Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘Paraclete’

የጰራቅሊጦስ ዕለት የጽዮን ቀለማትና እርግቦች ተዓምር | Miracle of The Colors of Zion + Doves on The Day of Paraclete

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 4, 2023

🌞 የንጋት ጸሐይዋ ብሩህ ሆና ትታያለች፤ ከቤተ ክርስቲያን ከወጣሁ በኋላ ወንበር ላይ ሆኜ ፀሐይዋን እየሞቅኩ ጸሎት ሳደርግ ርጥበት ወይንም እንባ የያዘው አይኔ በግማሽ ተከፍቶ ወደ ፀሐያዋ ሲያተኩር ብሩህ የሆኑት የማርያም መቀነት ቀለማት ዓይኔ ውስጥ ያንጸባርቁ ነበር። ድንቅ ነው! በጸሎት ጊዜ በተደጋጋሚ ይከሰታል። መሞከር የሚሻ ቢሞክረው ጥሩ ነው።

  • የጽዮን (ኢትዮጵያ) ቀለማት / የማርያም መቀነት
  • የማርያም መቀነት ወርደሽ ንገሪያቸው
  • ወራሪና ባንዶች ካለ ባህሪያቸው
  • አይቶ ለመረዳት የታወሩ ናቸው
  • የኢትዮጵያ ሰንደቅ እኔ ነኝ በያቸው
  • በሠማዩ ላይ ሲታይ ቀለም
  • የሷ ነው እንጂ ሌላ አይደለም

______________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የጰራቅሊጦስ ድንቅ ተዓምር፤ ሰክሬአለሁ፤ ቃላት የለኝም!

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 11, 2022

😇 አዎ! ጰራቅሊጦስ ሐዋርያትን የወይን ጠጅ ሳይጠጡ እንዳሰከራቸውና በሀገሩ ሁሉ እንዳናገራቸው እኔም በእነዚህ ቀናት የሰከርኩ መስሎ ነው የተሰማኝ፤ ክርስቶስንና ቤተሰቦቹን በተመለከት ከብዙዎች ጋር በመነጋገር ላይ ነኝ፤ ሰው ሁሉ በበጎ እየቀረበኝ ነው። በእውነት ድንቅ ነው! በእውነት ጰራቅሊጦስ የሃይማኖትን አልጫነት የሚያጣፍጥ የልቡና ጨው ነው። ጰራቅሊጦስ በጭለማ ላሉ የሚያበራ የይቅርታ ብርሃን ነው።

  • ወደ ጸሎት ቤት ስገባ
  • ጸሎት ቤት ውስጥ

😇 ቅድስት እናታችንና ልጇ እግዚአብሔር ወልድ + የማርያም መቀነት + ክቡር መስቀል

ከጸሎት ቤት ስወጣ፤ ማረፊያ ወንበሩ ላይ፤ ይህን አየሁት። የሕፃን ልጅ መጫወቻ ነው፤

እንጠንቀቅ! ቀስተ ደመና የሰዶማውያን አይደለም! “ኬኛ!” ብለው ሊነጥቁን ግን ይሻሉ!

  • ከጸሎት ቤት ልክ ስወጣ ሜዳው ላይ ሰባት እርግቦችን አገኘሁ
  • ማታ ላይ ቤቴ እንደገባሁ መብራቱ ይህን ሠርቶ ነበር።
  • ጠዋት ላይ ደግሞ የእመቤታችን ሥዕል የማርያም መቀነትን ቤቴ ግርግዳ ላይ አንጸባርቆ ይታይ ነበር፤ ድንቅ ነው!

❖❖❖ እምዕርገት እስከ ጰራቅሊጦስ መዝሙር “በሰንበት ዐርገ ሐመረ” ❖❖❖

(በ፫/) በሰንበት ዐርገ ሐመረ ገሠፀ ባሕረ፤ ወገሠፆሙ ለነፋሳት፤ ወይቤሎሙ ኢትናፍቁ ወኢይምጻእ ኑፋቄ ውስተ ልብክሙ፤ በከመ ፈነወኒ አቡየ አነኒ እፌንወክሙ ውስተ ቤተ አቡየ ብዙኅ ማኅደር ቦቱ፤ ካዕበ እመጽእ ወእነሥአክሙ፤ ከመ ተሀልዉ ምስሌየ በመንግሥተ አቡየ ዘበሰማያት።

አመላለሰ

ከመ ተሀልዉ ምስሌየ በመንግሥተ አቡየ፤

በመንግሥተ አቡየ ዘበሰማያት።

ዓራራት

ትንሣኤሁ ገብረ በሰንበት ወሰበረ ኆኃተ ብርት እግዚአ ለሰንበት አመ ሣልስት ዕለት ምዖ ለሞት ወዓርገ ውስተ ሰማያት።

ሰላም

ወልድ እኁየ ውእቱ ፍቁርየ ውእቱ ተንሥአ እሙታን ገብረ ሰላመ ለኵሉ ዓለም ዓርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት ሎቱ ስብሐት ለዘቀደሳ ለሰንበት።

ዘቅዳሴ ምንባባት

  • ሮሜ ፲፥፩ ፡ ፍ፤
  • ፩ጴጥ ፫፥፲፭ ፡ ፍ፤
  • ግብ ፩፥፩ ፡ ፍ፤

ዘቅዳሴ ምስባክ፦

  • ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ፤
  • ወእግዚእነ በቃለ ቀርን፤
  • ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ። መዝ ፵፮፥፭

ወንጌል፦ ሉቃ ፳፬፥፵፭ ፡ፍ

ቅዳሴ ዘዲዮስቆሮስ (እምቅድመ ዓለም)

❖❖❖ /7 እርግቦች ❖❖❖

  • ሐዋሪያት ተባበሩ
  • በአዲስ ቋንቋ እየተናገሩ
  • ቃሉን አስተማሩ

❖ ፯ / ሰባት ፍጹም ቁጥር ነው

በቅዱስ መጽሐፍ አቆጣጠር ሰባት (፯) ፍጹምና ሙሉ ቁጥር በመሆኑ ከአንድ እስከ ሰባት ( ፩–፯ ) የተዘረዘሩት ምስጢራተ ቤተክርስቲያንም እንከንና ጉድለት የሌለባቸው ፍጹማን ናቸው።
ሰባት ቁጥር በመጽሐፍ ቅዱስ ሥርዓት ፍጹም ለመሆን ለማወቅ ከዚህ የሚከተሉትን ማስረጃዎች እንመልከት፦

❖ ሰባት ቁጥር ምስጢራት በቤተክርስቲያን፤

በመጽሐፍ ቅዱስና በስርዓተ ቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ ስባት ቁጥር ብዙ ምሳሌ እንዳለው ይታወቃል፡፡ በዕብራዊያን ዘንድም ሰባት ፍጹም ቁጥር ነው፡፡ ምሳሌ ፳፬፡፲፮ እግዚአብሔር ከሰኞ
እስከ እሑድ ያሉትን ቀናት በሰባት ቁጥሮች ወስኗል ሕዝበ እስራኤል ከግብጽ ባርነት ወጥተው በሲና በርሀ ሲጓዙ ይመሩት የነበሩት በ፯/7 ደመና እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ዘዳ ፲፫፡፳፩

ከዚህ ቀጥለንም ለቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ የ፯ ቁጥር ምስጢራትን ምሉዕነትን የሚያስረዱ ልዩ ልዩ ማስረጃዎችን በዝርዝር እንመለከታለን፦

❖ ሀ/ ሰባቱ አባቶች

፩. ሰማያዊ አባታችን እግዚአብሔር
፪. የነፍስ አባት
፫. ወላጅ አባት
፬. የክርስትና አባት
፭. የጡት አባት
፮. የቆብ አባት
፯. የቀለም አባት

❖ ለ/ ሰባቱ ዲያቆናት

፩. ቅዱስ እስጢፋኖስ
፪. ቅዱስ ፊልጶስ
፫. ቅዱስ ጵሮክሮስ
፬. ቅዱስ ጢሞና
፭. ቅዱስ ኒቃሮና
፮. ቅዱስ ጳርሜና
፯. ቅዱስ ኒቆላዎስ

❖ ሐ/ ሰባት የጌታ ቃላት /እኔ ነኝ

፩. የሕይወት እንጅራ እኔ ነኝ
፪. የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ
፫. እኔ የበጎች በር ነኝ
፬. መልካም እረኛ እኔ ነኝ
፭. ትነሣዔና ሕይወት እኔ ነኝ
፮. እኔ መንገድና ሕይወት ነኝ
፯. እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ

❖ መ/ ሰባቱ ሰማያት

፩. ጽርሐ አርያም
፪. መንበረ መንግሥት
፫. ሰማይ ውዱድ
፬. ኢየሩሳሌም ሰማያዊት
፭. ኢዮር
፮. ራማ
፯. ኤረር

❖ ሠ/ ሰባቱ ሊቃነ መላእክት

፩. ቅዱስ ሚካኤል
፪. ቅዱስ ገብርኤል
፫. ቅዱስ ሩፋኤል
፬. ቅዱስ ራጉኤል
፭. ቅዱስ ዑራኤል
፮. ቅዱስ ፋኑኤል
፯. ቅዱስ ሳቁኤል

❖ ረ/ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት

፩. የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን
፪. የሰርምኔስ ቤተ ክርስቲያን
፫. የጴርጋሞን ቤተ ክርስቲያን
፬. የትያጥሮስ ቤተ ክርስቲያን
፭. የሰርዴስ ቤተ ክርስቲያን
፮. የፊልድልፍያ ቤተ ክርስቲያን
፯. የሎዶቅያ ቤተ ክርስቲያን

❖ ሰ/ ሰባቱ ተዐምራት

ጌታ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈጸሙ ተዐምራት

፩. ፀሐይ ጨልሟል
፪. ጨረቃ ደም ሆነ
፫. ከዋክብት ረገፉ
፬. ዐለቶች ተሠነጠቁ
፭. መቃብራት ተከፈቱ
፮. ሙታን ተነሡ
፯. የቤተ መቅደስም መጋረጃ

❖ ሸ/ ሰባቱ የመስቀሉ ቃላት

፩. አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ
፪. አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው
፫. ዛሬ ከእኔ ጋራ በገነት ትሆናለህ
፬. እነሆ ልጅሸ እናትህ እነሆት
፭. ተጠማሁ
፮. ተፈጸመ
፯. አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እስጥሃለሁ

❖ ቀ/ ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን

፩. ምሥጢረ ጥምቀት
፪. ምሥጢረ ሜሮን
፫. ምሥጢረ ቁርባን
፬. ምሥጢረ ክህነት
፭. ምሥጢረ ተክሊል
፮. ምሥጢረ ንስሐ
፯. ምሥጢረ ቀንዲል

❖ በ/ ሰባቱ ዐበይት አጽዋማት

፩. ዐቢይ ጾም
፪. የሐዋርያት ጾም
፫. የፍልሰታ ጾም
፬. ጾመ ነቢያት
፭. ጾመ ገሀድ
፮. ጾመ ነነዌ
፯. ጾመ ድኅነት

ተ/ ሰባቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠሉ ነገሮች

፩. ትዕቢተኛ ዓይን ምሳ ፲፮፥፮፡፲፱
፪. ሃሰተኛ ምላስ
፫. ንፁህን ደም የምታፈስ እጅ
፬. ክፉ ሃሳብን የምታፈልቅ ልብ
፭. ለክፋት የምትፈጥን እጅ
፮. የሐሰት ምስክርነት
፯. በወንድሞች መካከል ጠብን የምታፈራ ምላስ

❖ ቸ/ ሰባቱ ፀሎት ጊዜያት

፩. ነግህ የጠዋት ጸሎት
፪. ሠለስት (የ፫ ሰዓት ጸሎት)
፫. ቀትር (የ፮ ሰዓት ጸሎት)
፬. ተሰአቱ (የ፱ ሰዓት ጸሎት)
፭. ሰርክ (የ፲፩ ሰዓት ጸሎት)
፮. ነዋም (የመኝታ ጸሎት)
፯. መንፈቀ ሌሊት (የሌሊት ጸሎት)

______________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

Happy PENTECOST: Divine Ethiopia

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 31, 2015

 

Its landscapes are biblical and its rituals haven’t changed for centuries.

There are moments when Ethiopia seems to belong to an atlas of the imagination – part legend, part fairy-tale, part Old Testament book, part pulling your leg.

In the northern highlands priests with white robes and shepherds’ crooks appear to have stepped out of a Biblical painting. In the southern river valleys bare-breasted tribeswomen, who scar their torsos for erotic effect and insert plates the size of table mats in their lower lips, seemed to have emerged from a National Geographic magazine circa 1930. Ethiopia.

resembles no other country in Africa”, wrote the great explorer Wilfred Thesiger, “or anywhere else.”

Its isolation is legendary. Not only was Ethiopia never colonised, but it also inflicted the greatest defeat on a European army in the history of the continent – at the Battle of Adwa in 1896. It was only the Italians, of course, but it still counts. Ethiopians were “forgetful of the world”, Edward Gibbon wrote, “by whom they were forgotten”. For long medieval centuries Europeans believed that Ethiopia was home to Prester John, legendary Christian ruler, descendant of one of the three Magi, keeper of the Fountain of Youth, protector of the Holy Grail, and all-round good guy who would one day rescue the Holy Land from the Muslims.

There are always two histories in Ethiopia: the history of historians, sometimes a trifle vague, often tentative; and the history of Ethiopians, a people’s history, confident, detailed, splendid, often fantastical. The two rarely coincide. Historians are still wringing their hands about the mysteries of Aksum in Tigray in the north, with its colossal stelae, its underground tombs, its ruined palaces and its possible connections to the Queen of Sheba. For a thousand years, until about AD 700, it was a dominant power in the region, “the last of the great civilisations of antiquity”, according to Neville Chittick , the archaeologist, “to be revealed to modern knowledge”.

Fortunately, the Ethiopians are on hand to fill in most of the historical blanks. The city was founded, they say, by the great-grandson of Noah. For 400 years it was ruled by a serpent who enjoyed a diet of milk and virgins. Historians may be divided about the Queen of Sheba but Ethiopians know she set off from here to Jerusalem with 797 camels and lot of rather racy lingerie to seduce King Solomon. Historians carelessly lost track of the Ten Commandments not long after Moses came down from Mount Sinai. Ethiopians have the originals under lock and key in a chapel in Aksum, guarded by those mute monks, assigned to kill all intruders.

Ethiopia may not be big on stylish boutiques hotels, littered with objets d’art and architectural magazines, but it is a delightfully old-fashioned place, with ravishing landscapes, sleepy villages and friendly, unhurried people.

Continue reading…

__

 

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , | Leave a Comment »

በዓለ መንፈስ ቅዱስ / ጰራቅሊጦስ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 22, 2013

Paraclete22አጋጣሚ? የእንግሊዙ ቴሌግራፍ ስለ ደብረ ዳሞ ይህን አቀረብገለባገለባውሲኤን ኤንእንኳን ያልተለምዶው ስለ ገዳማቶቻችን የሚለው አለ። ይህን ጽሑፍ በማቀርብበት በዚህ ሰዓት፡ ምስሉ ላይ የገባችው እርግብበመስኮቴ ብቅ ብላ ቁልጭ ቁልጭ ትልብኝ ጀመር። ቀስ ብዬ ፎቶ ካነሳኋት በኋላ፡ ጥሬ ስንዴ ለማምጣት ወደ መዓድ ቤት ገባሁ። ከፊሉን ስንዴ ለንፍሮ፣ ከፊሉን ደግሞ ለርግቧ ወስጄ ጣል ጣል ማድረግ ስጀምር እርግቧ ተንስታ በረረች። የበረረችበት አቅጣጫ ወደ ደቡብ ምስራቅ (የኢትዮጵያ አቅጣጫ) እንዲሁም ከኔ አንድ ኪሎሜትር ያህል እርቃ ልክ በዚያው አቅጣጫ ወደምትገኘው የመንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያንነው። ነገ ተነስተህ ወደዚያ መሄድ አለብህበማለት እርግቧ ምልክት እየሰጠችኝ መሆኑ ታወቀኝ። ወገኖቼን ይወደ ቤተክርስቲያኗ አመራለሁ፡ ከተቀቀለውም ስንዴበአብ፣ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እንቀምሳለን ማልተ ነውስብሐት ለእግዚአብሔር!

በዓለ መንፈስ ቅዱስ / ጰራቅሊጦስ

ይህች ታላቅ ዕለት ከቅድስት ሥላሴ አንዱ አካል የሆነው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ለቅዱሳን ሐዋርያት፣ ለቅዱሳን አርድእትና ለቅዱሳት ሴቶች የተገለጠባት ዕለት ናት፡፡ እነዚህ ሁሉ በጸሎት ተግተው በሚጸልዩበት ወራት መንፈስ ቅዱስ በተከፋፈሉ የእሳት ልሳን አምሳል የወረደበት ቅዱስ ቀን ነው፡፡

አስቀድሞ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳን ሐዋርያት ደብረ ዘይት በተባለ ታላቅ ተራራ ላይ ሳሉ እንዲህ ብሎ አስተምሯቸው ነበር “ኀይልን ከላይ ከአርያም እስክልክላችሁ ድረስ በኢየሩሳሌም በጸሎት ቆዩ፡፡”/ሉቃ 2436/ መቶ ሃያው ቤተሰብም በኢየሩሳሌም ሀገር በምትገኝ በቤተ መቅደስ በአንድነት ሆነው በጸሎት በመትጋት ቆዩ፡፡ ልጆችዬ መቶ ሃያው ቤተሰብ የሚባሉት 12ቱ ሐዋርያት፣ 72ቱ አርድእት/አገልጋዮች/ እና 36ቱ ቅዱሳን አንስት/ሴቶች/ ናቸው፡፡

ከዕርገት በኋላ በአሥረኛው ቀን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሐዋርያት ወዳሉበት፣ በጸሎትና በምሥጋና ወደ ሚተጉበት ሥፍራ በእሳት አምሳል /ምሳሌ/ ወርዶ በእያንዳንዳቸው ላይ ተቀመጠባቸው፡፡ ይሄንንም ሁኔታ ተከትሎ ምስጢር ተገለጠላቸው፣ ይፈሩ የነበሩት ሐዋርያትም ወንጌልን ለማስተማር ደፋሮች ሆኑ፣ በተለያየ ቋንቋዎች እንዲናገሩ እውቀት ተሰጣቸው፤ የእግዚአብሔርንም ጸጋ ተቀበሉ፡፡ ይህንን ታላቅ ኀይል እና ሰማያዊ ስጦታን የሰጣቸውን እግዚአብሔርን በታላቅ ዝማሬና እልልታ አመሰገኑት፡፡

በዓለ ሃምሳ የሚባለውን የአይሁድን በዓል ለማክበር ከተለያዩ ሀገራት የመጡ በጊዜው የነበሩ ቁጥራቸው በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የሐዋርያቱን ታላቅ የዝማሬና የእልልታ ድምፅ ሰሙ፡፡ ከመቶ ሃያው ቤተሰብ መካከል አንዱ የሆነው ቅዱስ ጴጥሮስ የተሰበሰቡት ሁሉም እንዲሰሙት ድምፁን ከፍ አድርጎ ቃለ እግዚአብሔርን እንዲህ ብሎ አስተማራቸው፡፡ “እናንተ የእስራኤል ሰዎች ሆይ እኛን የሰው ልጆችን ለማዳን እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ወደ ምድር መጥቶ ከክፉ ሥራ ተመለሱ፣ ኀጢአትን አታድርጉ፣ በቅድስና ኑሩ፣ ወደ እኔም ተመለሱ ቢላችሁ፤ እናንተ ግን ምንም በደል ሳይኖርበት ገረፋችሁት፣ አንገላታችሁት፣ በመስቀል ላይም ሰቀላችሁት፡፡ እርሱ ግን እግዚአብሔር ነውና ሞትን ድል አድርጎ ተነሣ፡፡ እርሱ ግን አሁንም ይቅር ባይ ነውና ከኀጢአታችሁ ተመለሱ ንስሐም ግቡ ፡፡” በማለት አስተማራቸው፡፡

የተሰበሰቡት ሰዎች ሁሉ ተገረሙ፡፡ ምክንያቱም ሐዋርያት በፊት የሚያውቁት አንድ ቋንቋ ብቻ ነበረ፡፡ በዚህ ሰዓት ግን ሰባ ሁለት ቋንቋን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ገልጦላቸው ለሁሉም በየቋንቋቸው አስተማሯቸው፡፡ ይህንንም ድንቅ ተአምር ከተመለከቱት ብዙዎች እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡ ወደ ሐዋርያትም ቀርበው “አባቶቻችን እናንተ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ናችሁና ምከሩን፡፡ እንደ እናንተ የእግዚአብሔር ልጆች እንድንሆንና በቅድስና እንድንኖር ምን እናድርግ?”በማለት ጠየቁ፡ በዚያች ቀን ቁጥራቸው ሦስት ሺ ያህል ሰዎች በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት አምነው ክርስቲያን ለመሆን ቀረቡ፡፡

ቅዱስ ጴጥሮስም እንዲህ አላቸው፡፡ “እነሆ ሁላችሁም ንስሐ ግቡ፡፡ በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት አምናችሁ ተጠመቁ፡፡” አላቸው በዚያው ዕለትም ሦስት ሺ ሰዎች ወደ ሐዋርያት በመቅረብ ኀጢአታቸውን ተናገሩ፤ ሐዋርያትም እግዚአብሔር ይፍታችሁ እያሉ ልጅነትን የሚያሰጣቸውን ጥምቀት አጠመቁዋቸው፡፡

ከዚያ ቀን ጀምሮም በየዓመቱ ይህችን ታላቅ የቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን የምትባለውን በዓለ ጰራቅሊጦስን ክርስቲያኖች በታላቅ ደስታና ምሥጋና እናከብራታለን፡፡ እናንተም ልጆችዬ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት በቤተ ክርስቲያን ተገኝታችሁ ቅዳሴ በማስቀደስ፣ መዝሙር በመዘመር እና በመጸለይ ይህችን ታላቅ በዓል ልታከብሯት ይገባል፡፡

የእግዚአብሔር አብ ጸጋ የእግዚአብሔር ወልድ ቸርነት የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አንድነት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን፡፡

ምንጭ

_

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: