Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘Meraras Aman Belai’

ንጉሥ አምደጽዮን – ጀግናው ኢትዮጵያዊ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 27, 2011

 

በመሪራስ አማን በላይ ተጻፈ። ከታላቅ ምስጋና ጋር


የአፄ ይኩኖ አምላክ የልጅ ልጅ የአፄ ውድም አርእድ ልጅ አምደጽዮን ስመ መንግሥታቸውን ሣልሣዊ ገብረመስቀል (ንጉሥ ላሊበላ) ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ተብለው በአንድ ሺህ ሁለት መቶ ዘጠና ስምንት (1298) .. ነገሡ።

የቀደማዊው ምኒልክን (ምንይልክ) ዘርና የነገሥታቱን ታሪክ ለማጥፋት ሮማውያንና አረቦች በሚልኳቸው መልእክተኞቻቸውና ጳጳሳቶች ከአዳም እስከ ምኒልክ የተጻፈው መጽሐፈ ሱባኤ መጽሐፈ አበው ከምኒሊክ እስከ አልአሜዳ ዘመን የተጻፉት መጽሐፍት ተለቅመው ጠፍተው በምትካቸው በአረብኛ ቃል የተጻፉ ተተክተው ሳለ እንዲሁ አይሁዳዊ የሆነቸው የአረቦች ጠላት ዮዲት ተነስታ የአረብኛን መጻሕፍቶችና አዋቂዎችን ስታቃጥል እንዲሁ አብሮ የነበረው በግእዝ የተጻፈው መጻሕፍ ሁሉ የሚበልጠው ተቃጥሎ ነበር።

ከግብፅ የመጡት ጳጳስ አባ ያዕቆብ፡ በአፄ አምደጽዮን መልካም ተግባር እንዲሁም የኖረውንና የተደበቀውን መጻሕፍት ሁሉ አሰባስቦ በመጻፉ ተናደዱና በየገዳማቱ በየአድባራቱ ለሚኖሩ መነኮሳትና መምህራን ጥሪ አድርገው እኛን ሳያማክር ሳይጥይቅ ወደየገዳማቱ መጻሕፍቶችን ልኮአልና እንዲቃጠሉ ምእመናኑም ለአፄ አምደጽዮን እንዳይገዙ አውግዙ ብለው የኤጲስ ቆጶስነት ማእረግ እየሰጡ ላኩዋቸው። አላማቸውም አፄ አምድጽዮን የአጻፉትን መጻሕፍት እንዳይቀበሉ ለማውገዝ ነበር።

በዚህን ጊዜ የጳጳሱን ፍቅድ ለመሙላት ብለው አባ አኖሪዎስና አባ ፊልጶስ የደብረ ሊባኖስን መነኮሳት አስከትለው ንጉሠ ነገሥቱ አፄ አምደጽዮን ከሚኖሩበት ዳጉ ሂደው በድፍረት ስር ማሽና ቅጠል በጣሽ አስማት ደጋሚ ደብተራ ሰብስበህ እግዚአብሔር የማይወደውን መጽሐፍት አጽፈህ በየገዳማቱ ልከሃልና በቶሎ ሳይራባ እንዲቃጠል አድርግ አሉት።

አፄ አምደጽዮንም እኔ የፃፍኩት እግዚአብሔር ለአባቶቻችን የአደረገላቸውን ተአምርና ቃልኪዳን እንዲሁ በዘመናቸው የሆነውን ሁሉ ለትውልድ ታሪካቸው እንዲተላለፍ እንዳይረሳ አጽፌአለሁ እንጂ እናንተ እነደምትሉትና እንደምታስወሩት አይደለም አላቸው።

አባ አኖሬዎስም ታሪክ ብትፈልግ ከግብጽ ለኛ ብለው የመጡትን ጳጳስ ቃል በሰማህና የሚሉህን ባደረክ ነበር፡ ግን አሁን በራስህ ፍላጎት ያደረከውን ስህተት አምነህ መጽሐፍቱን አሰብስብህ ባታቃጥለው አውግዤሃለሁ አገርም አይገዛልህ ብለው ተናገሩት።

ንጉሥ አምደጽዮንም አባ አኖሪዎስን በገበያ ላይ በጅራፍ እንዲገረፉ አዘዘ።

በዚህን ጊዜ የቤተ ክህነቱ ወገን በአባ አኖሬዎስ መገረፍ አጉረመረመ፡ ስሙንም ለማጥፋትና ለማቆሸሽ የአባቱን እቁባት እህቱንም አገባ ከሃዲም ነው ብለው መነኮሳቱ እየፃፉ በየገዳማቱ ላኩ አስወሩበትም፡ ነገር ግን ውግዘቱም ሆነ ሐሰተኛው ወሬ አምደጽዮንን ከክብራቸው ከመንግሥታቸው ሊያወርዳቸው ቀርቶ እንዲያውም በጦርነትም ይሁን በመንፈሳዊ ሥራቸው የእግዚአብሔር መንፈስ አልተለያቸውም፡ ከቀን ወደቀን መንግሥታቸው እየጸና እስከ ውቅያኖስ ባሕር ድረስ ባሉ ጎሣዎች ተከበሩ ታወቁ።

በአፄ አምደጽዮን መንግሥት ላይ የሚያምጽና መንግሥታቸውን የሚገለብጥ ሌላ ሰው እንዲነግሥ ቤተ ክህነቱ ተማከረ፡ በጻጻሱ በአባ ያእቆብ አሳሳቢነት በሚፈለጉበት የቱርክና የግብጽ የየመን ሱልጣኖችና ሸሆች በኢትዮጵያው በክርስቲያኑ መንግሥት ላይ እንዲያምጹና እንዲወጉት ለባላባቶች የጦር መሣርያና የጦር አሰልጣኞች ለወላስማዎች ላኩላቸው። የተላኩትም ከባላባቶች ጋር መጥተው ተቀላቀሉ።

በዚህን ጊዜ በንጉሥ አምደጽዮን በኩል ያለውን ኃይል የሚገልጽ ሰላይ እየላኩ ለይፋቱ ባላባት ለሃቅ አድዲን እንዲያምጽና እንዲዋጋ በአረብኛ ጽፈው ላኩለት። እርሱም ከአዳሉ ባላባት ጋር ተማክሮ ለአምደጽዮን እንደማይገብር አስታወቀ።

እንደዚህም ሆነ፡ ሃቅ አድዲን በወላስማ ላይ የበላይ እንደሆነ ኢትዮጵያንም ጠቅልዬ የክርስቲያን መንግሥት አጥፍቼ የእስላም መንግሥት በምትኩ አስቀምጣለሁ ብሎ ክርስቲያኖችን መግደል ዓብያተ ክርስቲያናትን ማፍረስ ጀመረ። እንዲሁም ንጉሥ ነገሥቱ እንደሚያደርጉት በኢትዮጵያ አገሮች የሚሾሙትን ሱልጣኖችና ኢማሞች ከሊፋዎችንም እየሾመ ይዘጋጅ ጀመር።

አፄ አምደጽዮንም ይህንን ወሬ በሰሙ ጊዜ በ1300 .ም ከተጉለት ወደ ይፋት ሄደው በወንድሙ በደራደርና በሐቅ አድዲን እየተመራ የሚመጣውን ሠራዊት ድል አድርገው ደራደርን በፈረሱ ላይ እንዳለ በጦር ወግተው ገደሉት። የእስላሞች ጦር መሪ ባላባት ሐቅ አድዲን ወደ ግዞት ወደ ጎጃም ተላከ። በእርሱ ፈንታ የወላስማን ማዕረግ ለወንድሙ ልጅ ለሰበን ሰጥተው የአመጸውን ሽረው ያላደመውን ሹመው በሰላም ወደ ዳጎ ተጉለት ተመለሱ።

አፄ አምደጽዮን በነገሡ በአሥራ ስምንተኛው ዘመነ መንግሥታቸው በወላስማ ስብረዲን የሚባል እስላም ተነሳና ለአምደጽዮን የሚገዛውንና የሚገብረውን ሁሉ አጥፍቶ አብያተ ክርስቲያናትን አቃጥሎ በምትኩ ጃሚዎችንና መስጊዶችን ማሰራት ክርስቲያኖችን መግደል ጀመረ።

አፄ አምደጽዮንም ሊቀ አፍራስ ዘየማን ሊቀ አፍራስ ዘጸጋም ሊቃውንተ ሃራ ዘፄዋ የሆኑትን ሁሉ ጥሪ አድርገው ከሾሙና ከሸለሙ በኋላ ሰብረዲን (ሰበርአደዲን)ወደሚኖርበት ወደ አዳልና ወደ ሞራ አገር ላኳቸው።

ከተላኩትም የቀኝ ፈረሰኞች የግራ ፈረሰኞች የጨዋ ሠራዊት አለቆች ከሰበር አደዲን ሠራዊት ጋር ገጥመው ድል አድርገው ብዙ ህዝብ ከማረኩና የታሰሩትን ከአስፈቱ በኋላ በመንደሩ ብዙ ወርቅና የዳሉል ሉል ድንጋይ ከአረብ አገር የተላከለት የጦር መስሪያ ሰይፍና ጦር ከሰብር አደዲን ቤት አግኝተው ወሰዱ። ሰብር አደዲን ግን አስቀድሞ ስለሸሸ ሊያገኙት አልቻሉም።

በአፄ አምደጽዮን ላይ ጠላት ሁነው የተነሱት የቤተክህነቱ ባለስልጣናት በየገዳማቱና በየአድባራቱ ህዝቡ አንገዛም እንዲልና እንዲያምፅ ሰብከውት ስለነበር በሰሜን በፀለምት በጠገዴ በወገራ በደንቢያ የተሾሙ ሁሉ አመፁባቸው።


EthiopianKingAmdetsion

(Please download file to open)

 

 

 

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , | Leave a Comment »

The 7 Heavens – Part ll

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 11, 2010

2.ራማ – ራማየ ሰማየ

በዚህ በራማ ሰማይ ክልል

  • ትእልፈተ ምእላፋት የሆኑ ክዋክብትና

  • ሠላሣ ሦስት ዓለማት

አሉት።

ከሠላሣ ሦስት ዓለማት መካከል ደብረቅዱሳን የሆነው የሐዩቀዩ ዓለም ይገኝበታል። በዚህ በየሐዩቀዩ ዓለም ውስጥ የሚገኙ ቅዱሳን ፍጥረት ከተፈጠሩ ጀምረው በዘለዓለም ያለመታከት እግዚአብሔርን ያመሰግናሉ፤ ለኃይሉም ክብር ያቀርባሉ። እንደማር ወለላና እንደወተት የመሰለ ጣፋጭና መአዛው ያማረ ባህር አለ ሁሉም በእርሱ ይረካሉ ይታደሳሉ።

3.ኢየሩየ (ኢሩያ) ሰማይ

በኢየሩይ ክልል ውስጥ በስምዋ ሰማያዊት

  • ኢየሩሳሌም

የምትባል ብሔረ ሕያዋን ዓለም አለች።

ከዚህች ዓለም ምድር የተፈጠረው አድማኤል ኪሩብ በእግዚአብሔር መልክና በእግዚአብሔር አምሳል ተፈጥሮ የእግዚአብሔር ልጅ ተብሎ በኢየሩይ ሰማይ ውስጥ በአድማኤል ስም ኦዶም ወደተባለች ዓለም ተወሰደ ከዚያም በክብር ሲኖር ከእግዚአብሔር ትዕዛዝ ከመውጣቱና ከመሳሳቱ የተነሳ ወደተፈጠረበት ዓለም ተጣለ ነገር ግን የተስፋ ዘር የሆነው ዳግማዊ አዳም ተነስቶ የአዳምን ነገድ ነፍሳት የሚሰበሰብበት የሕይወትና የምህረት ዓለም እንድትሆን አደረገ።

4.ውዱድ ዱዱያኤል ሰማይ

በዲዲያኤል ሰማይ ክልል

  • የረቀቁና የገዘፉ ታላላቅ ክዋክብቱና

  • ሃያ አንድ ዓለማት

ይኖሩበታል።

ያሬስያ የተባለው ፀሐይም በክልሉ በአሉ ፍጥረቶች ላይ ብርሃኑን ያበራል የጨለማም ጥላ ይታይበታል። ቅዱሳን መላእክትና እረቂቃን መናፍስት በሀያ አንዱ ዓለማት ውስጥ እንደንብ ሲራወዱ እንደመንጋ አእዋፍት ሲበሩና ሲንሳፈፉ ይታዩባቸዋል።

5.አርያአርያም ሰማይ

በዚህ በአርያም ሰማይ

  • የእሳት ፈሳሽ ፏፏቴ የሚፈስበት

  • የሚገለባበጥ የእሳት ነበልባል ቅጥር የተደረገበት

  • የነፋሳትና የውኃ ድምፅ የነጎድጓድም ድምፅ የመሰለ የቅዱሳን መላእክት ድምፅ የሚሰማበት

  • የብርሃናት መላእክት ለእግዚአብሔር ክብር የተሰለፉበት

  • በአንደበት በቃላት ሊነገር በምሳሌም ለማስረዳት ለመግለጽም በመጽሐፍ ሊጻፍ የማይሞክር የድንቅ የግሩም ልዩ ቅዱስ የሆነው መንበረ ፀባኦት

ይገኝበታል።

በአርያም ሰማይ የእግዚአብሔር መንግሥት ለሰው ልጆች ይታይ ዘንድ በክብርና በምስጋና ይመጣል። መንግሥቱም የዘለዓለም ሕይወት ነው። መንግሥተ ሰማይ ተብሎ ከሚጠራው ከሰማያቶች መካከል አንዱ የእግዚአብሔር መንግሥት በአርያም ነውና።

በዚህ በቅዱሱ መንበረፀባኦት ላይ የእግዚአብሔር የቃሉ ክብር ይገለጻል። ግዙፉን የሆኑ ሥጋ የለበሱና ረቂቃን የሆኑ ሁሉ ያዩታል። በፊቱም እየሰገዱ ከአንተ ከፈጣሪያችን በቀር ሌላ ቸር አባት ጌታ የለንም ለአንተ በአንተ አፍ እስትንፋስ ሁላችን ተፈጥረናል ስምህን በክብር እየጠራን እናመስግንህ ይሉታል ምህረቱና ቸርነቱ ለዘለዓለም እንደሆነ ታውቆአል።

ለዚህ ነው የአዳም ነገድ የሆነው ሁሉ እግዚአብሔርን የዘለዓለም መንግሥትህ ትምጣልንእያለ የሚጸልየውና በተስፋ የሚጠባበቀው፤ ለተመረጡት ቅዱሳን ንጹሐን ለጻድቃንም የተዘጋጀው የእግዚአብሔር መንግሥት በአርያም ሰማይ መሐልና ክልል ውስጥ በሚገኘው መንበረ ጸባኦት ስር በጽርሐ አርያም ነው። /አርያም አዳራሽ/

ጽርሐ አርያም የሕይወት ዓለም ነው፡ በአምስተኛው ሰማይ በአርያም ከመንበረፀጋኦትና ከጽርሐ አርያም በቀር ሌላ ዓለሞች የሉም።

የአዳም ዘር የሆኑት ሁሉ ፍጻሜ የሌለው ሕይወታችን በዚህ መንፈሳዊ ቅዱስ የሕይወት ዓለም ነው። የምንወርሰውም ሰማያዊ እርስታችን ብለን በተስፋ የምንጠባበቅ ትእዛዛቶቹን የፈጸምን ቅዱሳን የእግዚአብሔር ልጆች ብቻ ነን እሄውም በማይፈርሰው በመንፈሳዊ አካል እንጂ በሚፈርሰው በግዙፍ ሥጋ አካል አይደለም። በብፁዕ ሥጋዊና መንፈሳዊ አካል የሚወርሱ ከዚህ ዓለም ደስታና ጥቅም ያልተካፈሉ ብፁአን ንጹሐን የሆኑ ብቻ ናቸው እንጂ የዚህን ዓለም ኃጢአት የተካፈሉ ደምና ሥጋ ፈጽመው አይወርሱትም።

6. ኤረርኤሮርያ ሰማይ

በዚህ በስድስተኛው በኤሮርያ ሰማይ ክልል ውስጥ

  • አእላፋት ምዕልፋታት ክዋክብትና

  • ሠላሳ ሦስት ዓለማት

ይገኛሉ።

ከሠላሳ ሦስት ዓለማት መካከል እግዚአብሔርን ለካዱና እግዚአብሔርን ለማያውቁ ለአጋንንት መናፍስት ለተገዙና ለአምላኩ ሙታን ኃጥአን የተዘጋጁት የዳግመኛ ሞት ዓለሞች የጨለማ ዓለም ሲኦል የእሳት ዓለም ገሃነም የአጋንንት መናኽርያ መገናኛ በርባሮስ የፍዳና የስቃይ መፍለቂያ ዲያብሎስም የታሰረበት በርባሮስ ይገኝበታል።

እነዚሁ ከሠላሳ ሦስቱ ዓለማት መካከል አራቱ ዓለማት ለሰው ልጆች ሥጋ ለብሰው ለነበሩ አጸያፊና አስቀያሚ ነውና ከዚህ ከስቃይና ከፍዳ ዓለሞች ነጻ ለመሆን የእግዚአብሔር የቀኑ ትእዛዞችን መጠበቅ መልካም ሥራ / ስነ ምግባር እውነተኛ የሆነን እምነት መከተልና ማድረግ ነው። እውነተኛ ሃይማኖት የአለው ከሥራው ለአስተዋለው ይታወቃልና እሄውም ለሰው ልጆች ፍቅርና ሰላም የሚያመጣው ከእግዚአብሔር ነው። ከዚህ የወጣ ግን እስከፍርድ ቀን የጨለማ ዓለም ወደሆነው ወደሲኦል ይወርዳል። ከፍርድ ቀን በኋላ እንደየፍርዱና እንደየክፋቱ ለሥቃይና ለፍዳ ከሦስት ተከፍሎ ወደገሃነምና ወደ እንጦሮጦስ ወደ በርባሮስ ይጣላል። በዚያ የጩኽት የልቅሶ ብዛት ለዘለዓለም ይሆናልና ከመሆኑ በፊት የሰው ልጆች ሁሉ መልካሙን ሥታ ቢሰሩ እውነተኛውን ሃይማኖት ቢከተሉ የተሻለ እድል ነውና እግዚአብሔር በሰጠው ነጻ አእምሮ መምረጥና ማድረግ የራሱ የግሉ ውሳኔ ነው።

7. ሻዳያ ሰማይ

ይህ ሰባተኛው የሻድያ ሰማይ

  • የግዚአብሔር ግርማ መለኮት የሚገለጽበት

  • የብርሃናት ብርሃን የሆነ ክብሩ የሚይንጸባርቅበት

  • ባለሠረገላ መንኮራኩር መንበረ መንግሥተ ሰማይ (ጽርሐሰማይ) የተንሳፈፈበት በዙሪያውም እንደውኃ ጎርፍ የእሳት ማዕበል ድምፅ የሚሰማበት

  • የእሳት መንጦላዕት የተጋረደበት

  • እንደሚራወጹ የቀትር ንቦች ድምጻቸው እንደመብረቅ የሚያስደነግጡ መላእክት ብርሃናት በማህበር ዜማ ለእግዚአብሔር የክብር ምስጋና የሚያቀርቡበት

ሰማይ ነው።

እግዚአብሔር የዘለዓለም ሕይወት መንግሥቱን በሰማያት ያፀናበት የሰባቱም ሰማያት ጸጋ የገለጸበት የሰባቱ ምስጢር ይህ ነው።

እንዲሁ ለእኛ ለምድራውያን ሰባት ቀናትን የአዘጋጁልን ከሰባቱ ቀናትም መጨረሻ የሆነችውን እለት ማረፊያ ትሆነን ዘንድ እናከብራትም ዘንድ የሰባቱን ሰማያት ምሳሌ ምስጢር አደረገልን። ስለዚህ የእግዚአብሔር ምህረቱና ቸርነቱ በፍጡራኑ ላይ የበዛ ስለሆነ ስሙን በክብር እየጠራን እናመስግነው።

ሻዳይ በተባለው የምስጢር ዓለም ውስጥ የሚገቡ እርሱ ራሱ መርጦ ያዘጋጃቸው ንጹሐን ቅዱሳን ልጆቹ ብቻ ናቸው። ለዚህ የተመረጡ የዚህን ዓለም ደስታ ያልተካፈሉ ብሩሃን – ብሩካን ናቸው።

እግዚአብሔር በሰባቱ ብሩሃን ብሩካን ሰማያት ጠፈር ክልል ውስጥ መቶ ዓለማትን አእላፋተ ማእለፍታት ክዋክብትን ፈጥሮ ወደ እጣ ክፍሎቻቸው አሰፈራቸው። ለዘለዓለም በአሉበት እንዲጸኑ አደረጋቸው። ለሰባቱ ሰማያት ሠራዊቶቻቸው ይሆኑ ዘንድ ዓለማትንና ክዋክብትን እንደአደለ ሁሉ እንዲሁ ለዓለማት ሐብቶቻቸውና ሠራዊቶቻቸው ይሆኑ ዘንድ ልዩ ልዩ የሆነ የሚሳብና የሚንቀሳቀስ የሚዘልም የሚበረግግም አራዊትንና እንስሳትን በበሐርም ውስጥ የሚሳብና የሚንሳፈፍ ደማዊ ነፍስ ያለውም የበቀለም ፍጥረት በሰማይ በታች በአለ ጠፈርም የሚበሩ የአእዋፋትና የንስር ዓይነቶች እንደየወገኑ በመሬት የበቀለ በባሕርም የበቀለ የእፀዋት ዓይነት ፈጥሮ አደላቸው። ሁሉም እንደተፈጥሮው እንደየወገኑ እንደዘር ዓይነቱ ብዙ ተባዙ ብሎ ዘርን ሰጣቸው።

እግዚአብሔር በዓለማትና በከዋክብት መካከል አንዱ ፍጥረት ወደሌላው ክልልና ክበብ (ጠፈር) እንዳይተላለፍ ገደብ የአለው የተፈጥሮ ባህርይ ሰጣቸው። ስለዚህ ተንቀሳቃሽና የማይንቀሳቀሱ ደማዊ ነፍስና ለባዊ ነፍስ የአለው ፍጥረት ሁሉ ከተፈጠሩበት ዓለሞቻቸው እንዲፀኑ ተመልሰውም ወደተፈጠሩበት እንዲቀላቀሉ የእድሜ ገደብ አደረገባቸው። አንደኛው ፍጥረት ለሌላው ፍጥረት ምግቡ እንዲሆንም አዘጋጀው።

ለሕይወት እግዚአብሔር ለነፍስም ሕይወት ለአካልም ነፍስ ለደምና ለሥጋ ለአጥንትም ለተገጣጠሙት ብልቶች ሁሉ አካል እንደሚያስፈልጋቸውና በአካል አንድ ሁነው ፍላጎታቸውን እንደሚያከናውኑ ሁሉ እንዲሁ ከእግዚአብሔር ዘንድ በእግዚአብሔር ቃል ለተፈጠሩት ለመቶ ዓለማት በውስጣቸውና በውጭ የሚርመሰመስ ተንቀሳቃሽና የማይንቀሳቀሱትንም ሁሉ ፈጥሮ እንዲበዙም በውስጣቸው ዘርን ሰጣቸው። ሁሉም እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑ ሆኑ።

እግዚአብሔርም የፈጠረው ሁሉ መልካም እንደሆነ አየ። ፍጥረቱንም ብሩህ ብሩክ ሁን ብሎ ባረከው። እስትንፋስንና ሕይወትን የሚሰጠው የእግዚአብሔር መንፈስ የህይወት እስትንፋስ ተሞሉ። የስነልቦና የአእምሮ የስነቃልን ድምጽ እንደየወገናችው ተሰጣቸው። በተሰጣቸው ስነ አእምሮና ስነቃል ፈጣሪያችን አንድ አምላክ እግዚአብሔር እንደሆነ ስሙን አውቀው በክብር አመሰገኑት።

ከመጀመሪያው ከፍጥረቱ አስቀድሞ ከእርሱ ዘንድ ጥበብ ተወለደ። ወላጅና ተወላጅ በፍጥረቱ ዘንድ ታወቀ፤ ከበረ ከፍ ከፍም አለ።

ጥበብም በእውቀት ከበረ በማስተዋልም ሰማያትን ዘርግቶአልና በውስጣቸውም ዓለማትን ፈጥሮ አፅንቶአልና የፈጠረው ሁሉ ከእርሱ ሰለተፈጠረ ለእርሱ ሆነ። ለእርሱ የሆነውን የመረጠውን ብሩህ – ብሩክ ቅዱስ ሲለው ፈጣሪውን በራሱ ድምጽና ቃና የሚያመሰግንበት የልሳን አንደበት አደለው። የፈለገውንም የሚመርጥበት አእምሮ ክፉንና ደጉን የሚለይበት ህሊና እርሱ ማን ወይስ ምን እንደሆነና የአለበትን ሠፈር ቦታ ወይም የአቅሙን ገደብ የሚለካበት ስነ ልቡናን ሰጠው።

በተሰጠው ስጦታ የማይጠቀም ፍጥረት ካለ የከንቱ ከንቱ ኢምንት ነው። የእጣው እድልም ጥፋትና ስህተት ነውና እሄውም ሰይጣን ሆነ ማለት ተሳሳተ ጠፋ ማለት ነውና።

__________________________________________________________________

የሰባቱ ሰማያት ስም ዓለሞቻቸው
1 ኢዮር (አየር) አሥራ ሁለት 12
2 ራማ ራማየ ሠላሳ ሦስት 33
3 ኢየሩይ (ሰማያዊት ኢየሩሳሌም/ጌልጌል) አንድ 1
4 ውዱድ ዲድያኤል ሃያ አንድ 21
5 አርያ – አርያም (መንበረ ጸባኦት ያለበት) 0 0
6 ኤረር ኢሮርያ ሠላሣ ሦስት 33
7 ሻዳይ ኤልሻዳይ (የሕይወት ምንጭ የአለበት፡ ስሙም ጔልጔል ይባላል) 0 0

___________________________________________________________________

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , , , | Leave a Comment »

The 7 Heavens: The 12 Worlds of Eyor Heaven

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 22, 2010

አዮር ሰማይ ክልል ውስጥ የአሉት አሥራ ሁለት ዓለሞች


  1. ሐመልማል

    ይህ የምድር ሠራዊት እንሆን ዘንድ እኛ የተፈጠርንበት ዓለም ነው። ጠባቂውና እንዲሰለጥንበት እግዚአብሔር የፈቀደለት አድማኤል ኪሩብ ይባላል። የአዳም ነገድ ሁሉ ከእርሱ አብራክ ወጥቶአል።

  2. ረሐም

    የዚህ ዓለም ጠባቂ መልአክ ሳውራኤል ኪሩብ ነው። በዓለም ረሐም ውስጥ የሚኖሩ ፍጥረቶች የበግና የፍየል መልክ የመሰለ ገፅ ሲኖራቸው የተሰጣቸው አእምሮ ከሰው ልጆች የላቀ የራቀውን የሚያውቁ የረቀቀውን የእግዚአብሔር ፍጥረትን ማየት የሚችሉ ናቸው። ከነርሱም ሌላ በረሐም ዓለም ውስጥ የተለያዩ ገጽ ያላቸው ቁጥራቸው ትእልፈተትእልፊታት ፍጥረታቶች አሉ።

  3. ገውዛ

    የዚህ ዓለም ጠባቂው ኪሩብ መልአክ ሱርያኤል ነው። ገውዛውያን መልካቸው እንደ ሰው ልጆች መልክ ሁኖ ቀንድና ጅራት አላቸው። የጅንጆሮና የጉሬዛ መልክ የመሰለ የአላቸውም አሉ። ሁሉም ሁለት እጆችና ሁለለት እግር አሏቸው እንዲሁ ግዙፋንና እረቂቃን የሆኑ በራሪዎች ይኖሩባቸዋል። እርስ በእርሳቸው አይነካኩም የሳውራ አፈር ቅመው ይኖራሉ።

  4. ሻርታ

    የዚህ ዓለም ጠባቂው ኪሩብ መልአክ ስርጣጣኤል ይባላል። በሻርታ ዓለም የሚኖሩ ፍጥረቶች እንደ ዳሞትራ ስምንት እግሮች የአላቸው የአንበጣ ገጽ ያላቸው ምግባቸው እርስ በእርስ በመበላላት አንዳንዶችም እንደ እባብ የሚያሸቱበት አፍንጫ ባይኖራቸውም በምላሳቸው መካከል በአለ ቀዳዳ ያሸታሉ፡ በምላሳቸው ይነድፋሉ፡ ያያሉም፡ በየጊዜው ተፈጥረው የሚሞቱ ፍጥረቶች ናቸው።

  5. ሰውድ

    የዚህ ዓለም ጠባቂው መልአክ ኪሩብ አዛዝኤል ይባላል፡ ሰውዳውያን ወደዚህ ዓለምና ወደ ሌላው ዓለም ለመንጠቅ እድል ተሰጥቷቸዋል። በሄዱበት ምድር ያለውን እፅዋት ያደርቃሉ፤ እሳተ ገሞራ ይፈጥራሉ፤ ተንቀሳቃሹን ሁሉ በነፋስ ያደርቁታል፤ እግዚአብሔር ለመቅሰፍት ያዘጋጃቸው ናቸው። ምግባቸው የሚቃጠል ዲንና ባሩድ የመሰለ ነው፡ ነገር ግን በሄዱበት ዓለም እንዲኖሩ እግዚአብሔር ስላልፈቀደላቸው ተመልሰው ወደተፈጠሩበት ዓለም ይሄዳሉ እንጂ

  6. ሰንባላ

    የዚህ ዓለም ጠባቂው መልአኩ ኪሩብ ስምስማኤል ይባላል። በሰንበላውያ ዓለም ትእልፊተትእልፊታት የሚሆኑ በአየር የሚንሳፈፉና የሚበሩ በምድር የሚሽከረከሩ አእዋፋትና እንስሳት አራዊትም አሉ። እንደነዚህ ምድር ዓለም እርስ በእርሱ ይጣላል፤ ይበላላልም። ነገር ግን የማይበላሉ አሉ እነርሱም እድሜያቸው በእነሱ አቆጣጠር ከመቶ እስከ አራት መቶ ይደርሳል። ነገር ግን የእኛ ዘመንና የሰንበላውያን ዘመን የተለየ ነው።

  7. ሚሳን

    የዚህ ዓለም ጠባቂው መልአክ ሚሳኤል ይባላል። የሚሳውያን መልካቸው የእንስሳና የአውሬ መልክ ይምሰል እንጂ የተፈጥሮ ባህሪያቸው ቅዱስ ነው። እግዚአብሔርን በክብር ያመሰግናሉ ይዘምራሉም። ከኤሮርያ ሰማይ ክልል ውስጥ ከሜምሮስ ዓለም ክበብ ውስጥ የሚኖሩትን ሮሃንያን ይመስላሉ /ረውሃንያ/ የተለያዩ የዜማ ድምፅ መሥሪያዎች አሏቸው።

    አንዳንድ ግዜ ወደ እኛ ዓለም ምድር ይመጣሉ፤ የሚከለክላቸው የዓየር ጠባይ የለም፤ ግዙፋንም እረቂቃንም አሉአቸው። በባሕር ቢሄዱ አይሰጡም በእሳተ ገሞራ ቢገቡ አይቃጠሉም አለቱን ሰንጥቀው ቢገቡ የሚያግዳቸው የለም፡ የእግዚአብሔርን ፍጥረት ያከብራሉ የሰው ልጆችን ይወዳሉ እግዚአብሔርን ከማመስገን አፋቸው አይቋረጥም።

  8. አቅራብ

    የዚህ ዓለም ጠባቂው መልአክ አቅርናኤል ይባላል። በዓለም አቅራብ ውስጥ የሚኖሩት ፍጥረታት በባሕር ውስጥ ይኖራሉ። የመልካቸው ገጽ የዝሆንና የጊንጥ ቅርፅ አላቸው። የተለያዩ የፍጥረት ነገዶች አሉ ሁሉም በበሐር ውስጥ እንጂ ወደሌላ የአፈርና የእሳት ጠባይ ወደአላቸው አይሄዱም አይኖሩምም።

  9. ቀውሳ

    የዚህ ዓለም ጠባቂው መልአክ ቀውቃሳኤል ኪሩብ ይባላል። በቀውሳ መሬት የሚኖሩ ከእሳት ተፈጥረው ከእሳት ፈሳሽ ውስጥ ስለሚኖሩ ብዛታቸው እንደሌሎች ዓለም ፍጥረት አይበዙም ቀውሳውያን የአገኙትን ይመገባሉ ያቃጥላሉ የእሳት ሕይወት ነው ያላቸው።

  10. ዠዲ

    የዚህ ዓለም ጠባቂው መልአክ አጂብጀማኤል ይባላል። በጀዲ ወይም በዠዲ ዓለም የሚኖሩ ፍጥረታት ከዚህች ምድር ዓለም የተፈጠሩትን እንስሳትና አራዊት አእዋፋትንም ይመስላሉ። በመልክ በግጽ እርስ በእርሳቸው የተለያዩም ቢሆን በልሳን ቋንቋ አንድ ናቸው በተለያየ የድምፅ መሳሪያ ይጠቀማሉ። ከሰው ልጆች የላቀ አእምሮ ስላላቸው የተጠበቡ መርማሪዎች ናቸው። በሰሩት የጥበብ መንኮራኵር ብዙ ዓለማትን ጎብኝተዋል ነገር ግን ከተፈጠሩበት ከዠዲ ዓለም ተለይተው ስለማይኖሩ ወደ መጡበት ተመልሰው ይሄሃሉ። ምግባቸውን እንደ ሰው ልጅ አብስለው የሚበሉና በመአዛው ብቻ የሚረኩ ነገዶች አሉአቸው እግዚአብሔርን በጣም ያመሰግናሉ።

  11. ደለዋ

    የዚህ ዓለም ጠባቂው መልአክ ደለዋውኤል ኪሩብ ይባላል። ይህ ደለዋ ዓለም የክበቡ ጥልቀት በጣም የጠቆረ ጨለማ ከመሆኑ የተነሳ እንደበርባሮስ የሚያስፈራ ነው። ነገር ግን በውስጡ የሚኖሩ እልፍ አእላፋትና ትእልፊተ አእላፋት የሚሆኑ ፍጥረታት በትናጋቸውና በምላሳቸው በማሽተት የሚፈልጉትን መርጠው ይበላሉ።

    በጆሮአቸው በዓይናቸው ፈንታ በምላሳቸው እንዲያዩና እንዲሰሙ እግዚአብሔር ስለፈጠራቸው ጨለማንና ብርሃንን ለይተው አያውቁም።

  12. ሁት

    የዚህ ዓለም ጠባቂው መልአክ ኩምኩማኤል ይባላል። በሁት ዓለም የሚኖሩ ፍጥረቶች እንደንብ መንጋ በአንድ ላይ የሚሰፈሩ እንደተራራም ይከመራሉ፤ ከመካከላቸው እንደንብ ወይም እንደምስጥ አንዲት እናት አላቸው። እናቲቱ እድሜዋ አልቆ ከሞተች ሁሉም በነው ያልቃሉ አፈር ይሆናሉ፤ ሕይወታቸው በእንስቲቱ ብቻ ነው ከነሱ ሌላ ሕይወት ያለው ፍጥረት የለም።

    በኢዮር ክበብ ውስጥ ያሉት አስራ ሁለት ዓለማት እነዚህ ናቸው። የአእምሮ መንፈስ የአለው አስተውሎ ይመርምርና ይወቅ ጥበብ በዚህ አለ።

______________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

ብሩክ Happy አዲስ New 2002 Year ዓመት!

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 9, 2009

ከወሮች መስከረም ከወሩም መጀመሪያ ቀን ለአዲሱ ዘመን እንዲሆን የሰንደቅ አላማ መታሰቢያ ቀን የቃልኪዳን ምልክት ቀስተደመና የሆነው ሰንደቅ አላማ እንደቆመ

_________________________________________________________________________________

EnqutatashErta

_________________________________________

የሚከተለው ምስጢራዊ ታሪክ የተገኘው፡ ክቡር መሪራስ አማን በላይ፡ ተርጉመው ካቀረቡልንና መጽሐፍ ዣንሸዋ የሚል ስያሜ ከተሰጠው ድንቅ መረጃ ጽሑፍ ነው። ክቡር መሪራስ አማን በላይ፡ ስለተባበሩን እጅጉን እናመሰግናለን፡ እግዚአብሔር ይባርክልን።

_________________________________________

ናህኤል የተባለው ኖህ እንደቅድመ አያቱ ሄኖክ በትውልዱ ዘመን ከቤተሰቦቹ ጋር እግዚአብሔርን የሚፈራ ጻድቅና ፍጹም ሰው ነበረ።

ኖህም ከሚስቱና ከልጆቹ ከልጆቹም ሚስቶች በምድር ለዘር እንዲተርፉ ከሰበሰባቸው አራዊትና እንስሳ አእዋፋትና አሞራዎች ጋር በመሆን ከጥፋት ውሃ የእግዚአብሔር ትእዛዝ ከመፈጸሙ የተነሣ በመርከቢቱ ውስጥ ገብቶ እንዲሁ ሌሎቹንም አስጠግቶ አድኖአል።

አዳም ከኤዶም ገነት ስለወረደ ንስሐ በመግባቱ እግዚአብሔር የተስፋውን ዘር ከሴት ልጁ ተወልዶ እንደገና የተነጠቀውን የእግዚአብሔርን ልጅነት እንደሚመልስለት ቃል ኪዳን አድርጎለት ከነበረችው ቀን እስከ ጥፋት ውኃ ድረስ ሁለት ሺህ ሁለት መቶ አምሳ ዓመተ ፍዳ ነበረ። ውኃው ከጎደለና ከደረቀ በኋላ ምድር ፀጥ ብላ በለመለመ ዛፍና በአትክልት ቅጠል በሳርም ተሸፍና ነበር። እንደዚሁ ከአሥራ ሁለቱ ወራቶች መካከል በመጀመሪያው ውር በመስከረም ምድሪቱ በአበባ ተሸፍና ነበር።

እንደዚህም ሆነ፡ ኖህና ቤተሰቦቹ መርከቢቱ በአራቱ መንኮራኩር መካከል በአንደኛው /አራራት/ በአሉባር ተራራ በአረፈችበት በመጀመሪው ወር በመስከረም ከወሩም በመጀመሪያው ቀን እርግቢቱ ለኖህ ለግላጋ ቀንበጥ የሆነ የወይራ ቅጠል እንደሰጠችው ሁሉ እንዲሁ መካከለኛው ልጁ ካም የአደይ አበባና የጽጌረዳ አበባ አምጥቶ እንቁዮጳሺ (እንቁጣጣሽ) ብሎ ሰጣቸው። እንደጠራ እንቁ ሁኑ ሲል ነው። በሌላ በኩል ደግሞ እግዚአብሔር ከጥፋት ውኃ እንድንድንና እንድናመልጥ መርከቢቱን እንድንሰራ በማድረጉና ለዘር እንድንተርፍ በማስቀረቱ መርከቢቱን በዚህች ቀን ምድር እንድትነካ በማድረጉ የእግዚአብሔርን ስምና ቸርነት ከትውልድ ወደ ትውልድ የምናስተላልፍበት ቀን ነው።

ስለዚህ ለአዲሱ ዘመን ቀኑም ለወሮች መጀመሪያ ለሆነው ወር ለመስከረም የመጀመሪያው ቀን ይሆናል፡ ወሩም የወሮች መጀመሪያ ይሆናል ሲል ካም ለቤተሰቦቹ እንቁጣጣሽ አላቸው። እነርሱም በየአመቱ የአጣህ አሉት።

ኖህም መርከቢቱ ምድር የነካችበትን መስከረም አንድ ቀንን ለወሩ የመጀመሪያው ቀን ለዓመቱ ወራቶች የመጀመሪያው ወር እንዲሆን ለልጅ ልጅ ከልጅም ወደ ልጅ እንዲተላለፍ በመጽሐፍ ዣንሸዋ ጽፎና መዝግቦ አስቀመጠው።

ኖህ የክህነቱ ስም ናህኤል የተባለው ልጆቹን አል፦ እግዚአብሔር የምናደርገውን ያሳየን ዘንድ ምሕረቱና ቸርነቱ ለዘለዓለም ከኛ ጋር መሆኑን እናውቅ ዘንድ ቃሉን ስምተን ትዕዛዛቱን እንፈጽም ዘንድ ሁለት ሰባት በሰው ልጅ በደል ምክንያት በጥፋት ውኃ የነገለውን የዛፍ ግንድና የደረቀውን እንጨት ሁሉ ሰብስቡ ከምርቱም፡ በዚያም አቃጥለን ለእግዚአብሔር የሚቃጠልና ንጹህ የሆነ የእህል መስዋእት እናቀርባለን አላቸው።

ልጆቹም የልጆቹም ሚስቶች ደከመን ሳይሉ ለሁለት ሰባት ተራራ ያክል አድርገው ግንዱን አመሳቅለው እንጨቱንም በበላዩ ከመሩት፡ አባታቸው የአላቸውን ሁሉ አደረጉ።

ናሆም ለእግዚአብሔር ዳግመኛ ከንጹህ እንስሳና ከንጹህ እህል ፍሬ መስዋእትን በአሉባር ተራራ ላይ በሰራው መሠዊያ ላይ ደመራውን አቃጥሎ አቀረበ።

እግዚአብሔር ናህኤል የተባለው ኖህ የአቀረበውን መስዋእትና መአዛ የአለውን ሽታ ተመለከተና ተቀበለው። እንደዚህም አለው፦ አንተ ከጠፋው ትውልድ ተለይተህ በፊቴ ጽድቅ ሁነህ በመገኘትህ እንደ ሄኖክም አካሄድህን ከእግዚአብሔር ጋር ስለአደረክ ከጥፋት ውኃ ልትድን ችለሃል፡ አሁንም እልሃለሁ፦ ከእኔ ከፈጠረህ ሌላ አምላክ ላልፈጠረህ እንዳታመልክ እንዳታምንም የልጅ ልጆችህም እንዲሁ ያደርጋሉ።

እኔም እነሆ ቃል ኪዳኔን ከአንተ በኋላ ከሚመጣው ከዘርህ ጋር አቆማለሁ፡ ከእናንተ ጋር ላሉትም የሕይወት ነፍስ ላላቸው ሁሉ በምድር ለሆኑ ሁሉ ይሆናል።

በእኔና በእናንተ መካከል ከእናንተ ጋር ደማዊ ነፍስና ልባዊ ነፍስ ሕያው ነፍስ በአለው መካከል ሁሉ ለዘለዓለም የማደርገው የቃል ኪዳን ምልክትና ሰንደቅ አላማ የሚሆን ይህ ነው።

ቀስቴን በደመና አድርጌአለሁ፡ የቃልኪዳኑም መታሰቢያ ምልክት በእኔና በምድር መካከል ይሆናል። በምድር ላይ ደመናን በጋረድሁና ዝናብ በአወረድሁ ጊዜ ቀስቲቱ በደመናውና በብርሃኑ መካከል ትታያለች፡ በእኔና በእናንተ የአለው የመታሰቢያውን ቃል ኪዳን አስባለሁ።

ሥጋ ያለውን ሁሉ ያጠፋ ዘንድ ዳግመኛ የጥፋት ውኃ አይሆንም፡ ቀስቲቱ በደመናና በፀሐይ ብርሃን መካከል እንደሆነች ሁሉ እንዲሁ በእኔና በምድር ላይ በሚኖረው ሥጋ በለበሰው ደማዊ ነፍስና ልባዊ ነፍስ መካከል የአቆምኩትን የዘለዓለም ቃል ኪዳን ለማሰብ አያታለሁ፡ የቃል ኪዳኔ መታሰቢያ የሰንደቅ ዓላማ ምልክት ይህ ነው አለው።

ኖህም ከእግዚአብሔር መልአክ ከሱርያኤል የሰማውንና የተማረውን የእግዚአብሔርን ትእዛዛት ቃል ኪዳኑን ሁሉ ልጆቹና የልጆቹ ልጆች ሁሉ እንዲጠብቁትና እንዲፈጽሙት አስተማራቸው።

ከመጽሐፈ ሄኖክና ከትንቢተ ሄኖክ ቀጥሎ ኖህ ስላለፉት አባቶቹ ታሪክና ስለጥፋት ውኃ ስለ እንሳስትና ስለአራዊት ስለሰማያትና በውስጣቸው ስላሉት ዓለሞችና ከዋክብት ስለባህር አሦችና ስለሰማይ ወፎች በምድር ስለሚሳቡ ተንቀሳቃሾች ስለድንጋዮችና ስለ እፀዋት ስለ ንፁህነትና ስለ እርኩሰት ስለ መድኃኒትና ስለ መርዝነት የሚገልጹትን ሁሉ ከኖህ በፊት ያልታወቁትን ምስጢሮች ገልጾ ጽፎአል። ይህም መጽሐፍ በመጽሐፈ አበው ወመጽሐፈ ኖህ ይባላል።

ከመጽሐፈ ኖህ በፊት የነበረውን ዜና አዳምንና መጸሐፈ ሄኖክን ጨምሮ ለልጆቹ እንዲያጠኑትና ለልጆቻቸው እንዲያስተላልፉት አስረክቦዋቸዋል። ነገር ግን ተከታዩ ትውልድ ከመልካሙ ተግባር (ስነ ምግባር) ይልቅ መጥፎውን ሥራ (ግብረ እኩይ) እየመረጡ ያጠኑበትና ጠላታቸው የሆነውን ሁሉ ይበቀሉበት ጀመር። ነገር ግን መርከቢቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ምድርን የነካችበት መስከረም አንድ ቀን ሁለተኛ ህዳር መባቻን ከመርከቢቱ ወጥተው የብስን የረገጡበትን ሦስተኛ ሚያዝያ በኋላ ፋሲካና ትንሣኤ የሆነበትን ወደመርከቢቱ የገቡበትን ቀን መታሰቢያ በዓል አድርገው ያከብሩታል። ይሄም በካም ልጆች ዘንድ አዲስ ዓመት አዲስ አዝመራ ሲመጣና ክረምቱ ገና ሳይመጣ እስከ አሁን የሚያከብሩና የሚያስታውሱ አሉ።

ኖህ ለልጆቹና ለልጆቹ ልጆች ለተከታዩ ትውልድ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍና መታሰቢያ ይሆናቸው ዘንድ በዓላትን አዘጋጀላቸው።

  1. ኖህ መርከብ ለመስራት ግንድን መጥረብ የጀመረበት መርከቢቱ በአሉባር ተራራ ላይ የአረፈችበትን እግዚአብሔር ከኖህ ጋር ቃል ኪዳን የአደረገበትን የመጀመሪያውን ወር መስከረም ከወሩም የመጀመሪያውን ቀንና የአሥራተኛው ቀን የመታሰቢያ የደስታ ቀን እንዲሆን አዟል።

  2. ኖህና ልጆቹ ከመርከቢቱ የወጡበትና አብረውት የነበሩትን እንስሳዎችና አራዊቶች ሌሎችንም ብዙ ተባዙ ምድርን ሙሉዋት ብሎ ባርኮ የአሰናበታቸው የህዳር መባቻን በየዓመቱ መታሰቢያ በዓል እንዲሆንና እንዲከበር ሲል ሥርዓት አድርጎ ሠርቶላቸዋል።

  3. ኖህና ልጆቹ የልጆቹ ሚስቶች ለዘር እንዲቀሩ አብሮ ከሰበሰባቸው ፍጥረታት ጋር ሁሉ ከጥፋት ውኃ ይድኑ ዘንድ ወደ መርከቢቱ የገቡበት ሚያዝያን ወር ከወሩም ሁለተኛውን ቀን መታሰቢያ በዓል እንዲሆን በሥርዓት እንዲከበር አዟል። ይህም ወር በአቢብ ወር እስራኤሎች ከግብፅ የወጡበት ቀን ስለሆነ የፋሲካ በዓል ይደረግበታል። እነዚህም መታሰቢያዎች ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ከመቃብር ይነሣ ዘንድና ዓለምን ያድን ዘንድ ስለ አለው ምስጢሩን በምሳሌ አስቀደመው፡ ይህም የትንሳኤ በዓል ነው።

ኖህ ሦስቱን በዓላቶች ከሌሎች በዓላት ይልቅ እንዲከበሩና እንዲታሰቡ ሥርአት አድርጎ በመጽሐፉ ጽፎ ለልጆቹ ሰጥቷል።

እነዚህንም በዓላት የእግዚአብሔር ኪሩብ ገብርኤል በሰሌዳ ላይ ጽፎ ለመላእክትና ለሰው ልጆች በሰማይና በምድር መታሰቢያ ይሆናቸው ዘንድ በእግዚአብሔር ተራራ ሥር ባለው የውኃ ምንጭ ራስ አስቀምጦ አተመው።

እንደዚሁ ከዚህች ቀን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በሰማይና በምድር መካከል በእግዚአብሔርና በሰው ልጆችም መካከል እግዚአብሔር የአደረገውን ቃል ኪዳን ያስታውሱት ዘንድ የእግዚአብሔር መልአክ ሱርያኤል በደመናውና በፀሐዩ ብርሃን መካከል ይታይም ዘንድ የቃል ኪዳኑን መታሰቢያ ምልክት የሆነው ቀስት በእንቁዮጵ ላይ ጽፎ ከሕይወት ምንጭ ውኃ ራስ አትሞ አስቀምጦታል።

ብሩክ አዲስ 2002 ዓመት!

________________________

Posted in Ethiopia, Infos | Tagged: , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: