Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘Ethiopian Art’

ቅዱስ ሚካኤል + ኢየሩሳሌም + ያልተባበሩት መንግሥታት + የኢትዮጵያ ድምጽ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 21, 2017

እነዚህ ድንቅ ሥዕሎች ከአሜሪካዋ ቦልቲሞር፣ ሜሪላንድ ዋልተርስ ቤተ መዘክር ድህረ ገጽ የተገኙ ናቸው። ከምስጋና ጋር።

ወደዚህ ድህረገጽ ዛሬ እንዴት እንደገባሁ አላውቅም፤ በወቅቱም ስለ ሌቀ መላእክት ሚካኤል የምፈልገው ነገር አልነበርም፤ ግን ያው ጠባቂያችን ሚካኤል በዛሬው ዕለት እንደ ድንገት ወደዚህ መራኝ። ይህ እራሱ ተዓምር በመሆኑ ቀኑን ሙሉ ተደስቼ ነበር የዋልኩት፤ በአልተባበሩት መንግሥታት የተከሰተውን አሳዛኝ ዜና እስከምሰማ።

የብዙ ጥንታውያን ሥዕሎችና ምስሎች ስብስብ በተለያየ መልክ ቢኖረኝም፡ እነዚህን አስደናቂ ሥዕሎች ግን ለመጀመሪያ ጊዜ ማዬቴ ነው። እንደዚህ ዓይነት የስብከት እና የቅዳሴ ሥርዓት እንደዚህ ከመሰሉ ድንቅ ባለቀለም ሥዕሎች ጋር ከ400 ዓመታት በፊት በሚያስገርም መልክ አባቶቻችን ሲፈጽሙ ነበር። በጣም አስደናቂና የሚያኮራ ነው!

በተጨማሪም ሁሉም ሥዕሎች ላይ የሚታዩት መልአክትና ቅዱሳን የኢትዮጵያውያን ገጽታ እንዲኖራቸው ተደርገው ነበር የተሠሩት። ፈረንጁም በአገሩ ይህን ነው ከአድናቆት ጋር እያሳየ ያለው። ታዲያ ይህን የሚያዩ ሠዓሊያን ወገኖች፡ መልአክቱንና ቅዱሳኑን ሁሉ ፈረንጅ አስመስለው አሁን ሲስሉ እጅግ በጣም አያሳዝንምን? አያንገፈግፍምን? ምን ነክቷቸው ይሆን? በእውነት፡ አባቶቻችንን ምን ያህል ቢንቋቸው ነው? የሚያሰኝ ጉዳይ ነው።

እነዚህ በድርሳነ ሚካኤል አነሳሽነት የተሠሩት ድንቅ ሥዕሎች የኢትዮጵያ ሥነ ጥበብ በአበበበት 17 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ ነበር በጎንደር ከተማ የተሠሩት። በወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥ ፍርድ ቤት እና ተጓዳኝ መኳንንቶች ቋሚ መኖሪያ በጎንደር አድረገው ነበር።

እነዚህ በብዙ ቀለማት ያሸበረቁና የሚያበሩ 49 ሥዕሎች የወቅቱን የበለጸገ የሥነ ጥበብ ባህል ያንጸባርቃሉ። የእጅ ጽሑፉ በሊቀ መላእክት ሚካኤል ተአምራት እና 49 ደማቅ ቀለም ባላቸው የእግዚአብሔርን ገጸባህሪያት በሚያሳዩ ሥርዓት ትምህርቶች ላይ ያተኮረ እንዲሁም በቅዱስ ሚካኤል የተፈጸሙ ተዓምራቶች አጣምሮ የያዘ ነው

የእጅ ጽሁፎቹ ክፍሎች እንደ ተለመደው በቅዱስ ሚካኤል ወርሃዊ በዓል ቀናት ይነበቡ ነበር እናም ሥዕሎቹ በምንባቡ ጎን አብረው ይቀርቡ ነበር

አርቲስቶቹ፡ እንደ ጥንታውያኑ የብራና ባለሞያዎች ሳይሆኑ፡ ልክ እንደ ሠዓሊዎች የሠለጠኑ ነበሩ። እናም የእነሱ ሥነ ጥበብ ከዘመናዊ የግድግዳ ሥዕሎች ጋር ሊዛመድ ይችላል ማለት ነው።

ከ አርባ ዘጠኙ ሥዕሎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦

  • + ቅዱስ ሚካኤል መካን የነበረችውን ሴት ልጅ እንድትወልድ ረዳት

  • + ቅዱስ ሚካኤል ለዓይነ ስውሩ ብርሃን ሲሰጠው

  • + ቅዲስ ሚካኤል እርኩስ መንፈስ ከቤተክርስቲያኑ ሲያስወጣ

  • + ቅዱስ ሚካኤል አንድ የተቸገረ ሰው የበዓል ቀኑን እንዲያከብር ሲረዳው

  • + ቅዱስ ሚካኤል በኃጢአተኞች ምትክ ሲለምን / ሲማልድ

  • + ሰማእት ኤፎሚያ (3ኛው ክፍለ ዘመን) ለሰይጣን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ስታሳዬው እንደ ቁራ ሸሽቶ በረረ፤ ከዛም፡ ሰይጣን በአራት ሴቶች ተምስሎ እንደገና ሲመጣ፤ ቅዱስ ሚካኤል በላዩ ላይ ወጣበት

Courtesy of The Walters Art Museum

የኢትዮጵያ ልጆች ይህችን የ ቅ/ ሚካኤል ዕለት እናስታውስ!

የድምጽ ሰጪ አገሮች ሰንጠረዡም በኢትዮጵያ ሦስት ቀለሞች፤ +አረንጓዴ፣ xቢጫቀይ ያሸበረቀ ነው። አረንጓዴ፤ አረቦች የሰረቁት የእስላም ቀለም ሆኗል፤ ቢጫ ገለልተኞች፣ ቀይ ደግሞ አመሪካና እስራኤል የደገፉት ናቸው። በጣም አስገራሚ ነው!

(የ ሄጌል ThesisAntithesisSynthesis ሞዴል)

ወንድሞቻችንን በባርነት ከምሸጡት፣ እህቶቻችንን ከፎቅ እየወረወሩ ከሚገድሉት አርቦች በማበር የኢትዮጵያን የድጋፍ ድምጽ በተባበሩት መንግሥታት እንድንሰጥ ተደርገናል። ዓጼ ኃ/ ሥላሴም ተምሳሳይ ድርጊት ከፈጸሙ በኋላ ነበር፤ ኢትዮጵያችን በጣም አስከፊ በሆነ መልክ እንድትራቆትና እንድትደቅ ሁለት ትውልድም እንዲጠፋ የተደረገው።

የግድ አሜሪካንና እስራኤልን መደገፍ የለብንም፡ ለዚህም እንደነ ቤኒን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኡጋንዳ፣ ኬንያ፣ ሌሶቱ፣ ማላዊ፣ ጊኒ ኤኳተሪያል፣ ፊሊፒንስ፣ ኮሎምቢያ፣ ፓናማ፣ አውስትራሊያ፣ አርጀንቲና፣ ቦስኒያ፣ ፖላንድ፣ ሮማኒያ ወዘተ የመሳሰሉት 35 አገሮች በገልተኝነት ድምጽ ከመስጠት መቆጠብ ነበረብን።

የሚያሳዝነው እስራኤልን ወይም አሜሪካን አለመደገፋችን ሳይሆን አረቦችን መደገፋችን ነው!

አገራችን ከፍየል አገራት ጋር አብራ መሰለፍ አልነበረባትም። ያልተባበሩት መንግሥታት በሊቢያ ስለሚካሄደው የባርነት ንግድና በእስላም አገሮች የሚታየው የክርስቲያኖች ጭፍጨፋን ልክ እንደዚህ በደንብ መውገዝ ነበረበት እንጂ ኢምባሲ ተዛወረ አልተዛወረ እንደ ትልቅ ነገር ተቆጥሮ የተለየ ሤራ መጠንሰስ አልነበረበትም። ወስላቶች!

እስራኤላውያን ለክፉም ሆነ ለበጎ በተለይ በኢትዮጵያውያን ላይ ልዩ የሆነ አትኩሮት ነው ያላቸው። ግብጽም፡ ልክ እንደ ቀድሞው በደስታ ጮቤ ትረግጣለች፤ ፍርሀት የተጫነው የመረጋጋት መመሪያ ሠርቶ አያውቅም።

800 ዓመታት በፊት በመሀመዳውያን ላይ ቅስም የሚሰብር ድል የተቀዳጀቸው ስፔይን (በዚህም፤ ኢትዮጵያ፡ ስፔይንና ፖርቱጋልን በመርዳት በይፋ የማይታወቅ ከፍተኛ ሚና ተጫውታለች፤ ሌላ ጊዜ..) ያው በካታላንውያን በኩል ኃይለኛ ፈተና ገጥሟታል፤ በዛሬው ዕለት በካታሎኒያም የተካሄደው ምርጫ ብዙ መዘዝ አለው። ካታሉኒያ + ቫሎኒያ + ባቫሪያ + ኤርትራ + ኦሮሚያ + ክሮአስያ + ስኮትላንድ + ቱርክ + ዩክሬየን + ኩቤክ  — እነዚህ ግዛቶች የአመጸኞቹ አለቃ ሰይጣን በክርስቲያን ሕዝቦች ላይ እንዲያምጹ ያዘጋጃቸው ግዛቶች ናቸው። በጌታችን ልደት ዋዜማም ይህ ሁሉ መከሰቱ ያለምክኒያት አይደለም።

ይህን የታህሳስ ፲፪ ፥ ፪ሺ፲ ዓ.ም ዕለትን በደንብ እናስታውስ።

 

የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ረድኤት በረከቱ አይለየን!!!

______

Posted in Ethiopia, Faith, Photos & Videos | Tagged: , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

Traditional Ethiopian Paintings and Folk Art

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 2, 2012

 

There are two styles in traditional Ethiopian paintings.  The first group includes artists who use the style found in old religious paintings in churches, manuscripts, or icons.  These paintings always include religious themes or stories from the bible or from the Kebre Negist, an addendum to the bible used in the Ethiopian Orthodox Church.  Some of the paintings are of a single subject while others have several panels featuring a story from the bible or Kebre Negist.

The second group of painting is distinguished by the bright colors, two-dimensional figures and the large eyes associated with many traditional Ethiopian paintings and folk art.  These folk paintings can be of a single subject or several panels illustrating telling a folk story, historical event, or bible story.  Most paintings done in this style are painted on stretched parchment.

For many years, most of the traditional paintings sold at St George Gallery came from Tadesse-Wolderegay and Priest Legessa, a well-known priest and traditional artist.  Since Priest Legessa’s death a few years ago, Itsub Dink, his daughter (Ethiopian priests can marry), has carried on his work and paints in the same style as her father.

These bright paintings are some of the best examples of African folk art and are a colorful addition to any décor.

Source: stgeorgeofethiopia.com

__

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: