Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘Negus Menilik’

የአፄ ዮሐንስ እና የንጉሥ ምኒልክ ዕርቅ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on August 30, 2011

 

*ከማሞ ውድነህ*

ካለፈው የቀጠለ

 

አሁንኮ አባታችን ያቀረቡልዎ ክስ የደንከልን በር ለሃይማኖት ተግባር ነው ብላችሁ ከገዛችሁ በኋላ ለንግድ ሥራና ለመንግሥት መገልገያ እንዲሆን አደረጋችሁ፤ የትንባሆ ነገር በሕዝቡ ዘንድ እንዲለመድ አድርጋችኋል ነውና ለዚህ መልስ ይስጡብለው ጠየቋቸው።

አባ ማስያስ በጸጉር የተሸፈነ የዱር ድመት የመሰለ ፊታቸውን ወደ ዕጨጌው ዘወር አድርገው፤

እሳቸውኮ እኛን በሆነ ባልሆነ የሚወነጅሉን አገራችሁ ከአውሮፓ መንግሥታት ጋር ተወዳጅታ በጥበብ እንዳትኮራ እንደ እነርሱ በመሳሰሉ ከእስክንድርያ በሚላኩ ሰባኪዎች አማካይነት አገራችሁ የግብጽ ጥገኛ ሆና እንድትኖር ከግብጽም ፈቃድ እንዳትወጣባቸው፡ በዚህ አገሩ የሚኖሩ እስላሞች ክርስቲያይኖች እንዳይሆኑባቸው የግብጽ ከዲብ ባለሟልነት እንዳይቀርባቸው ብለው ነውብለው ሲሳለቁ ዕጨጌውን ቁጣ ቱግ አድርጎ አስቆጣቸውና፤

ስሙ ወይ ማስያስ! ማንነትዎንኮ አሳምሬ ደርሼበታለሁ! የጣሊያኑ ንጉሥ ነፍስ አባት አይደሉም? ይህን ያምናሉ? ወይስ ይክዱኛል?” ብለው አፈጠጡባቸው።

ይኽ ነገር እውነት ነው?” ብለው ዮሐንስም ተጨመሩ። የችሎቱ ፍጥጫ ከአባ ማስያስ ላይ ተከመረ።

ብሆንስ ምንድነው ነውሩና ጥፋቱ?” አሉና አባ አንገታቸውን ደፉ።

ነውሩና ጥፋቱማብለው እጨጌም አባን ገለማምጠው፡ የችሎቱንም ሁኔታ ቃኝተው ክርክራቸውን ቀጠሉበት። ነውሩና ጥፋቱማ እንደ አባትነትዎ ከንጉሥዎ አጠገብ ሆነው መምከርና ማስተማር ሲገባዎ በወንጌል ስም፡ በክርስቶስ ስም ከሰው አገር ገብተው ሃይማኖት እየበረዙ ወንድምና ወንድም ለማፋጀት ተንኮል እየሠሩ መገኘትዎ ነውብለው ሲመልሱላቸው ችሎቱ ይበል ይበልብሎ አስተጋባላቸው።

አፄ ዮሐንስ አንገታቸውን አቀርቅረው ሲተክዙ ቆዩና በሆዳቸው ውስጥ ሲጤስ የነበረውን ንዴት ደጋግመው በመተንፈስ ካስወጡት በኋላ፤

እኮ ለዚህስ የሚሰጡት ምላሽ አለዎት?” ብለው ጠየቋቸው የዐይኖቻቸውን ቅንድቦች ዘግተው።

የንጉሥ ነፍስ አባትነት ከሀገራቸው ወጥታችሁ አታስተምሩ ብሎ አይከለከልም፡ እርሳቸውስ የከዲቡብለው ተናግረው ሳይጨርሱ እጨጌ አቋረጧቸውና፤

ጃንሆይ! በዚህ ችሎት የምትገኙ መኳንንትና ሊቃውንት! ልብ በሉልኝ! ‘ስሱ ሲበላ ይታነቃል! ሐሰተኛ በአነጋገሩ ይታወቃል እንዲሉ፥ የግብጽን ጦርና የመኳንንት ወስላቶች የምትረዱስ እናንተ አይደላችሁም? እውነተኞቹ የወንጌል ሰባኪዎች ከሆናችሁ ቀደም ሲል የቱርክ ጦር ዛሬም ግብጾች ክርስቲያኑን ሁሉ እስላም ካልሆንክእያሉ ሲያስጨንቁት ለምን አልገላገላችሁም?” ብለው አንገታቸውን አሰገጉባቸው።

እኮ? የደንከልን የባሕር በርስ ለንግድና ለወታደር ተግባር እንዲውል አሳልፋችሁ አልሰጣችሁም? የትንባሆ ዘርስ በእርሻ ላይ እየዘራችሁ ሕዝቡን እያስለመዳችሁት አይደለም? ለግብጥ ጦርና እኔን ካሎረፉ ወስላቶችስ ጥግና ጋሻ ሁናችሁ የለም? ይህን ሁሉ ታምናላችሁ? ትክዳላችሁ?” ብለው አፄ ዮሐንስም ቁጣና ፍጥጫ ጨመሩበት።

 

Continue reading…AtseYohannesNegusMenilik2

 

 

 

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: