Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘Maskal’

ህመም የለም ፣ መዳፍ የለም ፥ መስቀል የለም፣ አክሊል የለም

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 27, 2021

ህመም የለም ፣ መዳፍ የለም ፥ እሾህ የለም ፣ ዙፋን የለም። ሐሞት የለም ፣ ክብር የለም ፥ መስቀል የለም፣ አክሊል የለም።

በመስቀል ላይ ሣለ የገሃነመ እሳትን ጠባቂ ጭፍሮች ያስደነገጣቸው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው!

በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለውን የጸብ ግርግዳ አፍርሶ በመስቀሉ ሠሌዳ ላይ በደሙ ቀለምነት የሕይወታችንን መጽሐፍ የጻፈልን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። መስቀሉ፣ ጦሩ፣ ስሙ ጋሻችን ሆኖልና ድነነናል።

💭 በአቅራቢያዬ የምትገኘውን ውብ የቤተ ክርስቲያን ሕንፃ ዛሬ ስጎበኛት ይህን በአክሊል ቅርጽ ተሠርቶ የቆመውን መብራት አብሬ ለማየት ቻልኩ። ከእኅታችን የመስቀል ወረብ ጋር በእውነት ድንቅ ድንቅ ነው!

አቤቱ በዘመኑ ሁሉ የጥፋትና የኃጢአት አውሬ (ዲያብሎስ) እንዳይቀርበን በሐጹረ ቅዱስ መስቀልህ አጥርነት ጠብቀን፤ አሜን!

✞✞✞መስቀል ኃይላችን ነው!✞✞✞

______________________________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ቅዱስ እስጢፋኖስ | በአዲሲቷ ኢትዮጵያ የመስቀሉ ልጆች የዋቄዮ-አላህ አጋንንትን በቅርቡ ያቃጥሏቸዋል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 27, 2021

✞✞✞መስቀል ኃይላችን ነው!✞✞✞

♰♰♰

No Pain, No Gain; No CROSS No CROWN

ያለህመም ማግኘት የለም ፥ ያለ መስቀል ፣ አክሊል የለም

ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን፣ ለመጀመሪያ ጊዜ በንግሥት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት በ፲፱፻፱ ዓ/ም ተመሠረተ። በዚያን ጊዜም ዘመኑ በፈቀድው መልክ የቤተ ክርስቲያኑ ሕንጻ ተጠናቆ ሲወደስበት ሳለ፤ በጣልያን የወረራ ዘመን፣ በ፲፱፻፴፪ ዓ/ም ባልታወቀ ምክንያት የእሳት አደጋ ደርሶበት ሕንጻው ተቃጠለ።

ኢትዮጵያ ከ ፋሺስት የወረራ ቀንበር ከተላቀቀች በኋላ፤ የግንባታው ሥራ በሥራ ሚኒስቴር ኃላፊነት በዘመናዊ መልክ እንዲሠራ በተሰጠው ትዕዛዝ መሠረት ሚኒስትሩ ባላምባራስ (በኋላ ብላቴን ጌታ) ማኅተመ ሥላሴ ወልደ መስቀል በአንድ በኩል የአካባቢውም ኗሪ እና የቤተ ክርስቲያኑ ምእመን በመሆናቸው እና በሚኒስቴራዊ ኃላፊነታችው፤ ሥራውን በቅርብ እየተከታተሉና እየተቆጣጠሩ አሠርተውት የአሁኑ ሕንጻ ግንባታ ፍጻሜ አግኝቶ ጥቅምት ፲፯ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓ/ም ቅዳሴ ቤቱ የግብጽ ኮፕት ቤተ ክርስቲያን ፓትረያርክ፣ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ ፮ኛ በተገኙበት ተባረከ።

የቀዳሚ ሰማእት የቅዱስ እስጢፋኖስ ሞት ለክርስትና እምነት መስፋፋት ዋነኛ ምክንያት ነበር | የጽዮናውያንም እንዲሁ

እስጢፋኖስ — በግሪክ ቋንቋ አክሊል ማለት ነው። በግብሩ የቀን ሃሩር የሌሊት ቁር የማይለውጠው፣ መብራት ማለት ነው።

ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ የተቀዳጃቸው ሦስቱ አክሊላት፡

. ስለንፅህናው ስለድንግልናው

. ስለሰማዕትነቱ /ስለምስክሩ/ ስለተጋድሎው

. ስለስብከቱ /ስለትምህርቱ/ ስለተአምራቱ

ቅዱስ እስጢፋኖስ የተወገረበት ድንጋይ ሰባት አብያተ ክርስቲያናት ታንፆበታል። /ሰባት ቤተክርስቲያናትን አንጿል።/

የቤተክርስቲያን አባቶች የቀዳሜ ሰማዕት የቅዱስ እስጢፋኖስ ሞት ለክርስትና እምነት መስፋፋት ዋነኛ ምክንያት መሆኑ የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራውን እንድናይበት አድርጎናል ሲሉ ይገልፁታል እውነት ነውና።

_________________________________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

በመስቀሉ ኃይል ይህን የድቅድቅ ጨለማ ዘመን አልፈን ብርሃን የምናይበት ጊዜ ሩቅ አይደለም

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 27, 2021

✞✞✞መስቀል ኃይላችን ነው!✞✞✞

________________________________

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: