Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • May 2023
    M T W T F S S
    1234567
    891011121314
    15161718192021
    22232425262728
    293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘COVID-19’

ዋው! | የታንዛኒያ ፍየሎችና ፓፓያ ኮሮና ቫይረስ ስለተገኘባቸው የመመርመሪያ መሣሪዎቹ አያስፈልጉም ተባለ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 7, 2020

የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት ጆን ማጉፉሊ የኮሮናቫይረስ ምርመራውን ትክክለኛነት ከተጠራጠሩ አንድ ቀን በኋላ ለኮሮኔቫቫይረስ ምርመራ ሀላፊነቱን የያዘው የታንዛኒያ ብሔራዊ የጤና ቤተሙከራ ከሃላፊነት ተነስቷል።

በብሔራዊ ላቦራቶሪ ውስጥ የተለያዩ እንስሳት ፣ ፍራፍሬዎችና የተሽከርካሪ ዘይት በምስጢር ከተሞከሩ በኋላ ፕሬዚደንቱ እንዳስታወቁት በፍየልና ፓፓያ ላይ የተካሄደው የኮሮና ፍተሻ አዎንታዊ ውጤቶችን በመመለሳቸው፤ ማለትም በኮሮናቫይረስ መለከፋቸውን በማስየቱ የሚደረገው ምርመራና የመርመሪያ መሣሪዎቹ ከንቱ ናቸው በዚህ መልክ ምርመራ ማድረግ አያስፈልግም ብለዋል።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም እንዳሉት በቫይረሱ ተለከፈዋል የተባሉት ሰዎች በበሽታው ላይታመሙ ይችላሉ። በቤተ ሙከራ መሣሪያዎች እና ቴክኒሻኖች ተአማኒነት ላይ ያላቸውን ጥርጣሬ በይፋ አሳይተዋል፡፡

_______________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Health, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

7/ ፯ሺ ዜጎቿን በኮሮና ባጣችው ጀርመን ዓብያተ ክርስቲያናት ተከፈቱ | በ ኢትዮጵያስ?

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 6, 2020

ቪዲዮው የሚያሳያው በዓለም ድንቅ ከሆኑት ካቴድራሎች መካከል አንዱ በሆነው በኮሎኝ ከተማ ካቴድራል ቅዳሴ ሲካሄድ ነው። ምዕመናን ቀስበቀስ ወደ ቤተ ክርስቲያን መግባት ጀምረዋል።

👉 ጀርመን

  • 👉 170,000 በቫይረሱ ተጠቅተዋል
  • 👉 130,000 ከፋይረሱ አገግመዋል
  • 👉 7,000 በቫይረሱ ሞተዋል

ጀርመናውያን በብዛት “ክርስቲያኖችን” ቢሆኑም ለበዓላት ካልሆነ ወደ ቤተ ክርስቲያን እምብዛም አይሄዱም። እንደዛም ሆኖ፤ ለሰንበትና ለበዓላት የገባያ ቦታዎች ዝግ ናቸው።

👉 ኢትዮጵያ

በአውሮፕላን ያስገቡት ካልሆነ በቀር ኮሮና የሚባል ቫይረስ በኢትዮጵያ የለም፤ በሌላ ነገር እንጅ በኮሮና የሞተ ሰውም የለም። ቤተ ክርስቲያን የሚያዘወተረው የአማኞች ቍጥር በዓለም ከፍተኛው እንደሆነ በሚነገርባት ክርስቲያን ኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ዘግተዋል። ታሪክ የማይረሳው ትልቅ ቅሌት!

___________________________

Posted in Ethiopia, Faith, Health | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ጉድ ነው! ነርሷ አመለጣት | “በቂ ሕዝብ በኮሮና ገና አልበከልንም”

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 6, 2020

የብሪታኒያ ፎረንሲክ ነርሷ ራሄል ሴለር ለቢቢሲ በሰጠችው ቃለ መጠይቅ ነው አምልጧት የተናገራቸው። “ሰው፡ በተለይ አረጋውያን ገና መበከልና መገደል አለባቸው” ማለቷ ነው። እነዚህ አረመኔዎች!

______________________________

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Health, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

አረቦች በኮሮና የተለከፉ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሃገራችን እንደሚልኳቸው ከ፯ ዓመታት በፊት አስጠንቅቀን ነበር

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 27, 2020

👉 ልብ እንበል፦ በፈረንጅ 2012 .ም – አሁን በእኛ 2012 .ም ነው

ቪዲዮው የሚያሳየው እ..አ በ2013 .ም በሳውዲዎች የተካሄደውን የኢትዮጵያውያንን ጥረፋ ነው (200,000 ኢትዮጵያውያን)። በሕይወት ካሉ ዛሬ ምን ዓይነት ሁኔታ ላይ ናቸው?

ኢትዮጵያ ውጥረት ሲገጥማት (በመለሰ ዜናዊ ላይ የመንግስት ግልበጣው)አረቦቹ ለዚህ ጊዜ እንዲዘጋጁ የተደረጉትን ምስኪን ኢትዮጵያውይንን በቫይረስ አጋንንት እየሞሉ ልክ እንደ ባዮሎጂያዊ መሣሪያ በመጠቀም ወደ ኢትዮጵያ ይልኳቸዋል።

👉 ..አ በ2012 .ም ፡ ላይ ሜርስ የተሰኘው ኮሮናቫይረስ በሳውዲ አረቢያ መቀስቀሱን እዚህ ላይ አውስተን ነበር።

👉 Saudi Arabia Confirms Four More Coronavirus Cases

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 17, 2013

ይህ ኮሮና ቫይረስ የተቀሰቀሰው በአውሮፓውያኑ በልግ 2012 .ም ላይ ነበር። ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ እና አቡነ ጳውሎስ በእነ አላሙዲን በተገደሉ በአንድ ወር ውስጥ ቫይረሱ መስፋፋት ጀመረ። ብዙም ሳይቆይ ሳውዲ አረቢያ፤ ልክ ሰሞኑን በዘመነ ኮሮና እንደምታደርገው (5ሺ ኢትዮጵያውያን በካርጎ ወደ ኢትዮጵያ ተልከዋል ፣ በቦታቸው 5ሺ በጎችና ፍየሎች ከኢትዮጵያ ወደ ሳውዲ ተልከዋል፤ ልብ በል ወገን!)ያኔም በመጀመሪያው ዙር እስከ ሁለት መቶ ሺህ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ኢትዮጵያ ጠረፈች (ቪዲዮው)

👉 ይህን አስመልክቶ በጊዜው በጦማሬ እንደሚከተለው በተከታታይ አቅርቤው ነበር፦

👉 Saudi Arabia Doubles Down on Abuse

እነዚህ የሳዑዲ ፍጡራን ምን ያህል ደካሞች፣ ርጉሞች እና ጨካኞች እንደሆኑ አገር ቤት ያለው ወገናችን በደንብ አድርጎ የሚገነዘበው አይመስለኝም።

ሁላችንንም በጣም ሊያሳስበንና በተለይ ደግሞ ኢትዮጵያውያን የሕክምና ባለሙያዎች ተገቢውን ትኩረት ሊሰጡት የሚገባው ጉዳይ፡

በቅርቡ በአረብ አገሮች የተስፋፋውና “ኮሮና” የሚባለው መቅሰፍታዊ የግመል ቫይረስ ነው። ይህ ቫይረስ ወይም ተመሳሳይ የባዮሎጂ መርዝ ምናልባት በሚመለሱት ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ዓማካይነት በአገራችን ተስፋፍቶ ሕዝባችንን የበለጠ እንዳያዳክምብን ጉዳዩን በቅርብ እየተከታተልን ማጥናት ይኖርብናል። ሳዑዲዎች ኢትዮጵያውያኑን ለማባረር የተዘጋጁት ዱሮ ነው። የኢትዮጵያውያኑ ‘ህገወጥነት‘ ጉዳይ ምክኒያቱ እንዳልሆነ ብዙዎቻችን የምናውቀው ነው።

ቁጥራቸው እየጨመረ የመጣው የአውሮፕላን በረራዎችስ? የሳዑዲ አውሮፕላኖች ለዓለም ዓቀፉ የ Chemtrails ሴራ አስተዋጽዖ በማበርከት በአገራችን የዓየር ክልል መርዙን የመርጨትስ ጥሩ አጋጣሚ ፈጥሮላቸው ይሆንን? ሲ አይ ኤ በቻይና አካሂዶታል ሲባል እንደነበረው። ወደ ኢትዮጵያ የሚበሩ የአረብ አውሮፕላኖች ሁሉ በዚህ የ Chemtrails ሴራ ሊጠረጠሩ ይገባቸዋል። ቀይ ባሕርን በእጃቸው አስገብተዋል፡ የቀሯቸው ዓየራችን፣ ውሃችን እና መሬታችን ናቸው።

ባለፈው ጊዜ የመከላከያ ምኒስትራቸው ግብጽ ውስጥ ፀረ–ኢትዮጵያ የሆነውን ንግግር ማሰማቱም ከዚህ ሁሉ ሁኔታ ጋር የተያያዘ ነው። ኢትዮጵያውያን በሳውዲ ዕብድ ውሾች በየመንገዱ መታደን በጀመሩት ዕለት፡ የ Skull & Bones ምስጢራዊ ድርጅት ዓባል፡ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ በሳዑዲ ዓረቢያ ጉብኝት እያደረጉ ነበር። ስለሁኔታው የተነፈሱት ነገር የለም።

የዓለም ዓቀፋዊ ምስጢራዊ ቡድኖች ሁሉ መናኽሪያዋ ሳዑዲ የሰይጣን መቀመጫ ሆና በማገልገል ላይ ትገኛለች። ይህን መናኽሪያ ሊያወድም እና ሊያጠፋ የሚችለውም “ቀጫጫ እገር ያለው ኢትዮጵያዊ” እንደሚሆን እራሳቸው ሙስሊሞች ቅዱስ ናቸው የሚሏቸው ሃዲቶች ይተነብያሉ።

ቀደም ሲል መሪዎቻችንን ገድለው ብሔራዊ አለመረጋጋትን በመፍጠር የዋሐቢዎችን እንቅስቃሴ ባገራችን ለማጠናከር ሞከሩ። አሁን ደግሞ በሚቀጥለው እርምጃቸው ይህ በታሪክ ከፍተኛ ቦታ መያዝ የሚችለው የስደተኞች እንደገና ወደ ኢትዮጵያ መጉረፍ ለዚህ ህልማቸው አስተዋጽዖ ያበረክታል ብለው ያምናሉ። ሕብረተሰባችንን በሁሉም አቅጣጫ በመተናኮልና በሕዝባችን ላይ ውጥረት እየፈጠሩ በማደናገር ዲያብሎሳዊ ህልማቸውን እውን ለማድረግ መውደቂያቸው እስኪደርስ ይታገላሉ። የመውደቂያቸው እና ኤርታዓሌ የእሳት ጉድጓድ ውስጥ የመግቢያቸው ቀን በጣም ተቃርቧል!

የሳዑዲ ዜጋ እና ከልዑሉ ቀጥሎም ሁለተኛው ኃብታም የሆኑት ሸህ ሙሀመድ አላሙዲ የኢትዮጵያውያኑን እጣ በሚመለከት ምን እያሉ ይሆን? ሳዑዲዎች በወገኖቻችን ላይ ለብዙ ዓመታት ስላደረሱት የከፋ በደል እንዲሁም ስለ ዋሃቢዝም ርዕዮተዓለም የሚሉትን ለመስማት በጣም ነው የጓጓሁት። ይህን በተመለከተ ለኢንተርቪው የሚጋብዛቸው ኢትዮጵያዊ ይኖር ይሆን?

ወገናችንን ወደ ሳዑዲ የሚልኩ፡ ኢትዮጵያውያንን ከሳዑዲ እንዲባረሩ ካደረጉት የሚለዩ አይደሉም!”

👉 Stay Away from Camel Milk and Egyptian Tomb Bats

A deadly MERS is a coronavirus, part of a family of microbes that includes SARS (severe acute respiratory syndrome) is sweeping the Middle East — could it go global?

The virus first emerged in the eastern oasis town of Al-Ahsa in the spring of 2012. But not until April 2014 did it seem likely to be a pandemic: That is to say, nearly halfof all cumulative cases since 2012 have occurred in Saudi Arabia in April 2014. “Jeddah: the novel coronavirus situation is reassuring and thankfully does not represent an epidemic.” The daily tollsof cases and deaths have been increasingly confusing

___________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Health | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ማዳጋስካር ከአሪቲ ለኮሮና መድኃኒት አገኘሁ ትላለች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 24, 2020

የማዳጋስካር ፕሬዝዳንት አንድሪ ራጆይሊና ና በ COVID-19 የሚሠቃዩ በሽተኞችን ማከም እና ማዳን ይችላል ብሎ ያመነበትን መድሃኒት በይፋ ጀምረዋል፡፡

በማለጋሲ የተተገበረ ምርምር ተቋም እና COVID ኦርጋኒክ የሚል ስያሜ የተሰጠው መድኃኒት የተገኘው በማደጋስካር ደሴት የወባ በሽታን ለመዋጋት ከሚረዳው ከ አሪቲ ቅጠል ነው ።

ፕሬዝዳንቱ እንዳሉት “ሁሉም ሙከራዎች እና ምርመራዎች የተካሄዱ ሲሆን የሕመሙ ምልክቶችን የማስወገድ ውጤታማነቱ መረጋገጡና በማዳጋስካር ለሚገኙ ህመምተኞችም ሕክምና መደረጉን አረጋግጠዋል”።

____________________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Health, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: