስጥልኝ!” “ክርስቶስ / አምላክ ያውቃል!” ብለው በፍጹም አይናገሩም። የአረቡን እንጂ ኢትዮጵያኛውን የአገራችንን አገር ልብስ ሲለብሱም አይታዩም። እነዚህ አስገራሚ ክስተቶች የሚያሳዩን፡ አረብ ሙስሊሞች ከላይ የተጠቀሱትን እስላማዊ ቃላቶች ደግመው ደጋግመው በመናገር የወገኖቻችንን ሕሊና እንደሚያጥቡ፡ እንዲሁም እስልምና፡ የአረብ ኢምፔሪያሊዝም እንደ መሳሪያ የሚገለገልበት አደገኛ ርዕዮት ዓለም መሆኑን ነው። በአሁኗ ኢትዮጵያችን በአንዳንድ ቦታዎች ለተከሰተው አሳዛኝ የስነምግባራዊ ቀውስ፡ ከላሸቀው የምዕራባውያኑ ማሕበረሰባዊና ባህላዊ ኢምፔሪያሊዝም ጎን ኋላ ቀሩ የአረብ ሙስሊም ኢምፔሪያሊዝም ዓይነተኛ ሚና ይጫወታል። ፍቅር– ፡ ትህትና– ፡ ተድላ– አልባነት፣ ቁጡነት፣ ተሳዳቢነት፣ ቅናት፣ ምቀኝነት፡ የበታችነት ስሜት ወዘተ ከእስማኤልና ዔሳው ልጆች የተወረሱ ናቸው። ከአህያ ጋር የዋለ….ይባል የለ!
ህንፃ ግንባታ
ተዋሕዶ ክርስቲያኖች ቤተ መቅደሶቻቸውን ለመሥራት ቦታ ሲመርጡ መለኮታዊ በሆነ የቦታ መሪነትና አስተባባሪነት እንደመሆኑ ሁሉ (ክርስቶስ በቀራንዮ) ፡ ኮራጁ ፀረ–ክርስቶሱም ምክራቦቹን ወይም የአምልኮ ቦታዎቹን የሚሠራው በ መካው ጥቁር ድንጋይ ጠቋሚነት አማካኝነት ነው።
እንደምሳሌ የምነወስደው፡ ኢየሩሳሌምን ነው፦
እ.አ.አ በ637 ዓ.ም. እስላሞች በዑመር መሪነት ኢየሩሳሌምን ወረሩ፤ ለቀጣይ አራት መቶ ዓመታት ያህል ኢየሩሳሌም የእስላሞች ከተማ ሆነች። በዚህ ጊዜ የንጉሥ ሰሎሞን ቤተ–መቅደስ ታንጾበት የነበረው የሞሪያ ‘ተራራ‘ በእስላሞች ዘንድ ነቢያቸው ከዚህ ቦታ በመነሣት በመላእክት አማካይነት ታዋቂ የሌሊት ግዟቸውን አድርገዋል ተብሎ ስለሚታመንና ቦታውም በኢየሩሳሌም ከተማ የሚገኝ ነው በማለት ኢየሩሳሌምን ቅዱስዋ ከተማ “አል ቅዱስ” ብለው ሰየሟት። በቅዱስዋ ከተማ በሚገኘው በሞሪያ ተራራ ላይም በ691 ዓ.ም “የዑመር ከሊፋ” ወይም “የድንጋዩ ጉልላት” (Dome of the Rock) የተባለውን መስጊድ፣ በ703 ዓ.ም ደግሞ “አል አቅሳ” የተባለውን መስጊድ አነጹ”
እነዚህ መስጊዶች ፀረ–ክርስቶሱ ያሠራቸው መስጊዶች መሆናቸውን ለማወቅ፡ እስልምና በክርስቲያኖች ላይ ላለፉት 1400 ዓመታት ሲያካሂድ የነበረውን ዘግናኝ የግድያ ታሪክ ጠልቆ ማጥናት አያስፈልግም፤ መካ በሚገኘው ጥቁር ድንጋይ እና በእየሩሳሌም ሞሪያ ተራራ በታነጸው በዚህ የ “ድንጋዩ ጉልላት” መካከል የ666.6 ማይሎች የአየር ርቀት መኖሩን በማወቅ ብቻ በቂ ማስረጃ ልናገኝ እንችላለን። ይህን አፍ የሚያስከፍት መረጃ ጉጉል ማፕ በማድረግ ማንም ሊያየው ይችላል።
የባቢሎንን ሰማይ ጠቀስ ግንብ ታሪክ እናስታውሳለን፤ ታዲያ አሁንም ፀረ–ክርስቶሱ እንደቀድሞው ሰማይጠቀስ ፎቆችን መገንባት ይወዳል፤ እነዚህ ፎቆች ከማንም/ከምንም የበለጡ፡ ከፍ ብለው የሚታዩ እና የሰዎችን አትኩሮት የሚስቡ እንዲሆኑ ተደርገው ይሠራሉ። መንትዮቹ የኒው ዮርክ ሕንፃዎች ከመፍረሳቸው በፊት ችቦ ከያዘችው የፈረንሳይ ስጦታ: ከ “ነፃነት ኃውልት” ቀጥሎ የኒውዮርክ ከተማ ዋንኛዎቹ መለያዎች ስለነበሩ የብዙ ጎብኝዎችን አትኩሮት ሲስቡ ነበር። በሚፈርሱበት ወቅት ደግሞ ዓለም እስከምትቀየር ድረስ የመላው ዓለምን አትኩሮት ለመሳብ በቅተዋል። አሁን ደግሞ በአሜሪካ ረጅሙ የሆነው ሰማይ ጠቀስ ፎቅ (104 ፎቆች) “የነፃነት ግንብ” ወይም “የአንድ ዓለም የገበያ ማዕከል” ገና ከመከፈቱ የዓለማችንን ነዋሪ ቀልብ በመግፈፍ ላይ ይገኛል። ይህ ፎቅ ከእነ አንቴናው 1776 ጫማ ከፍታ አለው። የአገረ አሜሪካ ነፃነት የታወጀውም እንዲሁ በ1776 ዓ.ም. ነበር። ቪዲዮውን እንመልከት:-
ክርስቶስ ሲመጣ የአንድ ዓለም መንግሥት ይመሠርታል። ፀረ–ክርስቶሱ ደግሞ ኢ–አማንያኑና እስላሞቹን በማስተባበር የራሱን የአንድ–ዓለም መስተዳደር ሊመሠረት ይሞክራል። ለዚህም ይመስላል ሳዑዲዎች በምዕራባውያኑ ደጋፊነት ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመጠቀም ረጃጅም ሕንጻዎች ላይ አንቴናዎችን በመትከል አጋንንታዊ መልዕክቶቻቸውን በማንቀላፋት ላይ በሚገኘው ነዋሪ አንጐል ውስጥ ለመቅረጽ የሚከጅሉት።
ከጥቂት ዓመታት በፊት በዓለም ረጅም ነው ተብሎ የሚታወቀው ህንጻ በማሌዢያ ዋና ከተማ በኩዋላ ላምፑር የሚገኙት መንትያ ህንጻዎች ነበሩ። አሁን የዓለም ከፍተኛ ሰማይ–ጠቀስ ፎቅ በዱባይ ይገኛል። ይህን ህንፃ መጀመሪያ ላይ “ቡርጅ ዱባይ” አሉት በጥቂት ቀናት ውስጥ “ቡርጅ ከሊፋ” ወደሚለው መጠርያው ተቀየረ። ይህም ያለምክኒያት አይደለም። አዲስ አበባም “ከሊፋ ህንጻ” የሚባል ፎቅ አለ፡ ካልተሳሳትኩም፡ የዳቦ ዱቄቱንም በፀረ–ክርስቶሱ ቅመም በመበከል ላይ ያለ የዳቦ ዱቄት አምራች ድርጅት ወደ አገራችን መግባቱን ሰምቻለሁ። ሌላ ጊዜ እመለስበታለሁ…
የሚቀጥሉት የዓለም ከፍተኛ ሰማይ–ጠቀስ ፎቆች፡ መጀመሪያ፡ ከኢትዮጵያ ፊት ለፊት በምትገኘዋ በሳዑዲዋ ጂዳ ከተማ (መካ አጠገብ) ቀጥሎም ከአረሜኒያ አጠገብ በምትገኘዋ የ ባኩ ከተማ (አዘርበጃን) እንደሚሠሩ እየተነገረ ነው። አርመኒያ ምናልባት ከኢትዮጵያ ቀጥላ ሁለተኛዋ ክርስቲያናዊ አገር ናት። በአርሜኒያ የነዳጅ ዘይት የለም፡ አዘርበጃን ግን አለ፤ ኢትዮጵያ ዘይት አላወጣችም፡ ሳዑዲ አረቢያ ግን ትዋኝበታለች። አርሜኒያ እንደ ኢትዮጵያ ተራራማ የሆነች አገር ነች (ቱርክ የወሰደችባቸው የአራራት ተራራ የአርመኖች ነው)። ከተፈጥሯዊ ተራሮች ረዘም ብሎ ለመታየት ፉክክር…
በአዲስ አበባችን ዛሬ ከፍተኛ ነው የሚባለው ህንጻ መስቀል አደባባይ እና ቤተ–መንግሥት አጠገብ የሚገኘው የሸህ አላሙዲን ህንጻ ነው። ህንጻው እዚያ ቦታ ላይ ያለምክኒያት አልተሠራም። ለዚህም ይመስላል፡ ይህ “ጎንደሬ” የሚል ቅጽል ስም የተሰጠው ህንጻ ባዶ እንዲሆን የተደረገው። በስተጀርባው ያሉት የህንጻው መስኮቶች (ወደ ጊዮን ሆቴልና ቤተመንግሥት አቅጣጫ) ከላይ እስከታች በዕብነበረድ ግጥም ተደርገው ተዘግተዋል። አንቴናው ላይ ወይም ግንቡ ውስጥ ምን ዓይነት የኮሙኒኬሽን መሣሪያ እንዳለ እግዚአብሔር ነው የሚያውቀው። በነገራችን ላይ፡ ወደ ሜክሲኮ የሚገኘውም የጸጥታ አማራር (ፖሊስ) ዋናው መሥሪያ ቤት ህንጻም “ጎንደሬ” የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል። ይህም ዘመናዊ ህንጻ በሽህ አላሙዲን ተቋም ነው የተሠራው። በሌላ በኩል፡ በሁለቱ ቤተመንግሥታት መካከል፡ ፍልውሃ “ጸበል” ጎን የሚገኘው ሸረተን ሆቴል፡ እዚያ ቦታ ላይ የተሠራው መሬት ውስጥ ሁለት ቅዱስ–ታቦታት እንደሚገኙ (ከግራኝ መሀመድ ወረራ የተደበቁ) ስለሚታወቅ ነው የሚል ከባድ ወቀሳ ከተለያዩ ግለሰቦች ሰምቼ ነበር። ይህን ምናልባት በቅርቡ እናውቅ ይሆናል። በሌላ በኩል፡ ሸሁ በአዲስ አበባ ከፍተኛ በሆኑት ኮረብታዎች ላይ ህንጻዎችን ለመሥራት ይታገላሉ። አሁን የጻድቁ አብርሃም ቤተክርስቲያን በሚገኝበት በጣም ማራኪ ኮረብታ ላይ የመዝናኛ ፓርክ ነገር ለመሥራት ዕቅድ ነበራቸው ግን ሃሳባቸው ከሽፎባቸዋል። ፒያሳ፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ፊት ለፊትም እንደዚሁ አንጋፋ የሆነ ፎቅ ለመሥራት ይመኛሉ። በቻይናዎች ይሠራል የተባለውና በአፍሪቃ ከፍተኛ የሚሆነው ሰማይ–ጠቀስ ፎቅንም ለመሥራት ታቅዷል። ይህ ፎቅ እንዲያውም አዲስ አበባ ከምትገኝበት የ2.500 ሜትር ከፍታ ጋር ሲታከል በዓለም ከፍተኛው ሰው–ሠራሽ ነገር (የሆቴል መኝታ፣ ቢሮ…) ነው የሚሆነው። ሲያልቅ የሳዑዲዎቹ ፀረ–ክርስቶሳዊ አንቴና ይሰካበት ይሆን? ይህ ሁሉ ከፍ ከፍ ማለት ቅዱሶቹን የእንጦጦ ተራራዎች ለመብለጥ ይሆን? የፎቅ ጠላት መሆኔ ሳይሆን፡ ፎቆቹ እንደ ዱባዩ ወይም ኒው ዮርኩ “የተሻለ/የበለጠ” እንሠራለን በሚል ትዕቢታዊ መንፈሥ የሚሠሩ ናቸውን? ዓላማቸውስ ምን ይሆን? ለሚሉት ጥያቄዎች መልሶችን ለመፈለግ ያህል ነው።
በጃፓን–አሜሪካዊው፡ በ ‘ሚኖሩ ያማሳኪ‘ የተሠሩት መንትዮቹ የኒው ዮርክ ግንቦች ንጉሥ ሰሎሞን አሠርቷቸው ከንበረው የ “ያቁም እና በለዝ አዕማድ” ጋር በስፋት ተመጣጣኝነት እንደነበራቸው ይነገራል። የእነዚህን የንጉሥ ሰሎሞን ግንቦች ምስል ነፃ–ግንበኞች (ፍሪሜሰንስ) በምልክትነት ይጠቀሙባቸዋል። ይህ ጃፓናዊ ኢንጂነር ብዙ ፕሮጀክቶችን በሳዑዲ አረቢያ ሠርቷል።
መንትያ የሆኑ ህንፃዎች ምናልባት የአንጎላችንን ሁለት ክፍሎች መስለው እንዲሠሩ ተደርገው ሊሆን ይችላል። ግራው የወንድ፣ ቀኙ የሴት። ታዲያ ሥርዓት ይዞ በመካሄድ ላይ ያለው ጥቃት ሴትኛ በሆነው የቀኙ የአንጎላችን ክፍል ላይ መሆኑ ነውን?
“አዕማዱንም በመቅደሱ ወለል አጠገብ አቆማቸው፤ የቀኙንም ዓምድ አቁሞ ያቁም ብሎ ጠራው፤ የግራውንም ዓምድ አቁሞ በለዝ ብሎ ጠራው።” [መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ 7፥21]