Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • April 2023
    M T W T F S S
     12
    3456789
    10111213141516
    17181920212223
    24252627282930
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘Ethiopian Calendar’

ኢየሱስ ክርስቶስ – መስቀል – ኮሮና – የፀሐይ ግርዶሽ – ላሊበላ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 21, 2020

👉 ነጥብጣቦቹን እናገናኛቸው

🌑 ኢየሱስ ክርስቶስ

🌑 መስቀል

🌑 አክሊል(Corona/ኮሮና)(ወታደሮችም ከእሾህ አክሊል ጐንጕነው በኢየሱሰ ራሰ ላይ አኖሩ)

🌑 ዓለት (ያም ዓለት ክርስቶስ ነበረ)

🌑 የላሊበላ ውቅር አብያተክርስትያናት በአፄ ላሊበላ ዘመን አለት(ድንጋይ)ተፈልፍለው የተሠሩ

🌑 የንጉሥ ላሊበላ የልደት ቀን (በጊታቸን የልደት ቀን ተወለዱ)

🌑 የፀሐይ ግርዶሽ

🌑 የኢትዮጵያ ዓመት ፪ሺ፲፪ ዓ.

🌑 የማያዎች የቀን መቁጠሪያ 2012 ዓ.ም

ድንቅ ድንቅ በጣም ድንቅ የሆነ ዘመን ላይ ነን። ግን እያየን ነው የክርስቶስ ተቃዋሚዎቹ (አህዛብ፣ መናፍቃን፣ ግብረሰዶማውያኑ፣ እነ ግራኝ አብዮት አህመድና የፈረንሳዩ ኢማኑኤል(አማኑኤል የሚል ስም ይዟል)ለላሊበላ የተለየ ትኩረት መስጠታቸው?

የፀሐይ ግርዶሹ የተከሰተበት ዕለት ልክ የዛሬ ዓመት ላይ ገዳይ አብይ የላሊበላን ልጅ ጄነራል አሳምነውንና ሌሎቹን ኢትዮጵያውያን ጄነራሎችን ለመግደል ከተዘጋጀበት ዕለት ጋር ተገጣጥሟል። ዘንድሮ ግን ጥይት ሳይተኩስ ሚሊየን ኢትዮጵያውያንን በኮሮና ገድሎ ለመጨረስ ወስኗል። በኮሮና ሞተለሚባለው ለእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሞት የአብይ አህመድ አሊ እጅ አለበት(ዘር ማንዘሩ ይነቀል! ይጥፋ!)

____________________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ብዙዎችን ያስደነቀው የፀሐይ ግርዶሽ | ላሊበላ ነገሠ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 21, 2020

_________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

መላው ዓለም የኢትዮጵያ ካላንደር ነው ትክክለኛው፤ ቅዳሜ ለ፲፮ ሰዓት እንፁም እያለ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 18, 2020

  • 👉 በመጨው እሑድ አሮጌው ዘመን ይፈጸማል፤ ኋለኛው ዘመን በአዲሱ ዘመን ይተካል
  • 👉 በ ፪ሺ፲፪ (2012) .ም ምድራችንን ከባባድ ፈተናዎች ገጥመዋታል

ምድራችን በእኛ አቆጣጠር በ ፪ሺ፲፪ (2012) .. በፈረንጆቹ 2020 .. ላይ በከባድ ፈተናዎች ውስጥ እያለፈች ነው። እጅግ ጥንታዊው ከ1200 ዓመታት በፊት የነበረው የማያ የዘመን ቀመር ዐዲስ ያልተለመደ ክስተት የሚጀምርበት ዑደቱ የሚጠናቀቅበት የተፈጥሮ አደጋዎች በዝተው የሚታዩበት 2012 ላይ መሆኑን የሚያሳይ በመሆኑ ብዙ ዓለም ዐቀፍ ተመራማሪዎች በፈረንጆቹ 2012 ላይ መስሏቸው ብዙ አስተያየት በጊዜው ሲሰጡ ቆይተው ነበር። 2012 የሚል አስፈሪ ፊልም ከማያ የዘመን ቀመር በመነሣት የፈረንጆቹ ፪ሺ፲፪ (2012) ከመድረሱ ፫/ 3 ዓመት ቀድሞ በ2009 ላይ በሆሊውድ ተሠርቶ በሮናልድ ኤመሪክ ዳይሬክት ተደርጎ ሁላችንም ተመልክተነዋል።

በፈረንጆቹ ፪ሺ፲፪ (2012) /ሚ መለስ ዜናዊን ጨምሮ ሦስት አፍሪቃውያን መሪዎች አርፈዋል/ተገድለዋል፤ ሆኖም ሌሎች ብዙ ክስተቶች ሳይከሠቱ የእኛው ፪ሺ፲፪ (2012) .ም ላይ እንገኛለን። ፪ሺ፲፪ (2012) ዓመት ግን ገና ከመጀመሩ ለዓለማችን በጣም አስደንጋጭ ነበር። በዚህ ዓመት በመላው ዓለም ኮሮናን ጨምሮ በርካታ አስደንጋጭና አስደናቂ ነገሮች በመታየት ላይ ናቸው።

በመጭው እሑድ ሰኔ ፲፬ / ፪ሺ፲፪ (14/2012 .) June 21 – 2020

ከኢትዮጵያውያን ጋር ዝምድና ሊኖራቸው ይችላል ተብለው የሚነገርላቸው የአሜሪካዎቹ ማያዎች አሮጌው ዘመን ይፈጸማል፤ ኋለኛው ዘመን በአዲሱ ዘመን ይተካልይላሉ።

👉 ሰኔ ፲፬ / ፪ሹ፲፪ (14/2012 .) አቡነ አረጋዊ

ሁሉም ነገር ከኢትዮጵያ ቀመርና ከመጭው የፀሐይ ግርዶሽ ጋር መገጣጠሙ የሚገርም ነው።

🌑 ፪ሹ፲፪ /2012 .ም ግርዶሽ የሚታየው፡

  • ሰኔ ፲፬ / ፪ሺ፲፪ (14/2012 .) June 21 – 2020
  • በግርዶሹ 600 ሰዓት የሚፈጅ ጨለማ ይታያል፡፡
  • በመላ ኢትዮጵያ ይታያል፡፡
  • በተለይ ወለጋ፣ ጎጃም፣ ጎንደር፣ ደሴ፣ አላማጣ፣ ኢንጂባራ 98% ጨለማ ሆኖ ይታያል፡፡
  • የዓለምን አሰራር የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካን፣ የከፍተኛ የተፈጥሮ ኃይል ሊገኝ ይችላል ብለው ሳንቲስቶች ሀሳባቸውን እየሰነዘሩ ይገኛሉ፡፡
  • ከምዕራብ ኢትዮጵያ እስከ ሰሜን ኢትዮጵያ ድረስ ግርዶሹ ይታያል፡፡
  • ፀሐይ 98% ትሸፈናለች፡፡

🌑 የሚታይበት እና የሚያበቃበት፡

ከማዕከላዊ አፍሪካ ከኮንጎ ይነሳል፣ ሱዳን፣ ኢትዮጵያ፣ የመን፣ ፓኪስታን፣ ታይዋን፣ ንድና ቻይናን አቋርጦ ፓስፊክ ውቂያኖስ ላይ ያበቃል፡፡

🌑 ሙሉ ግርዶሹ የሚታይበት ወቅት

  • ከሌሊቱ ሰኔ 14/2012፲፬ / ፪ሺ፲፪ (14/2012 .) June 21 – 2020 .
  • – 1100 ሰዓት ይጀምራል፣
  • ከጠዋቱ 1245 እስከ ቀኑ 633

👉 ማስጠንቀቂያ፡

  • በዓይን ለማየት አይቻልም ዐይን ያሳውራል፣
  • በሱቅ ውስጥ የሚሸጥ መነጽር መጠቀም አይገባም፡፡
  • ለፀሐይ ግርዶሽ ተብሎ የተዘጋጀ መነጽር አለ፡፡
  • መነጽሩ አገር ውሰጥ አይገኝም፡፡
  • ለፀሀይ ግርዶሽ የሚሆን መነፀር አለን ከሚሉ አጭበርባሪዎች ጥንቃቄ ያድርጉ
  • ሲጨልም ማየት እንችላለን ነገር ግን ያለመነጽር ለማየት አንሞክር፣በጣም ጥንቃቄ ሊታከልበት ይገባል
  • ዐይናችን ሊፈስ ይችላል

የነገ ሰው ይበለን!

_______________________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ብሩክ አዲስ ዓመት – Happy Ethiopian New 2008 Year

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 8, 2015

Enkutatash2008

___

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , | Leave a Comment »

Is 9/11/13 Prayer Already Prompting Miracles?

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 20, 2013

My Note: I can not answer that. But, I am positive that prayers do wonders. I am also certain that the real universal New Year’s Day is September 11, which is celebrated among Ethiopians. For them it’s a very significant Holiday to celebrate the beginning/arrival of the “Day of Salvation”. There are even alternative thoughts that the real Birth Day of our Lord Jesus Christ, our Mother Holy Mary, Saint John, and many others saints, Holy men and women is September 11, Meskerem 1 according to the Ethiopian calendar. In any case, it would be wise if the rest of the world would take notice of the powerful signs that were displayed over the skylines of the great new Babylon city of New York (big apple), on this very day, 11 years ago, and join the Ethiopians in prayer and fasting, instead of conspiring to destroy them. Dark evil powers are out there actively fighting against humanity and against Egziabher The Lord. So, it would do us good, we would be blessed if we spend September 11 dedicating ourselves to contemplations, meditations and prayers. Let’s not forget to fast, specially on every Friday to contain Saudi zombies (Areb = Friday, in Ethiopic).

And they threw dust on their heads and were shouting with weeping and mourning, “Woe, Woe, O great city – in which all those who had ships on the sea got rich from her wealth – because in a single hour she has been destroyed!”” [Rev 18:19] This could indicate what might come in the future, please read the whole chapter.

 

 

Could prayer events in the U.S. be behind the revelation of political scandals unfolding in the nation’s capital on nearly a daily basis?

That’s what some supporters are beginning to suggest – albeit quietly

On May 2, the nation observed its official day of prayer – one proclaimed by Barack Obama at the request of Congress. Then on May 8, a special prayer meeting in the Capitol was observed by several members of Congress and former members including House Speaker Newt Gingrich.

A special message was delivered by Jonathan Cahn, author of “The Harbinger” and the inspiration behind “The Isaiah 9:10 Judgment” documentary. And now plans are being made for another National Day of Prayer and Repentance on Sept. 11.

Some supporters are beginning to suggest there may be a connection between recent news events and the prayers and calls for prayers.

Talk-show host Barry Farber, who announced his support for the 9-11-13 National Day of Prayer and Repentance on his nationally syndicated program this week was one of those who made the link.

“You’re reminding me of the lessons I learned – and forgot – during the Hungarian Revolution of 1956,” he told WND’s Joseph Farah, who first made the call for the 9/11 event.

“Everybody in Hungary went to bed on October 22, 1956, thinking they were the only anti-Communists left alive in Hungary. By mid-afternoon the next day, there were no Communists left in Hungary. Ditto for those of us who believe in God, endorse prayer, oppose abortion, despise Benghazi lies. Do you realize the extent of the revolution you might be leading? I forgive you if you don’t. It’s all too huge.”

Neither the earlier prayer events nor the upcoming one is meant to be political, but could they have political implications? That’s the question being raised.

Farah says he made the call for the 9-11-13 National Day of Prayer and Repentance out of a sense of frustration with politics and the decline in morality in the country. He suspects there is a connection between the revealing of national “sins” and the desire by believers to confess their own sins to God in unity with other believers.

“The key to this call is II Chronicles 7:14,” said Farah. “This is the prescription of a Holy God for national healing. He tells believers they are to do four things: humble themselves, pray, seek His face and turn from their wicked ways. In turn, God says He will hear their prayers, forgive their sins and heal their land. Honestly, I believe if believers across America do this, we will see miracles. Could it be they are already occurring? I wouldn’t be surprised.”

The 9-11-13 National Day of Prayer has been enthusiastically embraced by thousands around the country, including Rep. Michele Bachmann, R-Minn., Chuck Norris, David Barton, Jonathan Cahn, Greg Laurie and even syndicated radio talk-show host Mancow Muller. Recently Farah and a small working group behind the project have decided to give the event a new focus – repentance.

“Since the biblical prescription behind this project is II Chronicles 7:14, we determined, after much prayer ourselves, that repentance is the most important missing ingredient in America today,” said Farah. “God told Solomon that when the nation faces judgment for disobedience, there are four requirements for restoration: humility, prayer, seeking His face and repentance. Prayer without repentance is useless – that’s what the verse suggests. In fact, it suggests the prayers of believers go unheard unless is it accompanied by turning ‘from their wicked ways.’”

Also, significantly, Sept. 11, 2013 is the biblical Day of Teshuvah, which means repentance.

And while fasting is often a good idea as a companion to serious prayer, Sept. 11, 2013, comes just three days before Tishri 10 or Yom Kippur, which is a day of fasting.

Continue reading…

 

The Whole World Will Soon Use The Ethiopian Calendar

KasSakAccording to the report, all United Nations member counties voted to abandon Gregorian calendar and adopt the correct Ethiopian Calendars.

Starting from Wednesday, September 11, 2013, all countries in the world are going to use the Ethiopian calendar and celebrate the new year Meskerem 1, 2006.

The Reactions

The Germans said, “it is time we start using the correct calendar. We have been wrong all this time and the time has come to the world to follow our lead, start using the Ethiopian calendar.”

Brits are also agreed that the whole world should use Ethiopian Calendar.

The Italians said that Catholic Church is the one responsible to screw the whole world to use the current Gregorian calendar system and made every country use the wrong calendar for more than 1500 years.

An Italians said “ It is time we stop fooling ourselves and start following the real calendar year”.

The Americans are also 100% for it. “ohh…Yeah..New Year. Let’s party!!!” said an American citizen expressing his willingness to start to use the Ethiopian calendar.

However when we interviewed Japanese citizen Mr. Tokyoshi Chigamta, he asked “Wouldn’t it be easier for Ethiopians to start using Gregorian Calendar than the whole world change to use Ethiopian calendar?” He added “What benefit did Ethiopians get from becoming the only country in the world to use their own calendar? Did Ethiopia take loans and decided to change the calendar to pay 7 years later? I wonder what really happened.”

But too bad for Mr. Tokyoshi, the Japan’s government has already indorsed the decision and he has to use the Ethiopian calendar from now on.

In addition to the calendar, all countries will adopt the Ethiopian way of counting hours. The pm and am system is now out and the easy to use Ethiopian time system is going to be used by every country in the world.

__

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

ትክክለኛው የዘመን አቆጣጠር

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 31, 2010

  • ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት ከሚለው የንቡረ እድ ኤርምያስ ከበደ ወልደ ኢየሱስ መጽሐፍ የተወሰደ

በአረማዊነት ባህል፡ በክዋክብት ሥነ እውቀት ላይ የተመሠረተው የምዕራባውያን የዘመን አቆጣጠር፡ ከኢትዮጵያውያኑ የዘመን አቆጣጠር፡ የሚለይበት ባሕርይና አኹን ያለበት ቀውስ የደረሰበት ለምን ይሆን?

ኢትዮጵያውያን፡ በቅዱሱ ኪዳን ሃይማኖታቸው ላይ የመሠረቱትን፡ ይህን የጊዜ አቆጣጠር ሥርዓት፡ ምዕራባውያን፡ ኦርቶዶክሳውያን የተባሉት አብያተ ክርስቲያናት ጭምር፡ በአረማዊው፡ ዮልየስ ቄሣርና ጎርጎርዮስ (ግሬጎሪ) ፩፫ኛ በተባለው፡ በካቶሊካዊው ጳጳስ ስሞች እየሠየሙ፥ በየጊዜው እየለዋወጡና በመጨረሻ፡ ፰ ዓመታት ከ፲ ቀናት ያህል አክለውበት መቆየታቸው ይታወቃል። በዚህ የአቆጣጠራቸው ስልት፡ የጌታችን የኢያሱስ ክርስቶስን የልደት ቀን፡ ከ፬ እስከ፯ ዓመታት ለሚደርስ ዘመን፡ ከፍ አድርገው እንዲጨምሩ በመገደዳቸው፡ ይህን፡ ሰው ሠራሽ ቀውስ አስተካክለው ለማስታረቅ አቅቷቸው፡ እነሆ፡ እስካሁን ሲባዝኑ ይገኛሉ። በዚህ፡ በእነርሱው አቆጣጠር፥ ጌታ፡ የተወለደው፡ በ፬፥ በ፮ ዓመተ ምሕረት ላይ ሳይኾን አይቀርምከማለት በስተቀር፡ እርግጠኛውን ቀን፡ በቁርጥ ሊወስኑ ሳይቻላቸው ቀርቷል።

ይህ ቀውስ የተፈጠረባቸው፡ የጌታን የልደት ዓመት፡ አንድ ብለው መቁጠር ከጀመሩ በኋላ፡ ያ፡ የዓመተ ምሕረት መነሻ ዘመን፡ በአረማዊነት ዘመናቸው፡ ጁልያንበሚል ስምና በተለያየ ስልት ይጠቀሙበት በነበረው የአቆጣጠር ሥርዓታቸው፡ በ፬፥ በ፯ ዓመታት ላይ ውሎ ስላገኙት ነው።

ሌላው፡ ይህን ችግር የፈጠረባቸው ምክንያት፡ የምዕራባውያን የጊዜ አቈጣጠር፡ እንደ ኢትዮጵያውያኑ፡ በአንድ መሠረት ላይ ታንጾና በአንድ በተስተካከለ ሥርዓት ተቀምሮ የሚመራ ባለመኾኑ ነው። ይህንም፡ ከዚህ የሚከተለውን ማነጻጸሪያ ሓተታ በመመልከት መረዳት ይቻላል።

ኢትዮጵያውያን፡ የእግዚአብሔር ገነትተተከለባት፡ አዳምና ሔዋን የተፈጠሩባት አገራቸው የምትገኘው፡ በምድር ማዕከል ወይም መቀነት ክልል ውስጥ ስለኾነ፡ የጊዜ አቈጣጠራቸው ሥርዓት፡ መዓልቷና ሌሊቷ፡ ዓመቱን ሙሉ፡ በ፲፪፡ በ፲፪ ሰዓታት፡ እኩል በተከፈለበት የአሠፋፈር ስልት ላይ ተመሥርቶ፡ የባሕረ ሓሳቡ ቅመራ፡ ሥርዓቱን ጠብቆ፡ ያለችግር ይካኼዳል። ይኽውም፡ ወደኋላ፡ ወደረቂቃኑ ሳንኼድ፡ ከሣልሲት ተነሥተን፡ እስከ ዓመት ብንቈጥር እንኳ፡ ቀመሩ፡ የተስተካከለ ኾኖ እናገኘዋለን። ማለትም፡ ፷ (ስድሳ) ሣልሲታት፡ ፩ (አንድ) ካልዕት (second)፥ ፷ ካልዕታት፡ ፩ ደቂቃ፥ ፷ ደቂቃት፡ ፩ ሰዓት፡ ፳፬ ሰዓታት፡ ወይም ፷ ኬክሮስ፡ ፩ ዕለት፡ ፩፪ ሰዓታትን የያዘው፡ የብርሃን ጊዜ፡ መዓልት፥ ጨረቃ እንድትሠለጥንበት የተፈጠረችበት፡ ፩፪ ሰዓታትን የያዘው፡ የጨለማ ጊዜ፡ ሌሊትይባላል።

የመዓልቱ የጊዜ አቆጣጠር፡ የተፈጥሮውን ሥርዓት በመከተል፡ ከቀትር በፊትእና ከቀትር በኋላተብሎ፡ ፀሓይ፡ ጮራዋን በምትፈነጥቅበት፡ በንጋቱ ፩ ሰዓት ይጀምርና፡ በምትጠልቅበት፡ በምሽቱ ፲፪ ሰዓት ያበቃል፡ የሌሊቱም ጊዜ፡ እንደዚሁ፡ እስከእኩለ ሌሊት ድረስ፡ ከማታው፥ ከእኩለ ሌሊት በኋላ ደግሞ፡ ከሌሊቱእየተባለ፡ ጨረቃ ከምትታይበት፡ ወይም ጨለማው ከሚጀምርበት፡ ከምሽቱ፡ ፩ ሰዓት ይነሣና፡ ጎህ በሚቀድድበት፡ በንጋቱ ፲፪ ሰዓት ይቆማል።

በዚህ መሠረት የተደለደለችው፡ አንዲቱ ዕለት፡ ሰባት ስትኾን፡ ፯ቱ ዕለታት፡ ፩ ሳምንት ይኾናሉ።

የምዕራብውያኑ ግን፡ እንዲህ አይደለም። ምዕራባውያን፡ የሰሜኑንና የደቡብን የመሬት ዋልታ ተከትለው፡ በሰሜንና በደቡብ ክፍላተ ዓለማት፡ የሚኖሩ በመኾናቸው፡ ኢትዮጵያውያን፡ ክረምት፥ መፀው፥ በጋ፥ ጸደይ እንደሚሉት፡ የእነርሱም ዓመት፡ Winter(ዊንተር) Spring (ስፕሪንግ) Summer (ሰመር) Autumn (ኦተምን) በተባሉ፡ በአራት የተለያዩ ወራት ተከፋፍሎ፡ በክረምቱ፡ ሌሊታቸው፡ እስከ ፭ ሰዓታት የሚጨምርበት፥ እንዲያውም፡ ወደሰሜኑም ኾነ ወደ ደቡቡ የመሬት ዋልታ ጫፍ እይተጠጉ በኼዱ መጠን፡ የሚቀነሱት፡ ወይም የሚጨመሩት ሰዓታት እያደጉ ይኼዱና፡ ወደ መጨረሻው ጽንፍ ላይ ሲደርስ፡ ከናካቴው፡ ፮ ወራት ሙሉ፡ ሌሊት ብቻ፥ ወይም መዓልት ብቻ ይኾናል።

ይህም ማለት፡ ይህ ኹኔታ፡ በሰሜኑና በደቡቡ ክፍላተ ዓለም፡ በዓመቱ ውስጥ፡ እንዲህ ስለሚፈራረቅ፡ የክረምቱ ብርዳማ ጠባይ፡ ቀደም ብሎ እንደተገለጸው፡ የሰሜኑን ክፍል በሚያጠቃበት ጊዜ፡ በደቡቡ ክፍል ደግሞ፡ የበጋው ፀሓያማ ጠባይ ይሰፍናል ማለት ነው።

ይህ ብቻ ሳይኾን፡ በዓመት፡ ሁለት ጊዜያት፡ በየ፮ ወሩ፡ የሰዓት አቆጣጠራቸውን፡ እንደየክፍለ ዓለማቸው አቀማመጥ፡ በ፩ ሰዓት ያሳድጉታል፡ ወይም በ፩ ሰዓት ይቀንሱታል።

በኢትዮጵያውያን ዘንድ፡ ፯ቱ የሳምንቱ ቀኖች፡ የእግዚአብሔር፡ የሥነ ፍጥረት ሥራው፡ በተራና በቅደም ተከተል የተካሄደባቸውንና በቅዱሳት መጻሕፍት የተመዘገቡትን የዕለታት ስም እንደያዙ፡ የአዳምና ሔዋን ቋንቋ በሆነው፡ በግእዝ፡ አሐዱአንድ፡ ወይም፡ መጀመሪያ ቀንለማለት፡ እሑድ፥ ቀጥሎ፡ ሁለት፥ ወይም፡ ሁለተኛ ቀንለማለት፡ ማግሰኞ፡ ቀጥሎ፡ አራት፥ ወይም፡ የሰንበት መግቢያ፥ ወይም፡ የሳምንቱ ጊዜ፡ የሚጠልቅበት ቀንለማለት፡ ስድስተኛው ቀንዓርብ፥ በሰንበት ጌታ፡ በኢያሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ፡ ወደዘለዓለማዊነትከመለወጧ በፊት፡ ቀድሞ የነበረችበትን ሁኔታ ለማስታወስ፡ ሰባተኛዪቱን የሰንበት ቀንቅዳሜብለው ይጠርዋቸዋል።

ምዕራባውያን ግን፡ ለእነዚሁ የሳምንት ቀኖች፡ የሰጧቸውን የአረማውያን ጣዖታት አማልክቶቻቸውን ስም እንመልከት!

  • Sunday: Sun’s day (ሳንዴይ) ማለት የፀሓይ ቀን

  • Monday: Moon’s day (ማንዴይ) የጨረቃ ቀን፥

  • Tuesday: Tui’s day (ቱዩስዴይ)፡ ማለት፡ የጦርነቱ አምላክ፡ የቲዩ ቀን፥

  • Wednesday: Woden’s day (ዌድንስዴይ)፡ ማለት፡ የታላቁ አምላክ የውድን ቀን፥

  • Thursday: Thor’s day (ተርስዴይ)፡ ማለት፡ የነጎድጓዱ አምላክ፡ የቶር ቀን፥

  • Friday: Frigg’s day (ፍራይዴይ)፡ ማለት የታላቁ አምላክ፡ የዎድን ሚስት፡ የፍሪግስ ቀን፥

  • Saturday: Saturn’s day (ሳተርዴይ)፡ ማለት፡ የሰማዩ ኮከብ፡ የሳተርን ቀን።

በኢትዮጵያውያን ዘንድ፡ ፴ ዕለታት፡ ፩ ወር ሲኾኑ፥ ፲፪ ወራት እና ፭ ዕለታት ተሩብ ደግሞ፡ ፩ ዓመት ይኾናሉ። ፭ቱ ዕለታት ተሩብ፡ ጳጉሜይባላሉ። ጳጉሜ፡ የቃል ለቃል ትርጉሙ፡ ተውሳክጭማሪተረፍትርፍማለት ነው። ፲፪ቱ የምዕራባውያን ወሮች ግን፡ ፳፰፡ ዕለታትን፥ በየአራት ዓመቱም፡ ፳፱ ዕለታትን ከያዘውና (February – ፌብሩአሪ) ከሚባለው፡ ከአንደኛው ወር በቀር፡ እኩሌቶቹ፡ በ፴፥ የቀሩትም፡ በ፴፩ ዕለታት ተመድበው፡ ይህን በመሰለ የተዘበራረቀ መልክ ይቆጠራሉ።

በኢትዮጵያውያን በኩል፡ ከመስከረም እስከ ነሓሴ ድረስ ያሉት፡ ፲፪ቱ ወሮቻቸውና ጳጉሜ፡ እያንዳንዳቸው የሚጠሩበት ስም፡ ከእግዚአብሔር ከተሰጣቸው፡ የተፈጥሮ ጸጋቸው ጋር የተያያዘው ገጽታቸውን የሚያሳይ ትርጉም ያለው ሲኾን፡ በኢትዮጵያውያን የወራት አመዳደብ መሠረት፡ ከ September (ሴፕቴምበር) መስከረም እስከ እስከ August (ኦገሥት) ነሓሴ ድረስ ያሉት የምዕራባውያኑ ወሮቻቸው ግን እንደሳምንቱ ቀኖቻቸው ኹሉ፡ የተሠየሙት፡ በጣዖቶቻቸውና እንደአማልክት ይሰግዱላቸው በነበሩት ገዢዎቻቸው ስም ኾኖ ይገኛል።

ይኽውም፡ መስከረምን ከኢትዮጵያውያን፡ August(ኦገሥትን) ነሓሴን ደግሞ ከምዕራባውያን፡ ለምሳሌ ያህል ወስደን ብንመለከታቸው መስከረም፡ በኢትዮጵያኛ፡ ከረመወይም፡ ክረምትን አሳለፈከሚለው ግሥ ወጥቶ፡ ክረምቱ የሚያበቃበት፡ ማለትም፡ የዝናሙ ጠል አብቅቶ፡ የፀሓይ ብርሃን የሚፈነጥቅበት፡ የዓባይና የሌሎቹ ወንዞች ሙላት መጉደል የሚጀምርበትና ፍጥረቱ ኹሉ፡ ከተሸሸገበት በዓቱ እየወጣ፡ እርስ በርሱ የሚገናኝበት፡ አዲሱ ዓመት፡ የሚገባበት ማለት ነው። መስከረም ጠባየሚባለውም ለዚህ ነው። በምዕራባውያን ዘንድ ግን፡ August (ኦገሥት)፡ ስለወሩ ኹኔታ፡ ምንም ትርጉም የሌለው ኾኖ፡ እንደጣዖት ይመለክ ለነበረው፡ ለአረማዊው ርእሰ ነገሥት (Emperor): ለአውግሥጦስ ቄሣር፡ በመታሰቢያነት የተሰጠ ወር መኾኑን ብቻ ያስረዳል።

የኢትዮጵያውያን ዓመት የሚጀምረው፡ በመስከረም፡ የሚያበቃውም፡ በጳጉሜሲኾን፡ የምዕራባውያ ኑ ግን፡ በእነርሱ January (ጃንዋሪ)፡ ማለትም፡ በጥርይጀምርና፡ በDecember (ዲሴምበር)፡ ማለትም በታኀሣሥይጨርሳል። ስሙን በመታሰቢያነት፡ January (ጃንዋሪ) ብለው፡ ለዓመቱ የመጀመሪያ ወር የሰጡለት፡ Janus(ጃኑስ)፡ ለሮማውያን፡ ታላቁ ጣዖታቸው እንደነበረ፡ ቀደም ብሎ ተመልክቷል።

በኢትዮጵያውያን ዘንድ፡ ፬ ዓመታት፡ ፩ ዐውደ ዘመን ይኾናሉ። ይህም፡ እያንዳንዱ ዓመት፡ ፫፻፷፭ ከሩብ ዕለታት፡ ወይም ከ፮ ሰዓታት፡ ወይም ከ፲፭ ኬክሮስ ያለው ሆኖ፡ ዘመነ ማቴዎስዘመነ ማርቆስዘመነ ሉቃስእና ዘመነ ዮሓንስተብሎ ተሠይሟል፡ እነዚህ፡ የ፬ቱ ዓመታት ጳጉሜዎች ሰዓታት ሲደመሩ፡ ፩ ዕለት የሞሉና፡ በ፬ኛው ዓመት፡ በዘመነ ዮሓንስ መግቢያ፡ ፮ ዕለታት በመሆን፡ የባሕረ ሃሳቡ ቅመራ ይካተታል፡ የዘመን አቆጣጠሩም ዐውድ፡ እንዲህ በየአራት ዓመታቱ ይዘጋል።

ስለዚህ፡ የግሬጎሪወይም ግሬጎሪያንተብሎ የሚጠራው፡ የምዕራባውያን፡ የጊዜ አቆጣጠር ባህል፡ እንዲህ፡ ምስቅልቅሉ የወጣ በመሆኑ፡ በእርሱ ሰበብና ጠንቅ፡ ጽኑ የሆነው ሃይማኖታዊና ተፈጥሮአዊ መሠረት ያለው፡ የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ሥርዓት፡ ሊቃወስ ቀርቶ፡ ሊነካ እንኳ፡ ከቶ አይገባም።


Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: