Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • March 2023
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    2728293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘Ethiopian Monastery’

የእሥራኤል ፖሊሶች ኢትዮጵያውያን መነኮሳትን በማንገላታቱ ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን ወደ ኢየሩሳሌም ማዛወሯን ለጊዜው ገታች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 13, 2018

በኢየሩሳሌም ከተማ፡ የኢትዮጰያውያን ርስት ወደ ሆነውና፡ የእስራኤል ሬድዮ ጣብያ ተከራይቶ ይሠራበት ወደነበረው ከ110ዓመት በላይ ያስቆጠረ ህንፃ የእስራኤል መከላክያ ሰራዊት በራሱ ፈቃድ ገብቶ አባቶችን በኃይል ማስወጣቱ፣ ማንገላታቱና ማሠሩ አንድ ተንኮል ከበስተጀርባው አለ ያስብላል።

የግብጽ እጅ፡ ወይስ ኢትዮጵያ በኢየሩሳሌም ጉዳይ ከጥቂት ወራት በፊት ባልተባበሩት መንግሥታት ከመሀመዳውያኑ ጋር በመሰለፏ?

ያም ሆነ ይህ፡ በአባይ ወንዝ ሳቢያ፡ እስራኤልም ሆነች አውሮፓ፡ ሁሉም ከግብጽ ጋር ማበሩን ይመርጣሉ።100 ሚሊየን ቁንጥንጥ ግብጻውያን ከሚጠሙና ከሚራቡ 100 ሚሊየን ሰላማዊ ኢትዮጵያውያን መቸገራቸውን ይመርጣሉ። 100 ሚሊየን የተራቡ ግብጻውያን እስራኤልንም ሆነ አውሮፓን በስደትና በሽብር ያተረማምሷቸዋልና።

ስለዚህ፡ ዓለማዊው የእስራኤል መንግስት ኢትዮጵያን ወደ አረቦቹ በይበልጥ እንድትጠጋ መግፋት፣ ከእስራኤል ጋር ያላትንም ቅርርብ በጣም እንዳታጠብቅና በረከቱንም እንድታጣ ይሻሉ። የአባቶቻችንም መንገላታት የሚነግረን፡ ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን ወደ ኢየሩሳሌም አዙራ፡ በእስራኢል ዘንድ መልካም ግምት እንዳይሰጣት ለማድረግ በማሰብ ሊሆን ይችላል። Problem – Reaction – Solution.

ለማንኛውም፡ እስራኤል ዕብራይስጥ ቋንቋን እንደ አረብኛ ከቀኝ ወደ ግራ መጻፉን ማቆም አለባት፤ ኢትዮጵያም ከአረቦች ጋር ጢብጢብ መጫዋቱን መተው ይኖርባታል።

[ትንቢተ አሞጽ ፱፥፯]

የእስራኤል ልጆች ሆይ እናንተ ለእኔ እንደኢትዮጵያ ልጆች አይደላችሁምን? ይላል እግዚአብሔር

______

 

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

እግዚኦ! ፈረንጁ መነኩሴ፡ “የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ማህበረሰብ በጣም እንግዳ የሆነ አንድ የአምልኮ ሥርዓት አለው” ይላል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 20, 2017

ለገና በዓል የቸኮሌት ጥንቸልለፋሲካ ደግሞ የቸኮሌት አባባ ገና

ለስጦታ ይዘው ይመጣሉ – አንዳንዴም ፎፎ ቆሎ ያቀርባሉ

39 ዓመት እድሜ ያለው ጀርመናዊ ካቶሊክ መነኩሴ ነበር ከመላው ዓለም ወደ እየሩሳሌም ለመጡ ጋዜጠኞች ይህን የተናገረው፤ ኒቆዲሞስ ስኬንቤል ይባላል፤ ያውም በጌታችን ልደት ዋዜማ።

Source/ ምንጭ፡ Haaretz + Die Welt

በቃ ሙሉዋ ዓለም የእነርሱ ብቻ ናት! እነዚህ ሰዎች አይማሩም!

ኢትዮጵያዊው በተሰጠው መንፈሳዊ ጸጋ በጣም ነው የሚቀኑት፤ ስለዚህ በተገኘው አጋጣሚ ሁላ የቁሳዊ ድህነታችንን እየተጠቀሙ እኛን ለማንቋሸሽ ሲሞክሩ ይታያሉ።

ወንድሞቻችና እህቶቻችን በሆኑት የምስራቅ እና የጥንታውያን ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ሳይቀር ተመሳሳይ ነገር አልፎ አልፎ ይታያል፦

ክርስቲያን ኢትዮጵያውያን “ክርስቲያን በሚባለው ሌላው ዓለም”፣ አይሁድ ኢትዮጵያውያን በእስራኤል፣ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በአረብ አገሮች፤ በሁላችንም ላይ አድሎዓዊ እና አስከፊ የሆኑ ድርጊቶች ሲፈጸሙ እናያላን፤ በዚህም ለእኛ ኢትዮጵያውያን ያለችን አንዲት አገር፡ ኢትዮጵያ ብቻ መሆኗንን በደንብ እንታዘባለን፤ ታዲያ ከፈረንጆች እና ከአረቦች ጋር እየተባበሩ ይህችን እግዚአብሔር የሰጠንን ቅድስት አገር ለማጥፋት የሚታገሉት ቅሌታሞችና ማፈሪያዎች ይህ ጉዳይ አያሳስባቸውምን? ትግላቸውና ጦርነታቸው ከእግዚአብሔር ጋር አይደለምን?

እራሳቸውን “ነጮች” ብለው የሰየሙት ፈረንጆቹ ነጭነታቸው ለመንፈሳዊ ኑሮ እንደሚያስቸግራቸው የራሳቸው የሳይንስ ሊቆች ይጠቁማሉ። ከጸሐይ ብርሃን እጥረት የተነሳ ብዙ የሚላኒን ኬሚካል ይጎድላቸዋል። ሚላኒን ወይንም ሚላቶኒን በጥቁር ሕዝቦች ላይ፣ በተለይ በኢትዮጵያውያንን ላይ (ከፍተኛ ተራራ ላይ በሠፈሩት) ላይ በብዛት የሚገኝ ኬሚካል ሲሆን የመንፈሳዊ እና የሃይማኖታዊ ሕይወትን በማጠንከሩ ረገድ ዘንድ ከፍተኛ ሚናም እንደሚጫወት ይነገርለታል።

ነጮቹም ቢሆኑ በተሰጣቸው የማወቅ ፍላጎት-ጸጋ በቅንነት ከተራመዱ ተመሳሳዩን መንፈሳዊ ጸጋ እግዚአብሔር ይሰጣቸዋል፤ ግን በእንዲህ ዓይነት መልክ አይደለም፤ በማፌዝና በማጥላላት፤ ሌላውን ዝቅ ለማድረግ በመሞከር አይደለም።

 ጀርመናዊ ዶ/ር መነኩሴ እንዲህ ይላል፦

እዚህ እየሩሳሌም የምንገኝና የተለያዩ ዓብያተክርስቲያናት የምንወክል ክርስቲያኖች በዚህ በገና ወቅት፡ ለቡና እና ለተለየዩ መጠጦች እርስበርስ የመገባበዝ ባሕል አለን ነገር ግን ከዓብያተክርስቲያናቱ ሁሉ ትንሿ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በጣም እንግዳ የሆነ አንድ የአምልኮ ሥርዓት አላት።”

ልብ እንበል፡ “ትንሽ የሆነችው!“

ሰውዬው ቀጠል በማድረግ፦

የበዓላቱ አከባበር ስነ ሥርዓት ሁሉ ተመሰቃቅሎባቸዋል፤ ለገና እና ለፋሲካ የሚያመጧቸው ጣፋጮች ተዘበራርቀውባቸዋል፤

ለምሳሌ አለ ዶ/ር መነኩሴው፦

ለገና በዓል የቸኮሌት ጥንቸልለፋሲካ ደግሞ የቸኮሌት አባባ ገና በስጦታ መልክ ይዘው ይመጣሉ – አንዳንዴም ፎፎ ቆሎ ያቀርባሉ

አየን አይደለም፤

ስለ ጉርብትናው፣ ስለ ትህትናው፣ ስለፍቅሩ፣ ስለ አጽዋማቱ፣ ስለ ቅዳሴው እንዲሁም ኢትዮጵያውያን የጌታን ልደት በ ጃንዋሪ 7 እንደሚያከብሩ ያወሳው ነገር የለም።

አሁን ይህ ሰው ክርስቲያን ነኝ ሊል ነው?

ቀደም ሲል እንዳቀርብኩት ይህ አሜሪካዊ በገዳም አባቶች ላይ ሲያሽሟጥጥ የነበረውም በተመሳሳይ መንፈስ ነው፦

 

አይክፋን! እንዲያውም ደስ ይበለን!

ይህ በቅናትና በትዕቢት ላይ የተመረኮዘ ድርጊት የኢትዮጵያን ቤ/ክርስቲያን ብቸኛ በክርስቶስ ደም ላይ የተገነባች ጽኑ ቤት ያደርጋታል እንጂ ሊያፈርሳት አይችልም።

ተመሳሳይ ፊዘኛነት፣ ቅናትና ምቀኝነት፤

  • + ቃኤል በአቤል ላይ፣
  • + እስማኤል በይስሐቅ ላይ፣
  • + ኤሳው በያዕቆብ ላይ፣
  • + የዮሴፍ ወንደሞች በዮሴፍ ላይ፤

ሲያሳዩ አይተናል።

በዮሴፍ የቀኑት ወንድሞቹ ዮሴፍን በጥላቻ ወደ ጉድጓድ መጣላቸው ዲያብሎስ በቤተሰብ መካከል እንኳን እየገባ ሁከት እንደሚፈጽም እንማራለን።

አለምን ሁሌም ሲያመሰቃቅሏትና አሁንም እያወኳት ያሉት የቃኤል፣ እስማኤልና ኤሳው ዘሮች በዲያብሎሳዊ እራስወዳድነት መለከፋቸውን እያየነው ነው፦

  • + ስግብግብነት
  • + ቅናት
  • + ጥላቻ
  • + ጥፋት
  • + ግድያ

ፍሬዎቻቸው ለይተን እናውቃቸዋለን።

______

Posted in Ethiopia, Faith, Infos, Media & Journalism | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

All Eyes on Waldeba Monastery

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 24, 2012

The Franco-German public-service cultural television channel, “arte” just broadcasted a film about the famous Ethiopian monastery, Waldeba. This fascinating video about the monastery of “Waldeba” in northern Ethiopia depicts the lives of around 1000 monks and hermits.  Last year, the monastery opened its gates to foreign camera crews for the first time.  The privilege of shooting this film had French filmmaker, Jean-Louis Saporito and researcher François Le Cadre.

The 1500-year-old Christian manuscript, “The HYPERLINK “http://ethiopianheritagefund.org/artsNewspaper.html”Abouna GaHYPERLINK “http://ethiopianheritagefund.org/artsNewspaper.html”rima GospelHYPERLINK “http://ethiopianheritagefund.org/artsNewspaper.html”sHYPERLINK “http://ethiopianheritagefund.org/artsNewspaper.html”,  the world’s oldest Christian book that could only be touched by the monks was displayed in its entirety for  the very first time.

 

Continue watching…

_______________________________________________________________________________

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: