Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • March 2023
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    2728293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘Holy Spirit’

የቀድሞው ሙስሊም | መንፈስ ቅዱስ ልቤን ገርዞታል፥ ከሰይጣናዊው የእስልምና አምልኮ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 15, 2022

😈 የመሀመድ በሰይጣን ቁጥጥር ስር መውደቅ

መሀመድ ሰይጣን እንደያዘው ያስብ ነበር! ራሱን ለማጥፋትም ብዙ ጊዜ ሞክሯል!

ሙስሊሞች ሁሌም የሚሉት ነገር አለ እሱም “ቁራን የፈጣሪ ቃል ነው” የሚል ነው። ቁራን ግን ይህን አይመሰክርም። እንኳን የፈጣሪ ቃል ሊሆን ፀሀፊው መሀመድ እንኳ ሰይጣን ይዞት እራሱን ለማጥፋት ያስብ ነበር። ራዕይ ያየ እየመሰለውም የሰይጣንን ቃል እንደ ፈጣሪ ቃል ወስዶ ፅፏል።

እስቲ ሙስሊሞች ሳይሆኑ ቁራን ይንገረን!

ኢብን ይስሐቅ (ሲራ ረሱለላህ):-

መሀመድ በሰይጣን ቁጥጥር ስር የወደቀው እንዲህ ነበር፦

ጂብሪል የአላህን ትዛዝ ይዞለት መጣ! ተኝቼ እያለ መጣብኝና “አንብብ” አለኝ! እኔም “ምን ላንብብ” አልኩት! እርሱ ከላዬ ተኝኖ አስጨነቀኝ! የምሞትም መሰለኝ! ደግሞ ለቀቀኝና “አንብብ” አለኝ! እኔም “ምን ላንብብ” አልኩት! ሁለተኛ ጊዜ ከላዬ ተኝኖ አስጨነቀኝ! የምሞትም መሰለኝ!

ለሶስተኛ ጊዜ “አንብብ” አለኝ! እኔም “ምን ላንብብ” አልኩት! ለሶስተኛ ጊዜ “አንብብ” አለኝ! እኔም “ምን ላንብብ” አልኩት! እርሱም ለሶስተኛ ጊዜ ከላዬ ተኝኖ አስጨነቀኝ! የምሞትም መሰለኝ! ከዚያም አንብብ አለኝ! እኔም እንዳልሞት ብዬ “ከዚያ ብኋላስ ምን ላንብብ” አልኩት! እሱም “ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው በጌታህ ስም አንብብ” አለኝ!…

መሀመድ ሰይጣን ይዞት እራሱን ለማጥፋት ያስብ ነበር። ራዕይ ያየ እየመሰለውም የሰይጣንን ቃል እንደ ፈጣሪ ቃል ወስዶ ፅፏል

☪ ሙስሊሙ፦ “አንተ ከእኛ ሙስሊሞች የበለጠ ታውቃለህን? ሙስሊም እንድትሆን ያስገደደህ ሰው አለን?”

✞ ክርስቲያኑ፦ እኔ በፊት ሙስሊም ነበርኩ፤ እስልምናን ትቼው አሁን ክርስቲያን ነኝ፤ የኢየሱስ ክርስቶስ ክብሩ ይስፋ!

መሀመድ ለአቅመ ሔዋን ያልደረሰችውን አይሻን በስድስት ዓመቷ ነው ያገባት ሰውዬው አይሻን በጨቅላነቷ በማግባቱ በሙስሊሙ

ዓለም ለሚገኙት ብዙ ሕፃናት የሰቆቃ ምንጭ ሆኗል ይህ ህልም የመሀመድን የልብ ምኞት የሚገልፅ እንጂ የፈጣሪን ፈቃድ የሚያሳይ አይደለም፡፡ መሀመድ ፡ የእርሱን ምሳሌነት በመከተል ብዙ ሙስሊም ወንዶች ተመሳሳይ ተግባር ይፈፅማሉ፡፡ እንዲህ ያለውን አውዳሚ ተግባር በፈጣሪ ማሳበብ ትልቅ ድፍረት ነው!

የ53 ዓመቱ ጎልማሳ መሀመድ ከአይሻ ጋር በ 9 ዓመቷ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ፈጸመ ነገር ግን በሐዲሳቱ ውስጥ “በ 9 ዓመቷ ጋብቻውን አሟላ” በተባለው ውስጥ “አሟላ” (consummated) ።

ከሥጋ መገረዝ ሌላ በመንፈስ የሚደረግ የልብ መገረዝ እንዳለና ይህም እውነተኛው መገረዝ እንደሆነ ቢያስተምረንም (ሮሜ 2፣28-29 ቆላ 2፣11)፣

ኢየሱስ ክርስቶስ፤ የአማልክት አምላክ የጌቶች ጌታ፤ የነገስታት ንጉሥ፥ አልፋና ኦሜጋ፥ ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ የአለም ሁሉ ፈጣሪ ጌትዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ከእስልምና ሰይጣናዊ አምልኮ ነፃ አውጥቶኛል፤ ተወዳዳሪ የሌለው አባቴ ነው፤ ሙስሊም እያለሁ ተገርዤ ነበር፤ ግን ምንም ያመጣልኝ ነገር አልነበረም፤ አሁን በመንፈስ ቅዱስ ተገርዣለሁ፤ ልቤ በመንፈስ ቅዱስ ተገርዟል።

መንፈስ ቅዱስ ከሰይጣናዊው የእስልምና አምልኮ ነፃ አውጥቶኛል!

እስልምና፤ “ኢየሱስ ክርስቶስ፣ አልተወለደም፥ አልተሰቀለም፥ ሞቶ አልተነሳም፤ አምላክ አይደለም” ማለቱ፤ ሰይጣናዊ ቅጥፈት ነው!

______________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የጰራቅሊጦስ ድንቅ ተዓምር፤ ሰክሬአለሁ፤ ቃላት የለኝም!

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 11, 2022

😇 አዎ! ጰራቅሊጦስ ሐዋርያትን የወይን ጠጅ ሳይጠጡ እንዳሰከራቸውና በሀገሩ ሁሉ እንዳናገራቸው እኔም በእነዚህ ቀናት የሰከርኩ መስሎ ነው የተሰማኝ፤ ክርስቶስንና ቤተሰቦቹን በተመለከት ከብዙዎች ጋር በመነጋገር ላይ ነኝ፤ ሰው ሁሉ በበጎ እየቀረበኝ ነው። በእውነት ድንቅ ነው! በእውነት ጰራቅሊጦስ የሃይማኖትን አልጫነት የሚያጣፍጥ የልቡና ጨው ነው። ጰራቅሊጦስ በጭለማ ላሉ የሚያበራ የይቅርታ ብርሃን ነው።

  • ወደ ጸሎት ቤት ስገባ
  • ጸሎት ቤት ውስጥ

😇 ቅድስት እናታችንና ልጇ እግዚአብሔር ወልድ + የማርያም መቀነት + ክቡር መስቀል

ከጸሎት ቤት ስወጣ፤ ማረፊያ ወንበሩ ላይ፤ ይህን አየሁት። የሕፃን ልጅ መጫወቻ ነው፤

እንጠንቀቅ! ቀስተ ደመና የሰዶማውያን አይደለም! “ኬኛ!” ብለው ሊነጥቁን ግን ይሻሉ!

  • ከጸሎት ቤት ልክ ስወጣ ሜዳው ላይ ሰባት እርግቦችን አገኘሁ
  • ማታ ላይ ቤቴ እንደገባሁ መብራቱ ይህን ሠርቶ ነበር።
  • ጠዋት ላይ ደግሞ የእመቤታችን ሥዕል የማርያም መቀነትን ቤቴ ግርግዳ ላይ አንጸባርቆ ይታይ ነበር፤ ድንቅ ነው!

❖❖❖ እምዕርገት እስከ ጰራቅሊጦስ መዝሙር “በሰንበት ዐርገ ሐመረ” ❖❖❖

(በ፫/) በሰንበት ዐርገ ሐመረ ገሠፀ ባሕረ፤ ወገሠፆሙ ለነፋሳት፤ ወይቤሎሙ ኢትናፍቁ ወኢይምጻእ ኑፋቄ ውስተ ልብክሙ፤ በከመ ፈነወኒ አቡየ አነኒ እፌንወክሙ ውስተ ቤተ አቡየ ብዙኅ ማኅደር ቦቱ፤ ካዕበ እመጽእ ወእነሥአክሙ፤ ከመ ተሀልዉ ምስሌየ በመንግሥተ አቡየ ዘበሰማያት።

አመላለሰ

ከመ ተሀልዉ ምስሌየ በመንግሥተ አቡየ፤

በመንግሥተ አቡየ ዘበሰማያት።

ዓራራት

ትንሣኤሁ ገብረ በሰንበት ወሰበረ ኆኃተ ብርት እግዚአ ለሰንበት አመ ሣልስት ዕለት ምዖ ለሞት ወዓርገ ውስተ ሰማያት።

ሰላም

ወልድ እኁየ ውእቱ ፍቁርየ ውእቱ ተንሥአ እሙታን ገብረ ሰላመ ለኵሉ ዓለም ዓርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት ሎቱ ስብሐት ለዘቀደሳ ለሰንበት።

ዘቅዳሴ ምንባባት

  • ሮሜ ፲፥፩ ፡ ፍ፤
  • ፩ጴጥ ፫፥፲፭ ፡ ፍ፤
  • ግብ ፩፥፩ ፡ ፍ፤

ዘቅዳሴ ምስባክ፦

  • ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ፤
  • ወእግዚእነ በቃለ ቀርን፤
  • ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ። መዝ ፵፮፥፭

ወንጌል፦ ሉቃ ፳፬፥፵፭ ፡ፍ

ቅዳሴ ዘዲዮስቆሮስ (እምቅድመ ዓለም)

❖❖❖ /7 እርግቦች ❖❖❖

  • ሐዋሪያት ተባበሩ
  • በአዲስ ቋንቋ እየተናገሩ
  • ቃሉን አስተማሩ

❖ ፯ / ሰባት ፍጹም ቁጥር ነው

በቅዱስ መጽሐፍ አቆጣጠር ሰባት (፯) ፍጹምና ሙሉ ቁጥር በመሆኑ ከአንድ እስከ ሰባት ( ፩–፯ ) የተዘረዘሩት ምስጢራተ ቤተክርስቲያንም እንከንና ጉድለት የሌለባቸው ፍጹማን ናቸው።
ሰባት ቁጥር በመጽሐፍ ቅዱስ ሥርዓት ፍጹም ለመሆን ለማወቅ ከዚህ የሚከተሉትን ማስረጃዎች እንመልከት፦

❖ ሰባት ቁጥር ምስጢራት በቤተክርስቲያን፤

በመጽሐፍ ቅዱስና በስርዓተ ቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ ስባት ቁጥር ብዙ ምሳሌ እንዳለው ይታወቃል፡፡ በዕብራዊያን ዘንድም ሰባት ፍጹም ቁጥር ነው፡፡ ምሳሌ ፳፬፡፲፮ እግዚአብሔር ከሰኞ
እስከ እሑድ ያሉትን ቀናት በሰባት ቁጥሮች ወስኗል ሕዝበ እስራኤል ከግብጽ ባርነት ወጥተው በሲና በርሀ ሲጓዙ ይመሩት የነበሩት በ፯/7 ደመና እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ዘዳ ፲፫፡፳፩

ከዚህ ቀጥለንም ለቤተ-ክርስቲያን አስተምህሮ የ፯ ቁጥር ምስጢራትን ምሉዕነትን የሚያስረዱ ልዩ ልዩ ማስረጃዎችን በዝርዝር እንመለከታለን፦

❖ ሀ/ ሰባቱ አባቶች

፩. ሰማያዊ አባታችን እግዚአብሔር
፪. የነፍስ አባት
፫. ወላጅ አባት
፬. የክርስትና አባት
፭. የጡት አባት
፮. የቆብ አባት
፯. የቀለም አባት

❖ ለ/ ሰባቱ ዲያቆናት

፩. ቅዱስ እስጢፋኖስ
፪. ቅዱስ ፊልጶስ
፫. ቅዱስ ጵሮክሮስ
፬. ቅዱስ ጢሞና
፭. ቅዱስ ኒቃሮና
፮. ቅዱስ ጳርሜና
፯. ቅዱስ ኒቆላዎስ

❖ ሐ/ ሰባት የጌታ ቃላት /እኔ ነኝ

፩. የሕይወት እንጅራ እኔ ነኝ
፪. የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ
፫. እኔ የበጎች በር ነኝ
፬. መልካም እረኛ እኔ ነኝ
፭. ትነሣዔና ሕይወት እኔ ነኝ
፮. እኔ መንገድና ሕይወት ነኝ
፯. እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ

❖ መ/ ሰባቱ ሰማያት

፩. ጽርሐ አርያም
፪. መንበረ መንግሥት
፫. ሰማይ ውዱድ
፬. ኢየሩሳሌም ሰማያዊት
፭. ኢዮር
፮. ራማ
፯. ኤረር

❖ ሠ/ ሰባቱ ሊቃነ መላእክት

፩. ቅዱስ ሚካኤል
፪. ቅዱስ ገብርኤል
፫. ቅዱስ ሩፋኤል
፬. ቅዱስ ራጉኤል
፭. ቅዱስ ዑራኤል
፮. ቅዱስ ፋኑኤል
፯. ቅዱስ ሳቁኤል

❖ ረ/ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት

፩. የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን
፪. የሰርምኔስ ቤተ ክርስቲያን
፫. የጴርጋሞን ቤተ ክርስቲያን
፬. የትያጥሮስ ቤተ ክርስቲያን
፭. የሰርዴስ ቤተ ክርስቲያን
፮. የፊልድልፍያ ቤተ ክርስቲያን
፯. የሎዶቅያ ቤተ ክርስቲያን

❖ ሰ/ ሰባቱ ተዐምራት

ጌታ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈጸሙ ተዐምራት

፩. ፀሐይ ጨልሟል
፪. ጨረቃ ደም ሆነ
፫. ከዋክብት ረገፉ
፬. ዐለቶች ተሠነጠቁ
፭. መቃብራት ተከፈቱ
፮. ሙታን ተነሡ
፯. የቤተ መቅደስም መጋረጃ

❖ ሸ/ ሰባቱ የመስቀሉ ቃላት

፩. አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ
፪. አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው
፫. ዛሬ ከእኔ ጋራ በገነት ትሆናለህ
፬. እነሆ ልጅሸ እናትህ እነሆት
፭. ተጠማሁ
፮. ተፈጸመ
፯. አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እስጥሃለሁ

❖ ቀ/ ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን

፩. ምሥጢረ ጥምቀት
፪. ምሥጢረ ሜሮን
፫. ምሥጢረ ቁርባን
፬. ምሥጢረ ክህነት
፭. ምሥጢረ ተክሊል
፮. ምሥጢረ ንስሐ
፯. ምሥጢረ ቀንዲል

❖ በ/ ሰባቱ ዐበይት አጽዋማት

፩. ዐቢይ ጾም
፪. የሐዋርያት ጾም
፫. የፍልሰታ ጾም
፬. ጾመ ነቢያት
፭. ጾመ ገሀድ
፮. ጾመ ነነዌ
፯. ጾመ ድኅነት

ተ/ ሰባቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠሉ ነገሮች

፩. ትዕቢተኛ ዓይን ምሳ ፲፮፥፮፡፲፱
፪. ሃሰተኛ ምላስ
፫. ንፁህን ደም የምታፈስ እጅ
፬. ክፉ ሃሳብን የምታፈልቅ ልብ
፭. ለክፋት የምትፈጥን እጅ
፮. የሐሰት ምስክርነት
፯. በወንድሞች መካከል ጠብን የምታፈራ ምላስ

❖ ቸ/ ሰባቱ ፀሎት ጊዜያት

፩. ነግህ የጠዋት ጸሎት
፪. ሠለስት (የ፫ ሰዓት ጸሎት)
፫. ቀትር (የ፮ ሰዓት ጸሎት)
፬. ተሰአቱ (የ፱ ሰዓት ጸሎት)
፭. ሰርክ (የ፲፩ ሰዓት ጸሎት)
፮. ነዋም (የመኝታ ጸሎት)
፯. መንፈቀ ሌሊት (የሌሊት ጸሎት)

______________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የጥምቀት ተዓምር | ኦርቶዶክስ ሩሲያ እና ዩክሬን ወደ ጦርነት ሲያመሩ ፥ ርግቧ እንደ መንፈስ ቅዱስ ወረደች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 23, 2022

💭 ይህ ተዓምር የተከሰተው በዩክሬን ኦርቶዶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ወቅት ባለፈው የጌታችን የጥምቀት በዓል ዕለት ጥር ፲፩/፳፻፳፪ ዓ.ም ነበር።

😈 ልክ የኦሮሞው ቍራ አማራ እና ተጋሩ ኦርቶዶክስ ወንድማማቾችን እንደሚያባላቸው ፥ የኤዶማውያኑ ቍራም የሩሲያንና ዩክሬንን ኦርቶዶክስ ወንድማማቾችን ለጦርነት ዳርጓቸዋል

[መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፮፥፲፮]

እግዚአብሔር የሚጠላቸው ስድስት ነገሮች ናቸው፥ ሰባትንም ነፍሱ አጥብቃ ትጸየፈዋለች፤ በሐሰት የሚናገር ሐሰተኛ ምስክር በወንድማማች መካከልም ጠብን የሚዘራ…”

_______________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ጰ ፦ ብሂል ጰራቅሊጦስ መንፈሰ ጽድቅ ፥ ጰራቅሊጦስ እውነተኛ መንፈስ ቅዱስ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 20, 2021

❖❖❖ እንኳን ለበዓለ ጰራቅሊጦስ አደረሰን!❖❖❖

ጰራቅሊጦስ የሚለው ቃል ከሦስቱ አካላት አንዱ የኾነው የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ስም ሲኾን፣ ትርጕሙም በጽርዕ (ግሪክ) ቋንቋ፦

❖ ናዛዚ (የሚናዝዝ)

❖ መጽንዒ (የሚያጸና)

❖ መስተፍሥሒ (የሚያስደስት) ማለት ነው።

መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት በወረደበት ዕለት በቤተ ክርስቲያን የሚከበረው ይህ በዓል ‹በዓለ ጰራቅሊጦስ› ወይም ‹በዓለ ጰንጠቆስጤ› በመባል ይታወቃል። ‹ጰንጠቆስጤ› በግሪክ ቋንቋ በዓለ ኀምሳ፣ የፋሲካ ኀምሳኛ ዕለት፣ በዓለ ሠዊት (የእሸት፣ የመከር በዓል) ማለት ነው (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፱፻፮-፱፻፯)።

ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ዐሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት፣ ሰባ ሁለቱ አርድእት፣ አምስት መቶው ባልንጀሮች እና ሠላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አንስት በኢየሩሳሌም ከተማ በአንድነት ኾነው በጸሎት ይተጉ ነበር።

ጌታችን በሚያርግበት ጊዜ “እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ፤” ሲል ለሐዋርያቱ በሰጣቸው የተስፋ ቃል መሠረት በዐረገ በዐሥረኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል (ሉቃ. ፳፬፥፵፱)። ዅሉም በአንድ ቦታ ተሰባስበው ሳሉ በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማለዳ እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ድንገት ከሰማይ ወርዶ የነበሩበትን ቤት ሞላው። ከዚያም የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎች በዅሉም ላይ አረፉባቸው። በዚህ ጊዜ ዅላቸውም መንፈስ ቅዱስ ባደላቸው መጠን በየአገሩ ቋንቋዎች ዅሉ ተናገሩ (ሐዋ.፪፥፩-፬)።

ጌታችን መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት የላከበት ይህ ዐቢይ በዓል ዐሥራቱን፣ በኵራቱን፣ ቀዳምያቱን ካህናተ ኦሪት ስለሚቀበሉበት በብሉይ ኪዳን በዓለ ሠዊት ተብሎ ይከበር ነበር። በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ስለ ተቀበሉበት በበዓለ ሠዊት ምትክ በዓለ ጰራቅሊጦስ ገብቶበታል። የበዓለ ትንሣኤ መነሻው የአይሁድ የፋሲካ በዓል ማለትም በግብጽ፣ እስራኤል ከሞት የዳኑበት የመታሰቢያ በዓል እንደ ኾነው ዅሉ፣ ለበዓለ ጰራቅሊጦስም መነሻው ይኸው የአይሁድ የፋሲካ በዓል ነው። የአይሁድ ፋሲካ ከተከበረ ከሰባት ሳምንታት በኋላ በኀምሳኛው ቀን የሩቆቹ ከከተሙበት ወጥተው፣ የቅርቦቹ ከተሰባሰቡበት ተገናኝተው ለበዓሉ ፍጻሜ የሚኾነውን በዓለ ሠዊት (የእሸት በዓል) ያከብሩ ነበር።

ሐዋርያት በጽርሐ ጽዮን ተሰባስበው ሳሉ መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል ወርዶ ሰማያዊ ሀብትን፣ ዕውቀትና ጸጋን አድሏቸዋል። መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላም በአእምሮ ጐልምሰዋል፤ ጥቡዓን (ቈራጦች)፣ ጽኑዓን ኾነዋል፤ ለስብከተ ወንጌል የሚፋጠኑበትንና ለሰማዕትነት የሚዘጋጁበትን ልቡና ታድለዋል።

ቅድስት በኾነች በጽርሐ ጽዮን በሐዋርያት ላይ የወረደው የእግዚአብሔር አብ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር ወልድ ፍቅር፣ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አንድነት በዅላችን ላይ ይደር፤ እጽፍ ድርብም ይኹን

______________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የቀን ጅቦች (የግራኝ ሰአራዊት) ንጉሥ አንበሣን (አክሱም ጽዮንን) ከብበው አጠቁት ከዚያ…

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 19, 2021

የአባ ዘ-ወንጌልን መልዕክት የ666ቱ ጭፍሮች ለራሳቸው አጀንዳ ያመቻቸው ዘንድ እንዳሰኛቸው ጠምዝዘው ሲያቀርቡት ይታያሉ። 👉 አባታችን አባ ዘ-ወንጌል የሚከተለውን መልዕክት አስተላልፈዋል በማለት ጉዳዩን እነ ዘመድኩን በቀለ ለተከታዮቻቸው በተደጋጋሚ ሲያወሱት ነበር። ስለ አባ ዘ-ወንጌል የተወራው ሁሉ ትክክል አይደለም የማለት ድፍረት የለኝም፤ ሆኖም እራሳችንን መጠየቅ ያለብን፤ “እባቡ ግራኝ አብዮት አህመድና እንደ ጋንኤል ክስረት እና ገመድኩን ሰቀለ ያሉት ካድሬዎቹ ተዋሕዶ ክርስቲያኑን የትግራይን ሕዝብ ለመጨፍጨፍ አስቀድመው ያወጡት ጽሑፍ/ስክሪፕት ቢሆንስ? “የራሳችሁ አባት አባ ዘ-ወንጌል የተነበዩት ነውና ጭፍጨፋውንም፣ የዓብያተ ክርስቲያናትና ገዳማቱን ውድመትም ተቀበሉ፤ በሃጢአታችሁ ነውና፤ አሁን ለደህንነታችሁና ብልጽግናችሁ ስትሉ በሉ ጴንጤ ሁኑ” ብለው ተንኮለኛው ፈላስፋ ጆርጅ ሄገል ያረቀቀላቸውን “ችግር – ምላሽ – መፍትሔ / “Problem – Reaction – Solutionየተባለውን መመሪያ ተከትለው ቢሆንስ? መቼስ ይህን እንደሚያደርጉት አልጠራጠረም።

💭 አባ ዘ-ወንጌል ‘አስተላልፈውታል’ የተባለው መልዕክት እንዲህ ይላል፦

በአራቱም አቅጣጫ ኢትዮጵያ ትወረራለች። ሰላም በማስከበር በሚል ሰበብም በ፪/2 ሃያላን ሀገራት የሚመሩ ሰባት የሙስሊም ሀገራት በኢትዮጵያ ምድር ላይ እሳት ያዘንባሉ። በአሰብ ወደብ ላይ በልዩ ሁኔታ የተከማቸው የጦር መሣሪያ በኢትዮጵያ ምድር ላይ እንደበረዶ ይዘንባል። ብዙ ፍጅትም ይሆናል። ኦርቶዶክሳውያን በያሉበት፣ በየተገኙበት እንደከብት ይታረዳሉ። የኢትዮጵያ ምድር በደም ትጨቀያለች። የደም ጎርፍ፣ የደም አበላ በምድሪቱ ላይ ይፈሳል።”

👉 ሰባቱ የሙስሊም ሀገራት እነ ግራኝ ትግራይን ለመጨፍጨፍ ገና ከሦስት ዓመታት በፊት የሰበሰቧቸው እነዚህ የጅቦች መንጋ ሰራዊት አይደሉምን?

🔥 አማራ

🔥 ኦሮሞ

🔥 መናፍቅ

🔥 እስላም/አረብ

🔥 ኤርትራ

🔥 ሶማሊያ

🔥 ብሔር ብሔረሰቦች

የይሁዳ አንበሣን (አክሱም ጽዮን)ከብበው አጠቁት፤ በመጨረሻም ረዳቱ/ረዳታችን (መንፈስ ቅዱስ) ደረሰለት። ነጫጮቹን እርግቦች አየናቸው?

ያዘው! በለው! ስቀለው!”ሲሉ የነበሩት መቶ ጅቦች ፈረጠጡ! ሦስቱ አንበሦች ግን አንድ ሆነው ንጉሥነታቸውን አረጋገጡ!

ዲያብሎስ የአክሱም ጽዮን ልጆች የእርሱ አለመሆናቸውን ቆጭቶት እነርሱን ለመጣል ብሎ ለዘመናት በተለያየ መንገድ ተፈታተናቸው[ማቴ.፬፥፫]፡፡ ጌታችንን ከሀገራቸው እንዲሄድላቸውና ወደ ግብጽ እንዲሰደድ እንደ ለመኑት፤ የአክሱም ጽዮን ልጆችንም የክርስቶስ በመሆናቸው ከሀገራቸው እንዲወጡላቸው እያደረጓቸው ነው፤(ማቴ.፰፥፴፬)፡፡ የይሑዳ አንበሣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን “ጋኔን አለበት”(ሎቱ ስብሐት!)እንዳሉት ለአክሱም ጽዮን ልጆችም የተለያየ ስም እየሰጧቸው በመጥፎ እና በጠላትነት እንዲታዩ አደረጓቸው፤[ዮሐ.፲፥፳]፡፡ የይሑዳን አንበሣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በቅንዓት ተነሣሥተው “ይሰቀል ይሰቀል” እንዳሉት፤ እንደዚሁ የክርስቶስ ተቃዋሚው የግራኝ አህመድ የአህዛብ አገዛዝም በተለያየ መንገድ አመካኝቶ ግርግር አንሥቶ፣ መነሻውም ሰሜን ዕዝ እንደ ሆነ ዋሽቶ መንጋ ተከታይ መንጋውን “ያዘው! በለው! ይወገሩ፣ ይቀጥቀጡ! ግደላቸው!” እያስባለ የአክሱም ጽዮን ልጆች የክርስቶስ በመሆናቸው ብቻ እግዚአብሔር በሰጣቸው ምድር ገረፏቸው፣ ደፈሯቸው፣ አስራቧቸው፣ ጨፈጨፏቸው[ማቴ.፳፯፥፳፪፡፳፫]፡፡

ገና ከልጅነታችን በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠምቀን ክርስቲያን የሆንን ሁሉ ከእኛ ጋር ያለውን፣ “በኪሳችን የያዘነውን” ተንከባክበን ወደ ውስጥ ከተመለከትን ከውጭ ያለውና አላፊና ሰብዓዊ ከሆነው እርዳታ መጠበቅ አይገባንም/ አያስፈልገንም። ይህ ሰው፣ ይህ ሕዝብ፣ ይህ ተቋምና ድርጅት ለምን ስለኛ መከራ እና ሰቆቃ አልተናገረልንም? ለምንስ ለእርዳታ ከእኛ ጋር አልቆሙልንም? እያልን እራሳችንን የሚያጽናናን፤ ማለትም የሚያጽናን፣ የቅርብ ረዳታችን፣ የመንገዳችን ደጋፊ፣ የነፍሳችንን ሲቃ አዳማጭና የማይለይ ታዳጊ መንፈስ ቅዱስ ሁሌ ከእኛ ጋር አለና ነው። መንፈስ ቅዱስ በማይመረመር ፍርዱ የደሀን ደም ይበቀላል፣ ፍትሕን ይተክላል፣ እውነትን ያነግሳል፣ ሀሰትን ይደመስሳል፣ በኃጢአት የከበሩትን ያዋርዳል፣ ስለጽድቅ የተዋረዱትን ግን ያከብራል።

[የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፲፬፥፳፮]

አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።”

✞✞✞የሐና ማርያም ወራዊ መታሰቢያ በዓል✞✞✞

[መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ ምዕራፍ ፪]

፩ ሐናም ስትጸልይ እንዲህ አለች። ልቤ በእግዚአብሔር ጸና፥ ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ፤ አፌ በጠላቶቼ ላይ ተከፈተ፤ በማዳንህ ደስ ብሎኛል።

፪ እንደ እግዚአብሔር ቅዱስ የለምና፥ እንደ አምላካችንም ጻድቅ የለምና፤ ከአንተ በቀር ቅዱስ የለም።

፫ አትታበዩ፥ በኩራትም አትናገሩ፤ እግዚአብሔር አዋቂ ነውና፥ እግዚአብሔርም ሥራውን የሚመዝን ነውና፥ ከአፋችሁ የኵራት ነገር አይውጣ።

፬ የኃያላንን ቀስት ሰብሮአል፥ ደካሞችንም በኃይል ታጥቀዋል።

፭ ጠግበው የነበሩ እንጀራ አጡ፤ ተርበው የነበሩ ከራብ ዐርፈዋል፤ መካኒቱ ሰባት ወልዳለችና፥ ብዙም የወለደችው ደክማለች።

፮ እግዚአብሔር ይገድላል ያድናልም፤ ወደ ሲኦል ያወርዳል፥ ያወጣል።

፯ እግዚአብሔር ድሀ ያደርጋል፥ ባለጠጋም ያደርጋል፤ ያዋርዳል፥ ደግሞም ከፍ ከፍ ያደርጋል።

፰ ከሕዝቡ መኳንንት ጋር ያስቀምጣቸው ዘንድ፥ የክብርንም ዙፋን ያወርሳቸው ዘንድ፥ ችግረኛውን ከመሬት ያስነሣል፥ ምስኪኑንም ከጉድፍ ያስነሣል፤ የምድር መሠረቶች የእግዚአብሔር ናቸውና፥ በእነርሱ ላይም ዓለምን አደረገ።

፱ እርሱ የቅዱሳኑን እግር ይጠብቃል ኃጥኣን ግን ዝም ብለው በጨለማ ይቀመጣሉ፤ ሰው በኃይሉ አይበረታምና።

፲ ከእግዚአብሔር ጋር የሚጣሉ ይደቅቃሉ፤ በሰማይም ያንጐደጕድባቸዋል፤ እግዚአብሔር እስከ ምድር ዳርቻ ይፈርዳል፤ ለንጉሡም ኃይል ይሰጣል፤ የመሲሑንም ቀንድ ከፍ ከፍ ያደርጋል።

_______________________________________

Posted in Ethiopia, Faith, Infos, Life | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

መታየት ያለበት | ከኢየሱስ ክርስቶስ የመጣልንን መንፈስ ቅዱስ ያገኘንበት የመጀመሪያው ቤተክርስቲያን ይህ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 26, 2018

ይህ የሚመስጥና የሚያስለቅስ ታሪክ ነው።

ክርስትና እዚህ ቦታ ላይ ነው የተወለደው! ጰራቅሊጦስ ወይም ጰንጠቆስጤ ዕለት ከኢየሱስ ክርስቶስ የመጣልንን መንፈስ ቅዱስ ያገኘነው እዚህ ቦታ ላይ ነው።

በዓለም በጣም አስፈላጊ/ ተፈላጊ ከሆኑት ቦታዎች መካከል አንዱ ይህ ነው።

በዓለም የመጀመሪያው የቤ/ ክርስቲያን ህንፃ በጽዮን ተራራ ድብቅ በሆነ ቦታ መሬት ሥር ውስጥ ተቀብሮ ነው የሚገኘው።

በእየሩሳሌም የሚገኘው ይህ እጅግ በጣም ታሪካዊ ቦታ በግሪክ ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስቲያን ቁጥጥር ሥር ነው።

በዚህ ቅዱስ ቦታ፡ ልክ በኢየሱስ ዘመን እንደነበረው አሁንም በተከታዮቹ ላይ በደል ሲደርስባቸው

ማየቱ በጣም የሚያስገርም ነገር ነው።

ከ ሮማውያን ወታደሮች ለማምለጥ መሬት ውስጥ ተደብቀው ነበር ጸሎት ሲያደርጉ የነበረው። (ልክ እንደ ላሊበላ ዓብያተክርስቲያናት)

/ ያዕቆብ የመጀመሪያዋ የዚህች ቤ/ክርስቲያን ሐዋርያ ነበር።

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደዚህ ቤተክርስቲያን ትመጣ ነበር።

ኢየሱስ የ ያዕቆብ ወንድም ነበር። ያዕቆብ የኢየሱስን ትንሣኤ ካየ በኋላ አመነ፡ ከዚያም የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን ሐዋርያ ለመሆን በቃ።

የመጀማሪያዎቹ ክርስቲያኖች በ44 .ም አካባቢ ለሮማውያኑ ህገ ወጥ ነበሩ፡ ስለዚህ ያሳድዷቸውና ይበድሏቸው ነበር። ለዚህም ነበር በመሬት ውስጥ ተደብቆ እንዲሠራ የተደረገው።

በዚህም ዘመን ቢሆን ቤተክርስቲያኑ ታሥሯል፤ ልክ በኢየሩሳሌም እንዳለው፡ ወይም በአገራችንም እንዳሉት ገዳማትና ቅዱሳን ቦታዎቻችን፡ ይህም ቤተክርስቲያን አሁንም ድረስ ፈተናዎች ይበዙበታል። የቤተክርስቲያኑን በር ለመክፈት እንኳን ልዩ ፈቃድ ያስፈልጋል፤ ለጎብኚዎች ዝግ ነው፣ ማደስና መጠገንም አይፈቀድም። እንዲያውም ጽንፈኛ የሃይማኖት አክራሪዎች ወደዚያ እየሄዱ፡ በመስክቶት በኩል፡ ውስጥ ድረስ ቆሻሻ ይደፉበታል። ፀረክርስቶሱ ነው ኢየሩሳሌምንም የሚቆጣጠራትና።

ልክ በኢየሱስ ዘመን እንደነበረው አሁንም በተከታዮቹ ላይ በደል ሲደርስባቸው ማየቱ በጣም የሚገርም ነገር ነው።

በእውነትም፡ ይህ የሚያነቃቃና የሚመስጥ ድንቅ ቦታ ነው።

ይህ የመጀመሪያው ቤ/ ክርስቲያን የመጨረሻው ቤ/ ክርስቲያን ይሆንን?

እግዚአብሔር መንፈስ በሰው ላይ አድሮ ጥበብን ይገልጣል

ጰራቅሊጦስ የሚለው ቃል ከሦስቱ አካላት አንዱ የኾነው የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ስም ሲኾን፣ ትርጕሙም በጽርዕ (ግሪክ) ቋንቋ

  • ናዛዚ (የሚናዝዝ)
  • መጽንዒ (የሚያጸና)
  • መስተፍሥሒ (የሚያስደስት) ማለት ነው፡፡

መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት በወረደበት ዕለት በቤተ ክርስቲያን የሚከበረው ይህ በዓል ‹በዓለ ጰራቅሊጦስ› ወይም ‹በዓለ ጰንጠቆስጤ› በመባል ይታወቃል፡፡

በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት የተማረኩ አሕዛብም ‹‹ምን እናድርግ?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ከክፋታቸው ተመልሰው፣ ንስሐ ገብተው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንዲጠመቁ ነገሯቸዋል፡፡ በዚያችም ሰዓት ሦስት ሺህ ሕዝብ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ ተጠምቋል (ሐዋ.፪፥፩፵፩)፡፡

አዳምና ልጆቹን ከዲያብሎስ ተገዢነት እና ከሲኦል ባርነት ያወጣው ቸሩ መድኃኔ ዓለም የወደቁትን ወገኖቻችን ያንሳቸው፣ ጰራቅሊጦስንም ያውርድላቸው።

እንኳን አደረሰን!

______

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

በዓለ ጰራቅሊጦስ | የእግዚአብሔር መንፈስ በሰው ላይ ሲያድር ጥበብን ይገልጣል በአእምሮ ያጐለምሳል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 3, 2017

በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው: ግንቦት ፳፮ ቀን ፳፻፱ ዓ.

ጰራቅሊጦስ የሚለው ቃል ከሦስቱ አካላት አንዱ የኾነው የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ስም ሲኾን፣ ትርጕሙም በጽርዕ (ግሪክ) ቋንቋ

  • ናዛዚ (የሚናዝዝ)
  • መጽንዒ (የሚያጸና)
  • መስተፍሥሒ (የሚያስደስት) ማለት ነው፡፡

መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት በወረደበት ዕለት በቤተ ክርስቲያን የሚከበረው ይህ በዓል ‹በዓለ ጰራቅሊጦስ› ወይም ‹በዓለ ጰንጠቆስጤ› በመባል ይታወቃል፡፡ ‹ጰንጠቆስጤ› በግሪክ ቋንቋ በዓለ ኀምሳ፣ የፋሲካ ኀምሳኛ ዕለት፣ በዓለ ሠዊት (የእሸት፣ የመከር በዓል) ማለት ነው (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፱፻፮፱፻፯)፡፡

ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ዐሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት፣ ሰባ ሁለቱ አርድእት፣ አምስት መቶው ባልንጀሮች እና ሠላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አንስት በኢሩሳሌም ከተማ በአንድነት ኾነው በጸሎት ይተጉ ነበር፡፡ ጌታችን በሚያርግበት ጊዜ ‹‹እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ፤›› ሲል ለሐዋርያቱ በሰጣቸው የተስፋ ቃል መሠረት በዐረገ በዐሥረኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል (ሉቃ. ፳፬፥፵፱)፡፡ ዅሉም በአንድ ቦታ ተሰባስበው ሳሉ በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማለዳ እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ድንገት ከሰማይ ወርዶ የነበሩበትን ቤት ሞላው፡፡ ከዚያም የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎች በዅሉም ላይ አረፉባቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ዅላቸውም መንፈስ ቅዱስ ባደላቸው መጠን በየአገሩ ቋንቋዎች ዅሉ ተናገሩ (ሐዋ.፪፥፩)፡፡

ጌታችን መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት የላከበት ይህ ዐቢይ በዓል ዐሥራቱን፣ በኵራቱን፣ ቀዳምያቱን ካህናተ ኦሪት ስለሚቀበሉበት በብሉይ ኪዳን በዓለ ሠዊት ተብሎ ይከበር ነበር፡፡ በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ስለ ተቀበሉበት በበዓለ ሠዊት ምትክ በዓለ ጰራቅሊጦስ ገብቶበታል፡፡ የበዓለ ትንሣኤ መነሻው የአይሁድ የፋሲካ በዓል ማለትም በግብጽ፣ እስራኤል ከሞት የዳኑበት የመታሰቢያ በዓል እንደ ኾነው ዅሉ፣ ለበዓለ ጰራቅሊጦስም መነሻው ይኸው የአይሁድ የፋሲካ በዓል ነው፡፡ የአይሁድ ፋሲካ ከተከበረ ከሰባት ሳምንታት በኋላ በኀምሳኛው ቀን የሩቆቹ ከከተሙበት ወጥተው፣ የቅርቦቹ ከተሰባሰቡበት ተገናኝተው ለበዓሉ ፍጻሜ የሚኾነውን በዓለ ሠዊት (የእሸት በዓል) ያከብሩ ነበር፡፡

ከግብጽ እስከ ከነዓን ምድር የደረሰው የእንስሳት መሥዋዕት ሲጠናቀቅ በኀምሳኛው ቀን ይሰባሰብ የነበረው የአይሁድ ጉባኤም መንፈስ ቅዱስ ከወረደበት ዕለት ጀምሮ ተበትኗል፡፡ መሥዋዕተ ኦሪቱ በአማናዊው መሥዋዕት በኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋና ደም እንደ ተለወጠ ዅሉ ጉባኤ አይሁድም በኢየሩሳሌም ከተማ በተሰበሰቡ በቅዱሳን ሐዋርያት ጉባኤ ተለውጧል (ተቀይሯል)፡፡ ይህችውም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ከጉባኤያት ዅሉ ከፍ ከፍ ያለች የመንፈስ ቅዱስ ቤት ናትና፡፡ ‹‹ከዅሉ በላይ በምትኾን፣ ሐዋርያት በሰበሰቧት፣በአንዲት፣ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን፤›› እንዳሉ ሠለስቱ ምእት በጸሎተ ሃይማኖት፡፡

ሐዋርያት በጽርሐ ጽዮን ተሰባስበው ሳሉ መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል ወርዶ ሰማያዊ ሀብትን፣ ዕውቀትና ጸጋን አድሏቸዋል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላም በአእምሮ ጐልምሰዋልጥቡዓን (ቈራጦች)፣ ጽኑዓን ኾነዋል፤ ለስብከተ ወንጌል የሚፋጠኑበትንና ለሰማዕትነት የሚዘጋጁበትን ልቡና ታድለዋል፡፡ ቀድሞ ይናገሩት ከነበሩት ቋንቋ በተጨማሪ ፸፩ ቋንቋዎች ተገልጠውላቸው ምሥጢራትን በልዩ ልዩ ቋንቋ መተርጐም ጀምረዋል፡፡ ሐዋርያት በየገአሩ ቋንቋ ሲናገሩ የሰሙ በዚያ የነበሩ ሰዎችም በሐዋርያት ተገረሙ፡፡ አንዳንድ የአይሁድ ወገኖች ግን በሐዋርያት ላይ ያዩት ክሥተት አዲስ ነገር ስለኾነባቸው ‹‹ጉሽ ጠጅ ጠጥተው ሰክረው የኾነ ያልኾነውን ይቀባጥራሉ›› እያሉ ሐዋርያትን ያሟቸው ነበር፡፡

ቅዱስ ጴጥሮስም ይህንን ዐሳባቸውን በመንፈስ ቅዱስ አውቆ ‹‹ሰክረዋል የምትሉ

እናንተ እንደምትጠራጠሩት አይደለም፡፡ ጊዜው ማለዳ፣ ሰዓቱም ገና ሦስት ሰዓት ነውና፡፡ ዳሩ ግን በነቢዩ ኢዩኤል ‹ከዚህም በኋላ እንዲህ ይኾናል፤ መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ዅሉ ላይ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ› (ኢዩ.፪፥፳፰) ተብሎ የተነገረው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ፣ ይህንን ድንቅ ተአምር ያደረገው እናንተ የሰቀላችሁት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤›› በማለት ሰፊ ትምህርተ ወንጌል ሰጥቷቸዋል፡፡

በትምህርቱም ነቢያት ትንቢት የተናገሩለት፣ ምሳሌ የመሰሉለት አምላክ ወልደ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ መነሣቱን፣ ማረጉንና ዳግም በክብር በምስጋና መጥቶ በሕያዋንና በሙታን ላይ የሚፈረድ መኾኑን ሐዋርያት እንደሚመሰክሩ በአይሁድ ፊት አሰምቶ ተናገረ፡፡ በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት የተማረኩ አሕዛብም ‹‹ምን እናድርግ?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ከክፋታቸው ተመልሰው፣ ንስሐ ገብተው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንዲጠመቁ ነገሯቸዋል፡፡ በዚያችም ሰዓት ሦስት ሺህ ሕዝብ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ ተጠምቋል (ሐዋ.፪፥፩፵፩)፡፡

ቅዱሳን ሐዋርያት፡– ‹‹በዚህች ቀን በሦስት ሰዓት ኢየሱስ ክርስቶስ ጰራቅሊጦስን ልኮልናልና በላያችን ኃይልን ሞላ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ በሕያዋንና በሙታን ይፈርድ ዘንድ ሥልጣን እንዳለው በአዲስ ቋንቋ ተናገርን፤›› በማለት በዕለቱ ያዩትንና የተደረገላቸውን፣ እንደዚሁም የበዓሉን ታላቅነት ከመሰከሩ በኋላ ይህንን በዓል ማክበር እንደሚገባ አዝዘዋል፤ በዚህ ወቅት መጾምና ማዘን ተገቢ አለመኾኑንም ተናግረዋል (ዲድስቅልያ ፴፥፴፰፴፱፤ ፴፩፥፷፱)፡፡

ከዚህ ላይ ማስተዋል የሚገባን ቁም ነገር ‹መንፈስ ቅዱስ ወረደ› ሲባል፣ በሰዉኛ ቋንቋ መንፈስ ቅዱስ ከከፍታ ወደ ዝቅታ፣ ከሩቅ ወደ ቅርብ መምጣቱን ወይም መምጣቱን ለመናገር አይደለም፡፡ የእግዚአብሔር መንፈስ በሐዋርያት ላይ አድሮ ሰማያዊ ሀብትን፣ ዕውቀትን፣ ጥበብንና ልዩ ልዩ ጸጋን ማደሉን ለማስረዳት ነው እንጂ፡፡ ይኸውም ሥራዉን በሰው ላይ መግለጡን፣ ጸጋዉንም ማብዛቱን ለማመልከት የሚያገለግል ቋንቋ ነው፡፡ ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ ወረደ የሚለው ትምህርት መንፈስ ቅዱስን በቦታ፣ በጊዜና በወሰን መገደቡን አያመለክትም፡፡ የእግዚአብሔር መንፈስ በዓለሙ ዅሉ የሞላ ነውና፡፡ በሰው ላይ አድሮ ጥበብን ሲገልጥ ግን ‹ሞላ፤ አደረ፤ ወረደ› ተብሎ ይነገራል፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ለጊዜው ለሐዋርያት ቢሰጥም፣ በእነርሱ ላይ ብቻ ሳይገደብ እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ በምእመናን ላይም አድሮ ይኖራልና፡፡

በዓለ ትንሣኤውን በደስታ እንድናሳልፍ ፈቅዶ እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ጠበቀን፣ አሁን ደግሞ በጾም፣ በጸሎት ኾነን እርሱን የምናመሰግንበትን ወቅት ስላመጣልን አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ለዘለዓለሙ የተመሰገነ ይኹን፡፡

የዘመነ ጰራቅሊጦስ ምንባባት

በዓለ ጰራቅሊጦስ ሀብተ መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት የተሰጠበት፤ ብዙ ሺሕ ምእመናን የሥላሴን ልጅነት ያኙበት ዕለት በመኾኑ ‹የቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን› ተብሎ ይጠራል፡፡ በዓሉ ከዘጠኙ የጌታችን ዐበይት በዓላት አንዱ ሲኾን፣ በያዝነው ዓመትም ግንቦት ፳፯ ቀን ይዘከራል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከወረደበት ሰንበት (ከኀምሳኛው ቀን) ጀምሮ እስከሚቀጥለው ሰንበት ያለው ጊዜም (ስምንቱ ቀናት) ‹ዘመነ ጰራቅሊጦስ› ወይም ‹ሰሙነ ጰራቅሊጦስ› ይባላል፡፡ ይህም መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ ስለ መውረዱና በምእመናን ላይ ስለ ማደሩ የሚነገርበት ወቅት ነው፡፡ በዚህ ሰሙን በቤተ ክርስቲያን የሚነገረው ቃለ እግዚአብሔር፣ የሚሰጠውም ትምህርት የመንፈስ ቅዱስን በሐዋርያት ላይ መውረድ የሚመለከት ነው፡፡

በበዓለ ጰራቅሊጦስ ዕለት ‹ይትፌሣሕ› የሚለው የትንሣኤ መዝሙር በቤተ ክርስቲያን ይዘመራል፡፡ በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ የቅዱሳት መጻሕፍት ክፍሎችም በትንሣኤ ዕለት የተነበቡት ናቸው፡፡ ምንባባቱ ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ በመነሣቱ፣ በማረጉና መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት በመላኩ፤ እንደዚሁም ሥጋውን ቈርሶ፣ ደሙን አፍስሶ የሰውን ልጅ ከዘለዓለም ሞት በማዳኑ የሰው ዘር ብቻ ሳይኾን የሰማይ መላእክት፣ የምድር ፍጥረታት ሳይቀሩ ሐሤት እንደሚያደርጉ፤ ምድርም በክርስቶስ ደም በመንጻቷ የጌታችንን ትንሣኤ በደስታ እንደምታከብር የሚያስረዳ መልእክት አላቸው፡፡

ከበዓለ ጰራቅሊጦስ በኋላ ባሉት ሰንበታት (እሑዶች) የሚዘመሩ መዝሙራትም ትንሣኤን፣ ዕርገትን፣ የመንፈስ ቅዱስን መውረድ የሚያስረዱ ሲኾኑ፣ ምሥጢራቸውም ከሙታን ተለይቶ ለተነሣው፣ አዳምና ልጆቹን ከዲያብሎስ ተገዢነት እና ከሲኦል ባርነት ላወጣቸው ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ማቅረብ እንደሚገባ ያስተምራል፡፡ ከኀምሳኛው ቀን (ከበዓለ ጰራቅሊጦስ) ቀጥሎ በሚመጣው እሑድ (በስምንተኛው ቀን) የሚዘመረው መዝሙር፡– ‹‹ወረደ መንፈስ ቅዱስ ላዕለ ሐዋርያት ከመ ዘእሳት ወተናገሩ በነገረ ኵሉ በሐውርት …›› የሚል ሲኾን፣ ትርጕሙም መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል በሐዋርያት ላይ መውረዱንና በእርሱ ኃይል በዓለሙ ዅሉ ቋንቋዎች መናገራቸዉን የሚያስረዳ ነው፡፡

በዚህ ዕለት በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች፡ኤፌ.፬፥፩፲፯፤ ፩ኛዮሐ.፪፥፩፲፰፤ ሐዋ.፪፥፩፲፰፤ መዝ.፷፯፥፲፰ (ምስባክ)፤ ዮሐ.፲፬፥፩፳፪ ሲኾኑ፣ የምንባባቱ ፍሬ ሐሳብም የሚከተለው ነው፤

የጳውሎስ መልእክት፡እያንዳንዳችን መንፈስ ቅዱስ በገለጸልን መጠን የየራሳችን ልዩ ልዩ ጸጋ እንዳለን፤ የዮሐንስ መልእክት፡የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚፈጽም ለዘለዓለም ሕያው እንደ ኾነ፤ የሐዋርያት ሥራ፡መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ እንደ ወረደና በዓለሙ ዅሉ ቋንቋዎች መናገር እንደቻሉ፤ መዝሙረ ዳዊት (ምስባኩ)እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ልዩ ልዩ ጸጋን እንደሚሰጥ፤ የዮሐንስ ወንጌል፡እግዚአብሔር እኛን ልጆቹን እንደ ወላጅ አልባ እንደማይተወን ያስረዳሉ፡፡ ቅዳሴው ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ ሲኾን፣ ይህም ምሥጢረ ሥላሴን፣ የጌታችንን ሰው መኾን፣ ሕማሙን፣ ሞቱን፣ ትንሣኤዉን፣ ዕርገቱንና መንፈስ ቅዱስን መላኩን ይናገራል፡፡

ቅድስት በኾነች በጽርሐ ጽዮን በሐዋርያት ላይ የወረደው የእግዚአብሔር አብ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር ወልድ ፍቅር፣ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አንድነት በዅላችን ላይ ይደር፤ እጽፍ ድርብም ይኹን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

ምንጭ

በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት የተማረኩ አሕዛብም ‹‹ምን እናድርግ?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ከክፋታቸው ተመልሰው፣ ንስሐ ገብተው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንዲጠመቁ ነገሯቸዋል፡፡ በዚያችም ሰዓት ሦስት ሺህ ሕዝብ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ ተጠምቋል (ሐዋ.፪፥፩፵፩)፡፡

አዳምና ልጆቹን ከዲያብሎስ ተገዢነት እና ከሲኦል ባርነት ያወጣው ቸሩ መድኃኔ ዓለም የወደቁትን ወገኖቻችን ያንሳቸው፣ ጰራቅሊጦስንም ያውርድላቸው

__

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

Holy Spirit: The Most Precious Gift

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 3, 2012


This Sunday marks the high point in the Church’s post-Paschal celebrations. After proclaiming the Resurrection of Christ for the past several weeks, the Church has called our attention to several post-Resurrection appearances to underscore the reality of the risen Lord for the life of the Church.

Today marks the highpoint of those celebrations. Today we celebrate the coming of the Holy Spirit on the twelve disciples in the upper room on the Day of Pentecost. Why is this so important? Historically, Pentecost was the Jewish feast which celebrated the first fruits of the harvest. Every Jewish home celebrated God’s good gifts to them by giving the Lord a portion of their grain harvest, in anticipation of the full crop to come. It is simply a thank-you gift.

On this day the Church celebrates God’s gift of the Holy Spirit to the Church. Much of the service is devoted to two things: the Trinity and the coming of the Holy Spirit in the life of the believer. There is so much to say on a day like today, but there is one truth that especially stands out that I would like to emphasize. It comes from a phrase we find repeated several times in the special hymns for today, which reads, “Verily, the fire of the Comforter has come and lit the world.”

Verily, the fire of the Comforter has come and lit the world. Let’s look at this a little closer. The comforter is the Holy Spirit, described by Jesus in John 14 when he said, “I will pray to the Father and he will give you another Helper, or Comforter, that he may abide with you forever: the Spirit of truth.”

That’s what the Holy Spirit does for us. He is sent by the Father, through the Son, and abides in us through his Holy Spirit. That’s where the Church gets its emphasis on the Trinity today. But the other lesson focuses on the presence and power of the Holy Spirit in the lives of the disciples.

In Acts 1:8 Jesus said:

But you shall receive power when the Holy Spirit comes upon you, and you shall be my witnesses in Jerusalem, and in all Judea and Samaria, and to the uttermost part of the earth.

Why did Jesus focus on the power of the Spirit’s presence in the life of the disciples? Simply because they needed it. Up to now they were shaky and timid people, for the most part. They were following Jesus, but the Jesus they followed died and rose from the dead, and now they did not know what to do except to wait for the Spirit, as Jesus told them to do.

And then, it happened. We are told in Acts 2:

When the day of Pentecost had fully come, they were all with one accord in one place, and suddenly there came a sound from heaven as of a rushing, mighty wind, and it filled the whole house where they were sitting. Then there appeared to them divided tongues, as of fire, and one sat on each of them, and they were all filled with the Holy Spirit and began to speak with tongues, as the Holy Spirit gave them utterance.

And then, shortly after that:

Peter, standing up with the eleven, raised his voice and said to them, “Men of Judea, let this be known to you. This is what was spoken by the Prophet Joel.”

Power, power, power. That’s one of the most important truths we learn from Pentecost. Christ gave his Holy Spirit to his followers to take his place on earth, and to empower them for Christian service. That’s what Peter was doing when he preached. Why is the power of the Holy Spirit so important to have?

The power of the Holy Spirit is important because he enables us to fulfill Christ’s demands. It is as simple as that. We simply cannot fulfill the Lord’s commands apart from the inner strength to obey them.

Every once in a while I meet people who tell me, “I have tried and tried to live the Christian life, but just cannot do it. I have this hang-up, and I just cannot get over it. I have tried hard, and, well, I just cannot do it. I cannot live, and I cannot obey, Jesus’ teachings, even though I have tried with all my heart.”

Have you ever felt like that? Have you tried living the Christian life and felt like giving up because you do not have the power to live it? If so, I have good news for you today. You are absolutely right. You have just discovered one of the most important truths you could ever learn about the Christian life. That truth is the truth that will set you free from all self-help and all the self-reliance that has made you so discouraged.

And what is that truth? It is the truth that only the Holy Spirit can give you the power to live as Jesus wants you to live. You cannot live by the power of your own sweat. On the contrary, the inner power for living the Christian life is summed up on this Day of Pentecost, and it is given in the words of Jesus, who declared, “Without me you can do nothing.”

And that is the good news of the Gospel.

Source: AncientFaithRadio

________________________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , | 1 Comment »

ርግቢቱ ዓለም – The Scared Pigeon

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 19, 2012

 

ዓለምእህታችን እ. . አ በማርች 14 2012 .ም ከንጋቱ 1200 ሰዓት ላይ ነው ያረፈችው ተብሏል። ወገኖቻችንና አንዳንድ ብሩክ የሆኑትን የዓለማችን ነዋሪዎችን ያሳዘነው የዓለም አሟሟት እጅግ በጣም ልዪ የሆነ ነገር በሁላችን ዘንድ ሊፈጥር ችሏል። ከሁለት ወራት በፊት ወደ ቤይሩት ከተማ ብቅ ያለችው እህታችን ኃይለኛ የሆነ መልዕክት ይዛልን ነበር ወደዚያኛው ዓለም ያለፈችው። በዓለማችን በመከራ ማዕበል የማይንገላታ ሰው የለም፤ አረመኔ በሆኑት የአረብ ሕዝቦች እጅ የተያዘ ደግሞ ከየተኛውም የዓለም ክፍል በይበልጥ በሥጋም ሆነ በነፍስ እየተቀጠቀጠ ነው ለመኖር የሚበቃው። መከራ የምንቀበለው ነገ በገሃነም እሳት ሳይሆን ዛሬ በምድር ሳለን መሆኑ ትንሽ ሊያጽናናን ይገባል። ለዚህም ነው እህታችን ዓለም በዚህች ምድራዊ ሲኦል በእግረ አጋንንት ተረገጠው ለሚኖሩት እህቶቻችን ሁሉ አሁን መልዕክተኛ ሆና የቀረብችልን። መቼም በመከራና ችግር ጊዜ ድንቅ ነገር ይመጣልና እምብዛም መደነቅ የለብንም። የፈጣሪ ክብር ሲገለጥ ሐሴት በማድረግ ደስ ሊለን ይገባል፡ መንፈሱ በኛ ላይ አርፏልና።

ላይ ቪዲዮው ላይ የምትታየውን ርግብ ያነሳኋት ባለፈው ሣምንት፡ በማርች 14፡ ልክ ከቀኑ 1200 ሰዓት ላይ ነበር። ርግቢቱ በመኖሪያ ቤቴ በመስኮት በኩል ገብታ ጋራጅ መውረጃ ላይ ቁጭ ብላ ነበር ያገኘኋት። እኔን ስታይ እየተንደፋደፈች ወደላይ በመብረር ከቤቱ ለመውጣት መስኮቱ ጋር ትጋጭ ነበር። እኔም ቆም ብየ ለ10 ደቂቃ ያህል ከታዘብኳት በኋላ ልረዳት ጠጋ አልኩኝ። መጀመሪያ ላይ ለመሸሽ ብትሞክርም በመጨረሻ ይዣት በመስኮቱ ላወጣት ችያለሁ።

የርግቢቱ ሁኔታ፡ በዚያ ቀን በጣም ስታሳስበኝ የነበረችውን የእህታችንን፡ የዓለምን ሁኔታ ያሳየኝ መስሎ ነበር የታየኝ። ርግቢቱ ከአካባቢዋ አምልጣ የሆነ ነገር ለማግኘት ወደ ቤቱ ገባች፡ ግን ቤቱ ውስጥ ምንም ነገር ስላላገኘች ወደ መጣችበት ለመመለስ ፈለገች፡ ሆኖም የገባችበት መስኮት ዘንበል ብሎ በጠባቡ የተከፈተ ስለነበር በቀላሉ ከቤቱ መውጣት አልቻለችም። ቆም ብዬ በታዘብኳት ወቅት ርግቢቱ ስታሳየው የነበረው የጭንቀትና የመረበሽ ሁኔታ እጅግ በጣም ያሳዝን ነበር፣ ከታች ጠብጠብ ታደርጋለች፣ በቂ አየር ስላልነበረም ክንፎቿን ዘርግታ እንደልቧ መብረር አልቻለችም፣ ስለደከመችም አፎቿን በጣም ከፍታ አየር ትስብ ነበር። መስኮቱ ላይ ሆና ከውጭ ሌሎች እርግቦችን ሲበሩ ስታይ ከነርሱ ጋር ለመሆን በመንደፋደፍ ከመስተዋቱ ጋር ትጋጫለች። በመጨረሻም ምንም ማድረግ እንደማትችል ስለተገነዘበች ጠጋ ብዬ እንድይዛት ፈቀደችልኝ። በመስኮቱ በኩል እጄን አውጥቼ ስለቃት ከመቅጽበት ነበር ነፃ ሆና እየበረረች ወደሰማይ ለመውጣት የበቃቸው።

እንደ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ ፤ ማክሰኞ ማርች 14ለረቡዕ አጥቢያ እህት ዓለምን የምትከታተላት ነርስ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ተኝታ አየቻት፡፡ 11 ሰዓት ላይም ተኝታ ነበር፡፡ ለሦስተኛ ጊዜ በ12 ሰዓት ስትጎበኛት ለአየር ማስገቢያ በተከፈተ ኮሪደር ላይ አንሶላ ቀዳ ራሷን አጥፍታ ተገኘች፡ ስለዚህ የሞተቸው ረቡዕ ማርች 14 ከንጋቱ 12 ሰዓት ላይ እንደሆነ ተገልጧል።

ይህን ዜና ካገኘሁ በኋላ ርግቢቱን ያገኘኋት በ12 ሰዓት ላይ መሆኑ ባጋጣሚ እንዳልሆነ አሁን ገባኝ። ርግብ የ መንፈስ ቅዱስ፥ የሰላምና የነፃነት ምልክት ናት። 12 ቁጥርም ቅዱስ ቁጥር ነው። እህት ዓለም ከእርጉሞች እጅ ነፃ ወጥታለች የእግዚአብሔርን ሰላም አግኝታለች። የበደሏት እርጉም ሕዝቦች ግን የሚቀጡበት ጊዜ ደርሷል፣ አምላክ የሰጣቸውን ዕድል ባለመጠቀማቸውም ተፈርዶባቸዋል ፤ የዘሯትን የጥላቻ ሰብል በቅርቡ ያጭዷታል።

መዝሙር 12

5 ስለ ድሆች መከራ፥ ስለ ችግረኞች ጩኸት እግዚአብሔር፤ አሁን እነሣለሁ ይላል፤ መድኃኒትን አደርጋለሁ፥ በላዩም እገልጣለሁ።

6 በምድር ላይ እንደ ተፈተነ ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ ብር። የእግዚአብሔር ቃላት የነጹ ቃላት ናቸው።

7 አቤቱ፥ አንተ ጠብቀን፥ ከዚህችም ትውልድ ለዘላለም ታደገን።

8 በሰው ልጆች ዘንድ ምናምንቴ ከፍ ከፍ ባለ ጊዜ ክፉዎች በዙሪያው ሁሉ ይመላለሳሉ።

 

A well-written song by David, when he was in the cave; a prayer.

Psalm 142

1 To the LORD I cry out; to the LORD I plead for mercy.

2 I pour out my lament before him; I tell him about my troubles.

3 Even when my strength leaves me, you watch my footsteps. In the path where I walk they have hidden a trap for me.

4 Look to the right and see! No one cares about me. I have nowhere to run; no one is concerned about my life.

5 I cry out to you, O LORD; I say, “You are my shelter, my security in the land of the living.”

6 Listen to my cry for help, for I am in serious trouble! Rescue me from those who chase me, for they are stronger than I am.

7 Free me from prison, that I may give thanks to your name. Because of me the godly will assemble, for you will vindicate me.

_________________________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

ምስጢረ ጰራቅሊጦስ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 12, 2011

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

ዘንድሮ የጰራቅሊጦስ (ጰንጠቆስጤ) በዓል በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ሰኔ ፭ ቀን በመላው አብያተ ክርስቲያናት ተከብሮ ይውላል። ከጌታ ዘጠኙ ዐበይት በዓላት አንደኛው የጰራቅሊጦስ በዓል ነው። ይህ በዓል በኦሪቱ በዓለ ሠራዊት ይባላል። የእሸት በዓል ማለት ነው። ከፋሲካ ሰንበት በኋላ እሑድ በሃምሳኛው ቀን ላይ ስለሚውል በዓለ ሃምሳ ተብሎ ይታወቃል። ይህንን ዕለት ጽርአውያን በቋንቋቸው ጸንጠቆስጤ ይሉታል። የሃይማኖት ስም አይደለም። በዘመናችን በተለይም እንደ አውሮፓውያን ዘመን አቆጣጠር ከ ፲፱፻፮ ዓ.ም ጀምሮ በዚህ ስም ራሳቸውን የሰየሙ ቡድኖች የሃይማኖታቸው መታወቂያ በማድረግ ሲጠሩ ይሰማል። በመጽሐፍ ቅዱሱም ሆነ በጥንታዊት ቤተክርስቲያን ታሪክ በጰንጠቆስጤ ስም የሚታወቅ የሃይማኖት ድርጅት አልነበረም አይታወቅም።

ቤተክርስቲያናችን ይህን በዓል የምታከብረው መጽሐፍ ቅዱስንና ትውፊተ ሐዋርያትን መሠረት አድርጋ ነው። በግብረ ሐዋ.፪፥ ፩ – ፳፪ ተጽፎ እንደምናገኘው አይሁድ ከመላው ዓለም ተሰብስበው በዓለ ሃምሳን ሲያከብሩ ጰራቅሊጦስ የተባለው መንፈስ ቅዱስ ድምፁን እንደ አውሎ ነፋስ እያሰማ ጸጋውን እንደ ባዘቶ በእሳት ላንቃ አምሳል ከፍሎ ከፍሎ በጸሎት ጽሙዳን ለሆኑት መቶ ሃያ ቤተሰብ አድሏቸዋል። (ሐዋ.፪፥፲፬–፲፭) ሐዋርያትም ከሦስቱ ክፍላተ አህጉር ለመጡት አይሁድ መንፈስ ቅዱስ በገለጸላቸው ቋንቋ ለማስተማር በቅተዋል።

በሚያውቁት በአንድ የዕብራይስጥ ቋንቋ ላይ ሰባ አንድ ቋንቋ ስለተጨመረላቸው እንደ ልባቸው የክርስቶስን አምላክነትና ትንሣኤውን ያለ ፍርሃት መስክረዋል። በተገለጸላቸው ቋንቋ ለሰው ሁሉ ስላስተማሩ ሰሚዎቹ ተአምራቱን በማድነቅ የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ በልሳኖቻችን ሲናገሩ እንሰማቸዋለንበማለት ተገርመዋል። የመንፈስ ቅዱስን ሥራ የተጠራጠሩ ሰቃልያን ክርስቶስ አይሁድ ግን የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ለጉሽ ጠጅ ሰጥተው ማፌዝ ስለጀመሩ ቅዱስ ጴጥሮስ ነቢዩ ኢዮኤል በምዕራፍ ፪ ከቁጥር ፳፰—፴፪ የተናገረውን ትንቢት በመጥቀስ በተግሳፅ አሳፍሯቸዋል። ኢዮኤል የተናገረው ትንቢት ለአንድ ጊዜና ለመጨረሻው በዘመነ ሐዋርያት ተፈጽሟል። መንፈስ ቅዱስ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በቤተክርስቲያን አድሮ ለምእመናን እንደ ሃይማኖታቸው ጽናት፥ እንደ ምግባራቸው ቅንነት ጸጋውን ሲያድል ይኖራል። የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ በጥምቀተ ክርስትና በሜሮን ሲሰጥ በመጠኑ ነው። ምዕመናን ጸጋው እየተጨመረላቸው እንዲሄድ በገድል በትሩፋት ተወስነው የክርስቲያንን ተግባር እየፈጸሙ ሲሔዱ ጸጋው እየተጨመረላቸው እንዲሄድ በገድል በትሩፋት ተወስነው የክርስቲያንን ተግባር እየፈጸሙ ሲሔዱ ጸጋው እየተጨመረላቸው ከነጽሮተ ሥሉስ ቅዱስ፥ ከከዊነ እሳት ማዕረግ ለመድረስ ይበቃሉ። በዚህን ጊዜ እንደሐዋርያት በጥላቸው በልብሳቸው ሕሙም መፈወስ፣ ጋኔን ማውጣት፣ ሙት ማንሳት

ይቻላቸዋል። ቤተክርስቲያናችን ጠቅለል ባለ መልኩ ስለ መንፈስ ቅዱስ ለቤተ ክርስቲያን እንዳልተሰጠ ተቆጥሮ አንዳንድ መናፍቃን በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የሚሰነዝሩት ጉንጭ አልፋ ዘለፋ መሠረት የሌለው ስለሆነ አንደነቅበትም። እነዚህ የሚያለያዩ ሥጋውያንም የሆኑ።መንፈስም የሌላቸው ሰዎች ናቸውና። (ይሁዳ ፩፥፲፱) ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በመጀመሪያይቱ የቆሮንቶስ ክታቡ የኢየሱስ ክርስቶስን የባሕርይ አምላክነት አምነው በተጠመቁ ክርስቲያኖች መንፈስ ቅዱስ አድሮባቸው እንዳለ ገልጾልናል። በተጨማሪም የመንፈስ ቅዱስ አካሉ አንድ ሲሆን ጸጋው (ሀብቱ) ግን ልዩ ልዩ በመሆኑ ለምዕመናን ሁሉ አንድ አይነት ጸጋ የላቸውም ብሏል። (፩ቆሮ. ፲፪፥፩—፲፩) ጸጋውንም እነርሱ እንደወደዱት ሳይሆን መንፈስ ቅዱስ እንደፈቀደ እንደሚጠቅማቸው አድርጎ ይሰጣቸዋል። ከመንፈስ ቅዱስ ሥጦታዎች ከእምነትና ከፍቅር የሚበልጥ ጸጋ አለመኖሩን ዐውቀን በየሰፈሩ እየተሹለከለኩ መንፈስ ወርዶብናል እያሉ ከሚያጭበረብሩ ቢጽ ሐሳውያን ሁሉ መጠበቅ ይገባናል።

እነዚህ ሰዎች የጵጵስናም ሆነ የቅስና ማዕረግ ክህነት ሳይኖራቸው ራሳቸውን በራሳቸው ሾመው እጆቻችንን እየጫንን መንፈስ ቅዱስ እናሳድራለን በማለት ብዙዎቹን የዋሆች የመንፈስ ርኩስ ቁራኛ ስላደረጉዋቸው ምዕመናን ሆይ በተዋሕዶ ሃይማኖታችሁ እስከመጨረሻው እንድትጠበቁ እንመክራችኋለን። (፩ቆሮ.፲፪፥፫፧ ፩ቆሮ.፲፫፥ ፩—፲፫) በጸሎተ ሃይማኖታችን ስለ መንፈስ ቅዱስ ያለን እምነት እንደሚከተለው ይጠቃለላል፡

በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን። እርሱም ጌታ ሕይወትን የሚሰጥ ከአብ የሠረፀ፣ ከአብና ከወልድ ጋራ በአንድነት እንሰግድለታለን እናመሰግነዋለን። እርሱም በነቢያት አድሮ የተናገረ ነው።መንፈስ ቅዱስ እንዳይለየን በመናፍቅነትና በእልከኝነት ልባችን እንዳይደነድን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖታችን አጽንቶ በክርስቲያናዊ ሕይወት ለመመላለስ ያብቃን፡ አሜን።

MenfesQedus

 

ምንጭ፡ ethiopianorthodox.org

Speaking In Tongues: An Orthodox Perspective

Fr. George Nicozisin

Speaking in Tongues, “Glossolalia,” a popular practice with many Churches today, is a phenomenon which can be traced to the days of the Apostles. A decade ago, Speaking in Tongues was encountered only in Pentecostal Churches, Revival Meetings, Quaker gatherings and some Methodist groups. Today, Glossolalia is also found in some Roman Catholic and Protestant Churches.

Serapion of Egypt, a fourth century contemporary of St. Athanasios summarized Eastern Orthodox theology:

“The Anointing after Baptism is for the Gifts of the Holy Spirit, that having been born again through Baptism and made new through the laver of regeneration, the candidates may be made new through the gifts of the Holy Spirit and secured by this Seal may continue steadfast.”

Bishop Maximos Aghiorghoussis, Greek Orthodox Diocese of Pittsburgh and world-reknowned Orthodox theologian on the Holy Spirit states it this way: “For Orthodox Christians, Baptism is our personal Paschal Resurrection and Chrismation is our personal Pentecost and indwelling of the Holy Spirit.”

There are two forms of Glossolalia:

Pentecost Glossolalia happened this way: Fifty days after the Resurrection, while the disciples were gathered together, the Holy Spirit descended upon them and they began to speak in other languages. Jews from all over the civilized world who were gathered in Jerusalem for the religious holiday stood in amazement as they heard the disciples preaching in their own particular language and dialect (like in a United Nations Assembly). They understood!

Corinthian Glossolalia is different. St. Paul, who had founded the Church of Corinth, found it necessary to respond to some of their problems, i.e., division of authority, moral and ethical problems, the Eucharist, the issue of death and resurrection and how the Gifts of the Holy Spirit operated. In chapter 12, St. Paul lists nine of the Gifts of the Holy Spirit, i.e., knowledge, wisdom, spirit, faith, healing, miracles, prophecy, speaking in tongues and interpreting what another says when he speaks in tongues.

Specifically, Corinthian Glossolalia was an activity of the Holy Spirit coming upon a person and compelling him to external expressions directed to God, but not understood by others. In Pentecost Glossolalia, while speaking in several different tongues, both the speaker and the listener understood what was uttered. The Glossolalia manifested in Corinth was the utterance of words, phrases, sentences, etc., intelligible to God but not to the person uttering them. What was uttered needed to be interpreted by another who had the gift of interpretation.

GlossolaliaOrthodoxPerspective

TheTruthOfOurFaith

A Neuroscientific Look at Speaking in Tongues

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | 2 Comments »

 
%d bloggers like this: