Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘Memihir Girma’

ቀጣፊው የእንግሊዝ ጋዜጣ | “ኢትዮጵያውያን ‘ጋኔን ለማስወጣት’ የወር ደሞዛቸውን ለመምህር ግርማ ይከፍላሉ”

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on July 6, 2018

ዲያብሎስ በቅናት ሲያሽሟጥጥብን ደስ ሊለን ይገባል፤ ምክኒያቱም የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ለማወቅ እንችላለንና።

ይህን ቪዲዮ የሠራሁት የእንግሊዙ “ደይሊ ሜይል” በድህረ ገጹ ላይ ትናንትና ካወጣቸው ፎቶዎች ነው።

እነዚህን የመሳሰሉት ፎቶዎችና ቪዲዮዎች ለእኛ የተለመዱ ናቸው፤ መንፍሳዊ ውጊያ ምን እንደሚመስል በግልጽ የሚታይባቸው ፎቶዎች ናቸው። ለዲያብሎስ አሽሟጣጩና ተከታዮቹ ግን በተቃራኒው ከንቱ ነገር ነው። ዓይኖቻችን የተለያዩ ናቸው!

ይህ ታዋቂ የእንግሊዝ ጋዜጣ አንድ ዳዊት Tesinsky የተባለ ወስላታ የቼክ ሪፓብሊክ ፎቶ አንሺን ወደ መምህር ግርማ ልኮ ምስሎቹን ካገኘ በኋላ በድህረ ገጹ ላይ በጣም ቅጥፍት በተሞላበትና እጅግ በጣም አንቋሻሽ በሆነ መልክ ረጅም ዘገባ አቅርቧል። ኢትዮጵያውያንን፣ ተዋሕዶ ክርስትናን እና መምህር ግርማን እያንቋሸሸ፡ ማለት ነው። እንዴት ፈቀዱለት?!

ዲያብሎስ ቀናተኛው ከጻፋቸው ዓረፍተ ነገሮች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፤ ለማሽሟጠጥ ሲሻ ቃላቶቹን በቅንፍ ውስጥ አስቀምጧቸዋል፣ ምንም እንኳን በእንግሊዝኛው በ አንተእና በ አንቱልዩነት ባይኖርም፤ ግን ስለ መምህር ግርማ አንተበሚል መንፈስ ነው የተጻፈው፦

ርዕሱ፦ “በአንድ የጅምላ የጥምቀት ሥርዓት 150 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን “ጋኔን ለማስወጣት” የወር ደሞዛቸውን ለአንድ ቄስ ይከፍላሉ” የሚል ነው።

  • + ተወዳጅ የጊዜ ማሳለፊያ፦ ከአዲስ አበባ ወጣ ብሎ በሚገኝ መንደር (የረር ሥላሴ) መቶ አምሳ የሚሆኑ ሰዎች “ጋኔን አውጭውን” ዝነኛ ፈዋሽ ቄስ ለማየት መጥተዋል
  • + የምዕመናኑ ግንባር ላይ መስቀሉን በማሳረፍ ተቀደሰ ውኃ‘/ ጸበል ያርከፈክፍባቸዋል።
  • + ፎቶው፡ በሁሉም የዕድሜ ክልል ያሉ ሰዎች በህውከት ሲያለቅሱ፣ ሲጮኹና ሲፈራገጡ ያሳያል።
  • +የአምላክ ሥራ፦ ጋኔን አውጭው ፈዋሽ ቄስ መምህር ግርማ ወንድሙ የሰውየው ግንባር ላይ መስቀሉን ሲያሳርፉበት በእብደት ሲጮኽ ፎቶው ያሳያል
  • + ሌላው ፎቶ ላይ፡ አንዲት ሴት እየጮኸች ወደ መምህር ግርማ ስትመጣ እና ጎልማሶች ጸበል እየተረጩ ሲያለቅሱ ይታያል።
  • + ብዙ ዝናብ፦ ከ እርኩሳን መናፍስት ነጻለመሆን የመጣችው ሴት ላይ የጸበል ፉፏቴ ተለቀቀባት።
  • + የነፃነት ዋጋ፦ እንደሚባለው ከሆነ መምህር ግርማ ጋኔን የሚያወጡትተፈዋሾቹ የአንድ ወር ደሞዛቸውን ሲከፍሏቸው ነው።
  • + የዘመናዊ መድኃኒትን መቀበል የማይችሉት ኢትዮጵያውያን የወር ደሞዛቸውን ከፍለው “ጋኔን ያስወጣሉ”።

ቀጣፊው ቼክ ፎቶ አንሺ ይህን ብሏል፦

መምህር ግርማ በእዚህ ቦታ የበለጠ ገንዘብ ስለሚያገኝ በሌሎች ዓብያተክርስቲያናት ለማገልገል አሻፈረኝ ብሏል፤ እንዲያውም የኢትዮጵያ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከምታገኘው ገንዘብ በላይ ያገኛል።”

አቤት ቅጥፈት! አቤት ተንኮል! አቤት ጥላቻ! ያሰኛል። ግን በድጋሚ ደስ ይበለን። እግዚአብሔር በራሱ መንገድ የራሱን ፎቶዎች ያነሳል።

[የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፰፥ ፵፬]

እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና።

እኔ እስከማውቀው ድረስ፡ መምህር ግርማ በየረር ሥላሴ የሚሰጡትን ታታሪ የሆነ መንፈሳዊ አገልግሎት ካቆሙ ቆይተዋል፤ ታዲያ ይህ የእንግሊዝ ጋዜጣ ስለ እርሳቸው አሁን ለመናገር የወሰነው ከምን የተነሳ ነው? ከማንስ ጋር በመተባበር? ኃይሌ ገ/ሥላሴ (የረር ሥላሴ) ይኖርበት ይሆን? እነ አንዳርጋቸውስ?

የእንግሊዝ ሜዲያ ይህን የመሰለ ተንኮልና ጥላቻ በእንግሊዝ፣ በደካማው የአንግሊካን ቸርቻቸው እና በጨካኙ የንጉሣውያን ቤተሰብ ላይ ተንፍሶ አያውቅም፤ ፀረክርስትና ዘመቻው ግን ያው በመጧጧፍ ላይ ነው። ከሃዲዎች!

ሊሲፈራውያኑ የአንግሎአሜሪካውያኑ ስውር የዓለማችን መሪዎች የመፍንቅለ መንግስት በኢትዮጵያ አደረጉ፤ ያዘጋጇቸውን ሰዎች ሥልጣን ላይ አስቀመጡ፣ ቢቢሲ በኢትዮጵያ ቋንቋዎች አገልግሎት ጀመረ፣ እነ አንዳርጋቸውን እንዲለቀቁ ወተወቱ፣ ክትባት እየወጉ ያሳደጓቸውን እነ ኃይሌ ገ/ሥላሴን ፀረተዋሕዶ የሆነ ነገር እንዲናገሩ አዘዟቸው፣ የኦጋዴን ነዳጅ እንዲወጣ ተፈቀደ፣ የኢትዮጵያ ግድብ ኬኒያ ልጃቸውን እንደሚጎዳ ተዘገበ፣ ደቡብ ኢትዮጵያውያን የብጥብጥ እሳት እንዲፈጥሩ ተቆሰቆሱ፣ 666ቷ ሮቦት ሶፊያ ወደ ኢትዮጵያ ተላከች።

እኅተ ማርያም ትክክል ናት “አቤት እንግሊዝ ጉዷ” ስትለን። በትናንትናው ዕለትም ሰሬ ወረዳ እና ጋትዊክ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ በድጋሚ ተሰምቶ ነበርታይቶ የማይታወቅ ኃይለኛ የአየር ሙቀት በመላው አውሮፓ አለ፣ የድርቅ ዘመን እየመጣባቸው ነው ፣ የእስልምና እና የግብረሰዶም መቅሰፍት ያመጣባቸው መዓትማ ተዘርዝሮ አያልቅም።


The Exorcist: Priest performs mass exorcism on hundreds of people who paid up to a month’s wages to rid themselves of demons at Ethiopian ceremony


  • Hundreds queue up to meet with a priest and ‘exorcist‘ at a rural church outside Addis Ababa, Ethiopia

  • Exorcism rituals to ‘rid the body of demons‘ sometimes take place in the Ethiopian Orthodox church

  • This instance saw 150 line up to see a priest charging up to one-month’s wages for an ‘exorcism

  • Images show the priest touch believers on the forehead with a cross and spraying them with ‘holy water

A mass exorcism ritual involving hundreds of Ethiopian Christians, who paid up to a month’s wages to be punched by a priest and doused in ‘holy water‘, has been captured in a fascinating photo series.

Some 150 people had been queuing up at a church outside the Ethiopian capital Addis Ababa in order to meet a local celebrity healer whom they believe would be able to free them from ‘demons‘.

The photos show people of all ages crying hysterically as a cross touches their forehead, or being held down by relatives as they try to avoid being ‘exorcised‘, kicking and screaming.

Set me free: A woman is being held in place by two men as she screams while being sprayed with holy water

God’s work‘: A man is seen crying hysterically as priest and healer Memehir Girma Wedimu touches him with a cross

Other striking shots show a woman seemingly screaming with all her might as she is brought up to the priest, grown men in tears, and dozens of people being hosed down with holy water.

They were taken by Czech photographer David Tesinsky who had ventured to Ethiopia specifically to capture exorcism rituals.

After two weeks of trying to convince locals to let in photograph the religious events, he found the Yerer Selassie church, not far from Addis Ababa, where locals were lining up to meet Ethiopian Orthodox priest Memehir Girma Wedimu.

‘People were crying, screaming and Memehir was punching them,’ said Tesinsky. ‘Memehir, I learned, had rejected all other churches, because he earned more money than the church itself.

He kept asking for money – I saw one very old woman give him a $100 (£76) bill to ‘expel’ her of demons and he still wanted more, even though that $100 was most likely all she could earn in one month.’

Popular past-time: Some 150 people had lined up at the church outside Addis Ababa to meet with the priest

Rain in abundance: A young woman who had lined up to be ‘freed‘ from evil spirits is doused in water

Fear and faith: A man needs to be held in place and struggles as Memehir Girma Wedimu performs a ritual

Price for freedom: Memehir Girma Wedimu reportedly charged those who turned up for an exorcism up to one-month’s wages for a ‘spirit cleanser‘ ritual

Strong beliefs: Nearly three quarters of Christians in Ethiopia claim to have experienced or witnessed an exorcism

‘These exorcism rituals are usually performed if someone is not responding to modern medicine or if they are misbehaving.

‘Their families think they are possessed by a “demon spirit” or “buda” – the power of the evil eye. They must be performed by a local priest.’

Ethiopia has had a significant Christian population for centuries, and the Ethiopian Church is the largest pre-colonial Christian church in Africa.

The belief in demons and the devil found across the religious spectrum is strong, in particularly in rural areas, and according to a 2010 survey, nearly three quarters of Christians in Ethiopia claim to have experienced or witnessed an exorcism.

Source

‘People were crying, screaming and Memehir was punching them,’ said Tesinsky. ‘Memehir, I learned, had rejected all other churches, because he earned more money than the church itself. „

My Note:

What a load of crap, pack of lies, woow! Now they send a wicked Czech Photographer to mess up with Ethiopians, huh!

[John 8:44]

You are of your father the devil, and you want to do the desires of your father He was a murderer from the beginning, and does not stand in the truth because there is no truth in him Whenever he speaks a lie, he speaks from his own nature, for he is a liar and the father of lies.

______

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

Ethiopian Exorcist — መምሕር ግርማ በቅዱስ እስጢፋኖስ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 6, 2012

መንፈሣዊ ነፃነት ያለው ሰው ሥጋዊ ነፃነትም አለው!

_

 

ቪዲዮው ላይ የምናየው መምሕር ግርማ በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ተገኝተው ብዛት ካላቸው ምእመናን አጋንንት ሲያወጡ ነው።

በቅርቡ በአዲስ አበባ ከገጠሙኝ አስደናቂ የሆኑ ሁኔታዎች ይህ አንዱ ነበር።

መምሕር ግርማ በተመሳሳይ ድርጊት ተሠማርተው የቀረጹት ቪዲዮ ከሁለት ዓመታት በፊት እዚህ ብሎግ ላይ አቅርቤ ነበር። ነገር ግን እስከ አሁን ድረስ እሳቸው በአዲስ አበባ እንደሚገኙ አላውቅኩም ነበር።

ዘንድሮ በአዲስ አበባ ከገጠሙኝ አስገራሚና ድንቅ ከሆኑት ሦስት ሁኔታዎች መካከል ይህ አንዱ ነበር። ሦስቱም አጋጣሚዎችበጣም ተመሳሳይ በሆነ መንገድ የተከሰቱ መሆናቸው እስካሁን ድረስ ያስገርመኛል።

ዕለቱ ረቡዕ ነው፤ ከጠዋቱ 4 ሰዓት ላይ ጎተራ አካባቢ አውቶብስ ቁጥር 56 (ባልሳሳት) ውስጥ ገብቼ ወደ ሽሮ ሜዳ ለመጓዝ ወሰንኩ። (የአዲስ አበባ አውቶብስ ካልሞላ በቀር በሁሉም መስክ በከተማዋ የተሻለ መጓጓዣ ሆኖ ነው ያገኘሁት)። ትንሽ መጓዝ እንደጀመርን የአውቶብሱ ነጂ እብድነት የተሞላበት ዓይነት አነዳድ ነበረው፡ አውቶብሷን ልክ እንደ ስፖርት መኪና ወዲያና ወዲህ እያዋዥቀ ሌሎች መኪናዎችን በግራና በቀኝ በችኮላ እይቀደመና ጥንቅቃቄ በጎደለበት ሁኔታ ፍሬን እየያዘ በአውቶብስ ውስጥ የነበረነውን 20 የምንሆን ተጓዦች በመረበሽ በደብረዘይት መንገድ መሃል መንገድ ላይ ይነዳ ነበር። ሁኔታው ስላላስቻለኝ ፡ ጠጋ ብዬ ቁጣየን በጩኽት ገለጥኩለት፤ ምናለ ተጠንቅቀህ ብትነዳ፤ ይህን ሁሉ ሰው ጭነህ፤ ከጓደኞችህ ጋር በጎን እያወራህ መንዳት ተገቢ አይደለም፤ ምናለ ይህን ምስኪን መንገደኛ ባክብሮትና ትህትና ብታገለግሉ…” ሌሎች መንገደኞችም የኔን ቁጣ በመደገፍ ይወቅሱት ጀመርሹፌሩ ግን ይባስ ብሎ አውቶብሷን በይበልጥ ያርገበግባት ነበር። እኔም አላስቻለኝም፤ ልክ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት አውቶብሷን ሲያቆማት ወርጄ የአውቶብሷን ታርጋ መዘገብኩ። በእውነት፡ አንበሳ አውቶብስ ድርጅት በቅርብ የማውቃቸው ሰዎች ስለነበሩ የዚህን ሹፌር ጉዳይ እንዲከታተሉ አደርጋለሁ ብዬ ዛትኩ።

እስጢፋኖስ ጋር ከወረድኩ በኋላ ወደ ቤተክርስቲያኗ አመራሁ። እዚያም በጣም ብዙ ሰዎች ተሰባስበው አንዳንዶቹም ሲጮሁና ሲወራጩ አየሁ። ምን ይሆን ብዬ አንዷን እናት ስጠይቃቸው፡ ሰዎቹ መምህር ግርማን ብለው መምጣታቸውን ነገሩኝ። ሙሉ በሙሉ በውሃ ርሰው የነበሩት ሴትዮዋም፡ ና! ልጄ ይህን የመሰለ መቁጠሪያ እዚያ ማግኘት አለብህ ብለው መቁጠሪያው ወደሚገኝበት ቦታ ወሰዱኝ። አባ ግርማ ከሚገኙበትና ብዙ ሰዎች ከተሰበሰቡበት የቤተክርስቲያኗ ቅጥር ግቢ በጥግ በኩል አንድ ተለቅ ያለ መኪና ውስጥ የነበሩ ሴትዮ መቁጠሪያውን በ20 ብር ይሸጡ ነበር። ሴትዮም፡ መቁጠሪያ ነው የምትፈልገው?” አሉና አውጥተው ሰጡኝ። እኔም፡ ይቅርታ ያድርጉልኝና፡ አባ ግርማን ፎቶ ወይም ቪዲዮ ማንሳት ይቻል ይሆን?” ብዬ ሴትዮዋን ስጠይቃቸው፡ ሴትዮዋም በቁጣ፡ አይቻልም! ፈጽሞ አይቻልምብለው መለሱልኝ። ለመሆኑ ጉዳዮ እርስዎን ይመለከታል ወይስ ሌላ ፈቃድ ሊሰጠኝ የሚችል ሰው አለ?” አልኳቸው። እሳቸውም ወደ እኔ ቀና ብለው ሳይመለከቱ ቁጣቸውን ቀጠሉ። እኔም የሴትዮዋ ትህትና አልባነት ገርሞኝ ትንሽ ራቅ ብለው ወደሚገኙ ለአንድ ቄስ አባት ሁኔታውን አወሳኋቸው። ልጄ ከውጭ ነው የመጣኽው መሰለኝ፤ ይህን የመሰለ ቦታ ላይ ብዙ ዓይነት መናፍሳት ስለሚገኙ አንዳንዱ ሰው ሊፈተን ሊረበሽ ይችላልና አይድነቅህ ፡ ዝም ብሎ ማለፉ ነው የሚመረጠው ፡ ፎቶ ለማንሳት ከፈልግህ መምህር ግርማን ሄደህ ጠይቃቸውአሉኝ፡ በትህትና። እኔም ትክክለኛነታቸው ከምስጋና ጋር ካሳወቅኳቸው በኋላ፡ ወደ መምህር ግርማ ጠጋ ብዬ ከበስተኋላቸው ለሚገኙትን ረዳቶቻቸው እሳቸውን ማነጋገር እንደምፈልግ ሹክ አልኳቸው። ጋኔን በማስወጣት ላይ የሚገኙት መምህር ግርማም ዘወር አሉና፡ አንተ ማን ነህ? ከየት ነህ? ምን ፈልገህ ነው?” ብለው በያዙት መስቀል ግንባሬን ገፋ አደርጉት። ቀጥለውም እጃቸውን ወደ አንገቴ ሰደድ አድርገው እዚያ የሚገኘውን መስቀሌን መዳሰስ ጀመሩ፤ ምንድነው መስቀሉ በጨሌ የታሠረው?|” ፡ እሺ፡ ግድ የለም ፊልም ማንሳት ትችላለህበማለት ፈቃዳቸውን ገለጹልኝ። እኔም ከምስጋና ጋር አማተራዊ የፊልም አንሺ ሥራ ውስጥ በመግባት እጅግ በጣም አስገራሚ የሆኑትን ሁኔታዎች መታዘብ ጀመርኩ። ስማ፡ እዚያ ጋር፡ እዚያ ጋር፡ ፊልም ማንሳት አይቻልም!” የሚሉ የተለያዩ ድምጾች ከያቅጣጫው ይመጡብኝ ነበር። ነገር ግን እንደተፈቀደልኝ ሲያውቁ ፀጥ አሉ።

በርግጥ መምህር ግርማ ልዩ ጸጋ የተሰጣቸው፡ እድነስማቸውም ግርማ ሞገስ ያላቸው አባት መሆናቸውን ጠጋ ብሎ በማየት መገንዘብ ይችላል። ጸበሉ በተፈለገው ዓይነት መንገድ ይፍለቅ፡ በሰው ላይ የሚፈጥረው መንፈሳዊ ክስተት ኃያልና እውነትነት የተሞላበት ነው።

ከፍተኛ መንፈሳዊ ጦርነቶች በሚካሄዱባት አገራችን ዲያብሎስ ህዝባችንን እያዘናጋ ወደርሱ ወጥመድ ለማግባት ሌት ተቀን ደፋ ቀና እንደሚል፡ ቤተክርስቲያኖቻችን፡ ጸበላችንና መስቀላችን ከርሱ ጦር መከላከያ ይሆኑን ዘንድ የተሰጡን ውድ በረከቶች መሆናቸውን ይህን በመሳሰሉት አጋጣሚዎች በዓይኔ፡ በአካል ለመታዘብ እድሉ ስለነበረኝ፡ ያው ምስክር ሆኛለሁ።

ከቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያንም ልዩና ቅዱስ ከሆነው መንፍስ ጋር አብሬ ከወጣሁ በኋላ፡ የ 56 ቁጥር አውቶብሱ ሹፌር ሁኔታ ትዝ አለኝ፤ ሹፌሩን መገሠጼ ትክክል ቢሆንም ለቀጣሪው ክስ ላቀርብበት የነበረው ስሜታዊ ኃሳብ ትክክል እንዳልሆነ ገባኝ። እንዲያውም ምስኪኑ ሹፌር እኔን ያለ ፕላኔ በተዘዋዋሪ መንገድ ወደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ያደርሰኝ ዘንድ የሆነ ኃይል ልኮት መሆኑን በመገንዘቤ፡ በወቅቱ ደግሜ አግኝቼው ቢሆን ኖሮ ሞቅ ያለ የወንድማዊ ሰላምታ ልሰጠው በጣም ተመኝቼ ነበር።

አበው ይናገሩ

እስኪ ቀስቅሷቸው አበው ይናገሩ

የምንኩስና ግብር ምን ነበር ሚስጢሩ

የክርስቲያን ህይወት ምን ነበር ተግባሩ

መቃብሩን ክፈቱት አበው ይመስክሩ

እኔስ ሰው አማረኝ የሃይማኖት ጀግና

ወልድ ዋህድ ብሎ በእምነቱ የፀና፡፡

ጀግና ሰው አማረኝ ጠላት አሳፋሪ

ንጽህት ድንግል ብሎ እምነቱን መስካሪ

ነቢያት በመጋዝ የተሰነጠቁት

ሀዋርያት ቁል ቁል የተዘቀዘቁት

ሰማእታት በእሳት የተለበለቡት

ቅዱሳን ገዳም ደርቀው የተገኙት

ሚስጥሩ ምን ነበር አበው ይናገሩት፡፡

ይናገር ዝቋላ ጊሸን ላሊበላ

የቅዱሳንን አጽም ለምን እንዳልበላ፡፡

ዋልድባ ይናገር ዜጋመልም ሳይቀር

እንባቸው መፍሰሱ ለምን እንደነበር፡፡

ነበር ወይ ፈልገው ሹመት ሽልማት

ወይስ ሃብት ንብረት የተሟላ ቤት

ወይስ አምሯቸው ነው ፈልገው መሞት

እናንተ ገዳማት ምስጢሩን አውሩት፡፡

ጎበዝ ሰው አማረኝ በእምነቱ የፀና

ምግባር ሃይሞኖቱን በእጅጉ ያቀና፡፡

እንጦንስ የወለደው በምግባር በእምነት

ተምሮ ያደገ ከተክለሃይማኖት፡፡

የጊዮርጊስ ወዳጂ የት ነው የሚገኘው

በመሃል ከተማ በአራዳ ውስጥ ነው

ወይስ በዝቋላ በደብረ ሊባኖስ በደብረ ዳሞ ነው፡፡

ወገን ሰው ናፈቀኝ አይኔን ሰው አማረው

የሃይማኖት ጀግና የት ነው የማገኘው?

ልጋባ ወይ ዋልድባ ጫካ ካለበት

ማህበረ ስላሴ ከቅዱሳ ቤት

አክሱም ጊሸን ማርያም ከቃልኪዳን ቦታ

ይገኛል ወይ ጀግና ጠላት የሚረታ፡፡

ፈርሃ እግዚአብሔር በልቡ ያደረ

ቤተክርስቲያንን ያልተዳፈረ

የት ነው የሚገኘው ለሃይማኖቱ ሟች

ለተዋህዶ እምነት ጠበቃ ተሟጋች

የወገን መመኪያ የከሃዲ መቅሰፍት

ማነው እሱ ጀግና ተኝቶ እንደሆነ ይነሳ ቀስቅሱት

እስኪ ቀስቅሷቸው አበው ይናገሩ

የምንኩስና ግብ ምን ነበር ምስጢሩ

የክርስቲያን ህይወት ምን ነበር ተግባሩ

መቃብሩን ክፈቱት አበው ይመስክሩ፡፡

ወገን ሰው ናፈቀኝ አይኔን ጀግና አማረው

በእምነት የፀና የት ነው የማገኘው፡፡

ወልድ ዋህድ ብሎ በእምነቱ የፀና

ብቅ ይበል እንየው እሱ ማን ነው ጀግና

በጎችን ከተኩላ ነቅቶ የሚጠብቅ

መከራ ቢከበው ከቶ የማይሰቀቅ

የሃይማኖት ጀግና ቆራጥ ሰው ገበሬ

እንደዚያ እንደጥንቱ ይገኛል ወይ ዛሬ፡፡

የወገን የዘመድ ጥቅም ያላወረው

የመናፍቆች እጅ ኪሱን ያልዳበሰው

የዓለም ደስታዋ ልቡን ያልማረከው

የክርስቶስ ወዳጅ እሱ ጀግና ማነው?

ምስጢርን ከምስጢር አንድ አድርጎ ተምሮ

ወልድ ዋህድ ብሎ ሃይማኖት መስክሮ

እንጦንስን መቃርስን በልቡ ያኖረ

ከጳውሎስ ከቄርሎስ ጥበብ የተማረ፡፡

ድንግል እመቤቴ ብሎ የሚመሰክር

መሆኗን የሚያምን ማህደረ እግዚአብሔር

ቋቅ እንትፍ ብሎ የጠላ ክህደትን

ትንታግ ምልስ ጭንግፍግፍን

ልሣነ ጤዛ መናፍቅን

ወልደ አርዮስነ ዲቃላውን

በሰይፈ ሥላሴ የሚቀላ

ጀግና ማን ነው ብቅ ይበላ፡፡

ነበር ወይ ያን ጊዜ ለሹመት መጓጓት

እስኪ ጎርጎርዮስ ይምጣና ጠይቁት፡፡

ፍቅርንም ይጠየቅ አባ ሕርያቆስ

ምስጢርን ጠባቂ ወይም አባ መቃርስ

የክርስቶስ ባሪያ የአጋንንት መቅሰፍት

ወንጌል አስተማሪ የሃይማኖት አባት

ይህንን ጉድ እንዲያይ ይምጣ ተክለሃይማኖት

የፀሎት ገበሬ ገብረመንፈስ ቅዱስንም ይነሳ ቀስቅሱት

ይነሳ ጊዮርጊስ ይመስክር ምስጢር

የሃይማኖት ፍቅር ምን እንደነበር፡፡

ከእናቶቻችንም አሉ ለፍጥረት ያዘኑ

ዲያቢሎስ እንዲማር ጌታን የለመኑ

ስንቱን ልዘርዝረው የአባቶችን ሙያ

እመር ብለው የወጡት ከስጋ ገበያ

ፆም ፀሎት ነበር የሃይማኖት ጋሻ

እንደ መስኖ ውሃ ከነዱት መነዳት

አላማው ምንድን ነው የዘመኑ ወጣት፡፡

እኔስ ሰው አማረኝ በእምነቱ የፀና፡፡

ዐይኔን ሰው አማረው ጀግና ሰው ገበሬ

ሃይማኖት መስካሪ እንደ ጥንቱ ዛሬ፡፡

ምንጭ፡ ደቂቀ ናቡቴ

_

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: