Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘SpiritualWarfare’

አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ ፥ አድነን ፣ ከአሕዛብ መካከል ሰብስበን

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 20, 2020

❖❖❖ መዝሙረ ዳዊት ከ ምዕራፍ ፻፩ እስከ ምዕራፍ ፻፭ ❖❖❖

[መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፻፭]

፩ ሃሌ ሉያ፤ ቸር ነውና፥ ምህረቱም ለዘላለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ።

፪ የእግዚአብሔርን ኃይል ሥራ ማን ይናገራል? ምስጋናውንስ ሁሉ ማን ያሰማል?

፫ ፍርድን የሚጠብቁ፥ ጽድቅንም ሁልጊዜ የሚያደርጉ ምስጉኖች ናቸው።

፬ አቤቱ፥ በሕዝብህ ሞገስ አስበን፥ በመድኃኒትህም ጐብኘን፤

፭ የመረጥሃቸውን በጎነት እናይ ዘንድ፥ በሕዝብህም ደስታ ደስ ይለን ዘንድ፥ ከርስትህም ጋር እንጓደድ ዘንድ።

፮ ከአባቶቻችን ጋር ኃጢአትን ሠራን፥ ዐመፅንም፥ በደልንም።

፯ አባቶቻችን በግብጽ ሳሉ ተኣምራትህን አላስተዋሉም፥ የምሕረትህንም ብዛት አላሰቡም፤ በኤርትራ ባሕር ባለፉ ጊዜ ዐመፁብህ።

፰ ኃይሉን ግን ለማስታወቅ። ስለ ስሙ አዳናቸው።

፱ የኤርትራንም ባሕር ገሠጸ እርሱም ደረቀ፤ እንደ ምድረ በዳ በጥልቅ መራቸው።

፲ ከሚጠሉአቸውም እጅ አዳናቸው፥ ከጠላትም እጅ ተቤዣቸው።

፲፩ ያሳደዱአቸውንም ውኃ ደፈናቸው፥ ከእነርሱም አንድ አልቀረም።

፲፪ በዚያን ጊዜ በቃሉ አመኑ፥ ምስጋናውንም ዘመሩ።

፲፫ ፈጥነውም ሥራውን ረሱ፥ በምክሩም አልታገሡም።

፲፬ በምድረ በዳም ምኞትን ተመኙ፥ በበረሃም እግዚአብሔርን ተፈታተኑት።

፲፭ የለመኑትንም ሰጣቸው፤ ለነፍሳቸው ግን ክሳትን ላከ።

፲፮ ሙሴንም እግዚአብሔር የቀደሰውንም አሮንን በሰፈር ተመቀኙአቸው።

፲፯ ምድርም ተከፈተች ዳታንንም ዋጠችው፥ የአቤሮንንም ወገን ደፈነች፤

፲፰ በማኅበራቸውም እሳት ነደደች፥ ነበልባልም ኅጥኣንን አቃጠላቸው።

፲፱ በኮሬብም ጥጃን ሠሩ፥ ቀልጦ ለተሠራ ምስልም ሰገዱ።

፳ ሣርም በሚበላ በበሬ ምሳሌ ክብራቸውን ለወጡ።

፳፩-፳፪ ታላቅ ነገርንም በግብጽ፥ ድንቅንም በካራን ምድር፥ ግሩም ነገርንም በኤርትራ ባሕር ያደረገውን ያዳናቸውንም እግዚአብሔርን ረሱ።

፳፫ እንዳያጠፋቸው ቍጣውን ይመልስ ዘንድ የተመረጠው ሙሴ በመቅሠፍት ጊዜ በፊቱ ባይቆም ኖሮ፥ ያጠፋቸው ዘንድ ተናገረ።

፳፬ የተወደደችውን ምድር ናቁ፥ በቃሉም አልታመኑም፥

፳፭ በድንኳኖቻቸውም ውስጥ አንጐራጐሩ፤ የእግዚአብሔርን ቃል አልሰሙም።

፳፮-፳፯ በምድረ በዳም ይጥላቸው ዘንድ፥ ዘራቸውንም በአሕዛብ መካከል ይጥል ዘንድ፥ በየአገሩም ይበትናቸው ዘንድ፥ እጁን አነሣባቸው።

፳፰ በብዔል ፌጎርም ተባበሩበት፥ የሙታንንም መሥዋዕት በሉ።

፳፱ በሥራቸውም አስመረሩት፥ ቸነፈርም በላያቸው በዛ።

፴ ፊንሐስም ተነሥቶ ፈረደባቸው፥ ቸነፈሩም ተወ፤

፴፩ ያም እስከ ዘላለም ለልጅ ልጅ ጽድቅ ሆኖ ተቈጠረለት።

፴፪-፴፫ በክርክር ውኃ ዘንድም አስቈጡት፥ መንፈሱን አስመርረዋታልና፤ ስለ እነርሱም ሙሴ ተበሳጨ፤ በከንፈሮቹም በስንፍና ተናገረ።

፴፬ እግዚአብሔርም እንዳላቸው አሕዛብን አላጠፉም፤

፴፭ ከአሕዛብም ጋር ተደባለቁ፥ ሥራቸውንም ተማሩ።

፴፮ ለጣዖቶቻቸውም ተገዙ፥ ወጥመድም ሆኑባቸው።

፴፯ ወንዶች ልጆቻቸውንና ሴቶች ልጆቻቸውን ለአጋንንት ሠው፤

፴፰ የወንዶች ልጆቻቸውንና የሴቶች ልጆቻቸን ደም፥ ለከነዓን ጣዖቶች የሠውአቸውን ንጹሕ ደም አፈሰሱ፥ ምድርም በደም ረከሰች።

፴፱ በሥራቸው ረከሱ፥ በማድረጋቸውም አመነዘሩ።

፵ የእግዚአብሔርም ቍጣ በሕዝቡ ላይ ነደደ፥ ርስቱንም ተጸየፈ።

፵፩ ወደ አሕዛብም እጅ አሳለፋቸው፥ የሚጠሉአቸውም ገዙአቸው።

፵፪ ጠላቶቻቸውም ግፍ አደረጉባቸው፥ ከእጃቸውም በታች ተዋረዱ።

፵፫ ብዙ ጊዜ አዳናቸው፤ ነገር ግን በምክራቸው አስመረሩት፥ በኃጢአታቸውም ተዋረዱ።

፵፬ እርሱ ግን ጩኸታቸውን በሰማ ጊዜ ጭንቃቸውን ተመለከተ፤

፵፭ ለእነርሱም ኪዳኑን አሰበ፥ እንደ ምሕረቱም ብዛት ተጸጸተ።

፵፮ በማረኩአቸውም ሁሉ ፊት ሞገስን ሰጣቸው።

፵፯ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ፥ አድነን፤ ቅዱስ ስምህን እናመሰግን ዘንድ፥ በምስጋናህም እንመካ ዘንድ፥ ከአሕዛብ መካከል ሰብስበን።

፵፰ ከዘላለም እስከ ዘላለም የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ይባረክ ሕዝብም ሁሉ አሜን ይበል። ሃሌ ሉያ።

________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: