Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘Apostle Matthew’

Apostle Matthew in Ethiopia | ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ በአክሱማዊቷ ኢትዮጵያ | በፍርድ ቀን፤ ከ፪ሺ ዓመት በኋላ፤ “ወንጌል አልተሰበከልንም” ማለት የለም

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 22, 2022

✞✞✞

ጥቅምት ፲፪/ 12፤ የሐዋርያውና ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ በዓለ ዕረፍቱ ነው፤ ከቅዱስ ማቴዎስ ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡

💭 ፊልሙን ከዚህ ድንቅ ጽሑፍ ጋር እናነጻጽረው፦

👉 በ መሪራስ አማን በላይ

የዓለም መድኃኒት እየሱስ ክርስቶስ እኔን ማቴዎስን መርጦ ተከተለኝ አል እኔም ስላመነታ ተከተልኩት የመዳን ተስፋ የሆነውን የወንጌሉን ቃል እንድንሰማና ከእርሱ አፍ የሰማሁትንም ለዓለም እንዳሰማ ልኮኛል።

መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ሊያድን ከእግዚአብሔር አብ የመጣ ከእርሱም ሌላ አዳኝና መሐሪ ወደ እግዚአብሔር መንግሥትም የሚያገባ እንደሌለ የአየሁትን ልመሰክር የሰማሁትን ቃል ለእናንተ ለአሰማ ከቃሉ የተነሣ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ትሆኑ ዘንድ በስሙም ትጠመቁ ዘንድ ልኮኛል። ከአብና ከልጁም ከእኛም ህብረት እንዳላችሁ ያንጊዜ ታውቃላችሁ፤ ዓለሙ ግን የፈጠረውን ተጣሪውን ትቶ ላልፈጠረው ምህረት የአደረገለትን ጌታውን ትቶ ሥቃይንና መአትን ለሚያመጣበት ለክፉ መንፈስ እየተገዛና የክፉ መንፈስ ባሪያ በመሆን የኃጢአትን ንጉሥ ዲያብሎስን እያገለገለ ይገኛል።

ይህ ክፉ መንፈስ በሰዎች ልብ ላይ መርዙን እንደረጨ ሁሉ እንዲሁ በእግዚአብሔር ልጆች ላይ ደጋኑን ወጥሮ ቀስቱን እንደቀተረ ነው። አንዳንዶች ወገኖች ለእርሱ ሲማረኩለት ጥቂቶችም የሆኑ የእግዚአብሔር ምርጥ ሕዝቦች ከፍጹም እምነታቸውና ከመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የተነሣ በጸሎት ድል ያደርጉታል፡ በጾምም ያሸንፉታል ያሳፍሩታልም። ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣው ለእግዚአብሔር ልጅ ለእየሱስ ክርስቶስ ታማኝ ሠራዊቱ ናቸው። መንፈሱን ተላብሰዋል፣ ጸጋውን ተሞልተዋል፣ ኃይሉንም ታጥቀውታል። ሥልጣንም በአፋቸው ተሰጥቷል። እኒሁ እናንተም የእግዚአብሔር አብን ምህረት የልጁንም የእየሱስ ክርስቶስን አዳኝነት የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ልትቀበሉትና ልትለብሱት ለመጣችሁ ሁሉ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንላችሁ። የልጁም የእየሱስ ክርስቶስ ፍቅር ይፅናላችሁ። አሜን።

እቴ ህንድኬ ዣን ንግሥተ ነገሥታት ዘኢትዮጵያ በሆነች በአሥራ አንደኛው ዘመነ መንግሥትዋ ከእየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርት አንዱ ቅዱስ ማቴዎስ በመርዌ ከተማ የሚኖሩትን ህዝቦች ቃለ ወንጌል እየሰበከ አስተምሮ ማጥመቁን ሰማች፤ ይዘውት ወደ እርስዋ እንዲመጡ መልእክተኞችን ወደ ወንጌላዊ ማቴዎስ ላከች፡ ነገር ግን ስለክርስቶስ መወለድና ብዙ ታእምራትንና ድንቅ የሆኑ ሥራዎችን እየሱስ ክርስቶስ መሥራቱን ሰምታ ስለነበረ የእየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ነው ሲሏት መልኩን ለማየት የሚያስተምረውንም ለመስማት ጓጉታ እርሱ የእግዚአብሔር አገልጋይ ከመምጣቱ እኔ መሄድ አለብኝ ብላ በብዙ ሺህ ሠራዊት ታጅባ ወደ መርዌ /መርዋ/ በ70 ዓ.ም. ሄደች።

በዚያም ቅዱስ ማቴዎስን አግኝታ እንዲህ አለችው፦

“እየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እኛ እንደተላከና የሰላም አለቃ የዘለዓለም አባት እንደሆነ ከነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተነሣ አምናለሁ፤ ነገር ግን በውኃ ጥምቀት ከእግዚአብሔር መወለድን የእግዚአብሔር ልጅ መባልን አላውቅም ነበር፡ አሁን ግን አንተን ወደ እኛ የላከህና ከአንተ ላይ የአለ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ከስብከትህ የተነሣ ገለፀልኝ፡ የምትነግረን ቃለ ወንጌል ህይወት መድኃኒት እንደሆነ አወኩ በእርሱም አመንኩ ስለዚህ አጥምቀኝ።” አለችወ።

ቅዱስ ማቴዎስም እግዚአብሔር ወደ እርሱ እንደላካት አውቆ በደስታ ከሠራዊትዋ ጋር ወደ ግዮን ወንዝ ወረዱ ከዚያም ከእርሱዋ ጋር የነበረው ሠራዊትና መኳንንት ሁሉ በእየሱስ ክርስቶስ ስም አጠመቃቸው። እንዲህ ሲል፦

“በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠቃችሁ አለሁ!” እያለ።

እቴ ህንደኬ ዣን እንደህዝብዋ ተጠመቀች፤ ፍጹም ክርስቲያን ሆነች፤ ከዚያም ቅዱስ ማቴዎስን ከደቀ መዛሙርቶቹ ጋር ወደ አክሱም አምጥታ አክሎስ የሚባለውን ባልዋን ልጆችዋን ቤተሰብዋን ሁሉ በእየሱስ ክርስቶስ ስም አስጠመቀች። ቅዱስ ማቴዎስ በአክሱም አድርጎ ወደ ኢየሩሳሌም ሄደ፤ ከበርቶሎሜዎስ ቀጥሎ ለመጀመሪያ ጊዜ የኑብያን፣ የኢትዮጵያንና የናግራንን ሰዎች የአጠመቀ ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት አንዱ ወንጌላዊ ማቴዎስ ነው።

እንደዚህም ሆነ እቴ ህንደኬ ዣን ክርስቲያን በሆነች በአሥራ ሦስት አመትዋ አቡሳውያን /አበሾች/ የሚባሉት የአክሱም የአዶሊስ ሕዝቦችና ፈላስያን /ፈላሾች/ በሌዋውያን ምክር ወንድሙዋን ንጉሠ ባህር ዘዝቃሌስ ተብሎ የነበረውን ከተብን አፄ ባህር ሰገድ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ብለው በበላዩዋ ላይ አነገሡት፤ እቴ ህንደኬን ዣንና አክሎስ ልጆቸዋን ገድለው አቃጠሏት። እርሷም በሰማእትነት በሰማንያ ሦስት /83/ በነገሠች በ24 ዘመነ መንግሥቱዋ አረፈች።

አፄ ባህር ሰገድ ተብሎ በነገሠው በከተብ ዘመነ መንግሥት እየሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ክርስቶስ ተወልዶአል ብሎ የሚያስተምርና የሚአምን ሰው ቢገኝ እንዲገደል በአዋጅ ተነገረ።

የእስራኤል ልጆች የሆኑ ሌዋውያን ካህናት እየሱ ክርስቶስም አይደለም ስሙንም መድኃኒት አይደለም ለማለት “ኢየሱስ” እንጂ “እየሱስ” ብላችሁ አትጥሩ ብለው በምኩራብ በአደባባይ በቢተ መቅደስ በገበያ አስተማሩ።

እግዚአብሔርም የእስራኤልን ልጆችን ጥጦስ የሚባለውን አስነስቶ በጭካኔ እንደገደላቸው ሁሉ እንዲሁ የባህር ሰገድን መርከብ ሠራተኞችና በአዶሊስ በዳህቂቅ የሚኖሩትን ቤተ እስራኤል ሂክሶስ የሚባሉት የግሪኮችን ሰዎች አስነስቶ አስገደላቸው።

ንጉሠ ነገሥቱ ባህር ሰገድ ክርስቶስ እየሱስ በተወለደ 105 መታራ ከሚባለው አገር ላይ ከግሪኮች ከሮማውያን ጋር ጦርነት አድርጎ ተማርኮ በ81 ዓመት እድሜው በነገሠ በ22 ዘመነ መንግሥቱ ሞተ።

አንዳንድ ጎሣዎችና በጎሣዎች ውስጥ የሚገኙ ነገዶች ቃለ ወንጌል ያልተሰበከላቸው በጨለማ ዓለም ውስጥ ከመኖራቸው የተነሣ ከንቱ የሆነ አምልኮት ያመልኩና ለሚያመልኩት ነገር እንስሳና አእዋፍ ዶሮ ያርዱለት ነበር። ከዚያም አልፈው ሰውን አስረው እንደ እንስሳ የሚያቀርቡና የሚሰው ነበሩ። የሚያመልኳቸው ተራራዎች ዛፎች ሸለቆዎች ኮረብታዎች አራዊቶች ነበሩ። እንደዚሁ አስቀያሚ መልክ ያላቸው ቅርጾችን ያመልኩባቸው ነበር።

ነገር ግን የሰው ልጅ ክቡር ፍጥረት እንደሆነ ከሁሉም በላይ መሆኑን የሚያምኑና ሁሉን የፈጠረና ቻይ ጌታ እግዚአብሔር ብቻ አንድ አምላክ እንደሆነ በነቢያት ላይ አድሮ ለሰው ልጆች ህግና ሥረአት እንዲኖራቸው የፈቀደ ወይም የአዘዘ ትእዛዙንም የሚፈጽሙ የመልከ ጼዴቅ ካህን ዘሮች የእግዚአብሔር ልጆች ተብለው የሚጠሩ ኢትዮጵያውያን ብቻ ነበሩ። በኋላ ዘመን ደግሞ የአብርሃም ዘሮች በሙሴ አማካኝነት አንድ እግዚአብሔርን ማምለክ ጀመሩ። ከዚህ በኋላ ነው ሁለቱ ጎሣዎች አንድ እግዚአብሔርን በማምለክና በማመን ሲኖሩ የአለም መድኃኒት እየሱስ ክርስቶስ በቤተ ልሔም በተወለደ ጊዜ ሊሰግዱለት ሄደው ከሌላው ዓለም በፊት የተገኙትና ገጸ-በርከት አቅርበው ወደ ሀገራቸው በሰላም የተመለሱ።

አሁንም እኛ ኢትዮጵያውያን የክርስቶስን ትእዛዝና ትምህርት የተቀበልን እንደ ኃዋርያት ማለት ብሉያት መጽሐፍትን አስቀድመን እንደተቀበልን፡ መጽሐፍተ አዲሳትንም ወዲያውኑ ነው የተቀበልንና አምነን በጌታችን በእየሱስ ክርስቶስ ስም የተጠመቅነው፤ በስሙ ክርስቲያኖች የተባልነው እንጂ ሐዲሳትን መጻሕፍትን ብቻ እንደተቀበሉት እንደ አሕዛቦች አይደለም። ለዚህ ሁሉ ምስክራችን ፈጣሪያችን እግዚአብሔርና እግዚአብሔር ያዘዘው የአምልኮታችን ሥርአት ነው። እሄውም የማይታየው አምላክ በነቢያት ሰው እንደሚሆን አስቀድሞ መነገሩ በሐዋርያት ሰው መሆኑ መሰበኩን የሚያበስሩትን ብሉያትና ሐዲሳትን /በማስማማታችን/ በማዋሐዳችን እምነታችን ተዋሕዶ ሃይምንት ተብሏል። ምስጢሩም ቃል ሥጋ በመሆኑ የነቢያት ትንቢት በመፈጸሙ ተዋሕዶ ሃይማኖት አሰኝቶታል።

እሄን ክብርና ጸጋ ለሰጠን ለአንድ እግዚአብሔር የአምልኮት ምስጋናና ሥግደት ይገባዋል። እግዚአብሔር ለዘለዓለም ለሰው ልጆች ሰላምንና ፍቅርን ሕብረትንም ይስጠን። ምህረቱና ቸርነቱም በሰማይ እንደሆነ በምድርም ይሁን። አሜን።

______________

Posted in Ethiopia, Faith, Saints/ቅዱሳን | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

The Life of Saint Matthew the Apostle and Evangelist — ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 30, 2015

The Holy Apostle and Evangelist Matthew, son of Alphaeus, was a tax collector. When the Lord said, “Follow Me,” Matthew left his tax booth and followed Him. After that, he prepared a reception for the Lord in his home and thus provided the occasion for the Lord to express several great truths about His coming to earth. After receiving the Holy Spirit, the Holy Apostle preached the Gospel to the Parthians, Medes and Ethiopians. In Ethiopia, he appointed his follower Platon as bishop, and withdrew to prayerful solitude on a mountain, where the Lord appeared to him. Matthew baptized the wife and the son of the prince of Ethiopia, at which the prince became greatly enraged and dispatched a guard to bring Matthew to him for trial. The soldiers returned to the prince saying that they had heard Matthew’s voice, but could not see him with their eyes. The prince then sent a second guard. When this guard approached the apostle, he shone with a heavenly light so powerful that the soldiers could not look at him; filled with fear, they threw down their weapons and returned. The prince then went himself. Matthew radiated such light that the prince was instantly blinded. However, the holy apostle had a compassionate heart; he prayed to God, and the prince was given back his sight. Unfortunately, he saw only with physical eyes and not spiritual eyes. He arrested Matthew and subjected him to cruel tortures. Twice, a large fire was lighted on his chest, but the power of God preserved him alive and unharmed. Then the apostle prayed to God and gave up his spirit. The prince commanded that the martyr’s body be placed in a lead coffin and thrown into the sea. The saint appeared to Bishop Platon and told him where the coffin bearing his body could be found. The bishop retrieved the coffin with Matthew’s body from the sea. Witnessing this new miracle, the prince was baptized and received the name Matthew. After that, the prince left all the vanity of the world and became a presbyter and served the Church in a God-pleasing way. When Platon died, the Apostle Matthew appeared to the presbyter Matthew and counseled him to accept the episcopacy. He accepted the bishopric and, for many years, was a good shepherd until the Lord called him to His Immortal Kingdom. St. Matthew the Apostle wrote his Gospel in the Aramaic language. It was soon after translated into Greek and the Greek text has come down to us, while the Aramaic text has been lost. It is said of this evangelist that he never ate meat, but only vegetables and fruit. – adapted from the Prologue of Ochrid

The Apostolic History of Abidas, records Matthew staying in Ethiopia for 23 years, founding churches, ordaining a priesthood and converting the entire royal family.

Equally there is mystery about his death. The Apostolic History of Abidas has him being stabbed in the back by a soldier, whereas the sixth century Martyrdom of Matthew has him being crucified and then burnt to death at the hands of a tribe of cannibals. Clement of Alexandria’s account has him dying of old age around AD90

ቅዱስ ማቴዎስ ማነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የማቴዎስ ወንጌልን የጻፈው ከ12ቱ ሐዋርያት መካከል አንዱ የሆነው ቅዱስ ማቴዎስ ነው። “ማቴዎስ” ማለት የእግዚአብሔር ስጦታ ማለት ነው። 12ቱ ሐዋርያት ስም ዝርዝር የሚገኘው ከአራቱም ትቅሶች ውስጥ ማቴዎስ የሚለው ስም ተመዝግቦ ይገኛል። ማቴ 102-4

የማቴዎስ ወንጌል የተጻፈው በ41 .ም መሆኑ ነው። ይህም ዘመን የማቴዎስ ወንጌል ከአራቱም ወንጌላት እንዲሁም በጠቅላላ ከሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ሁሉ በቅድሚያ የተጻፈ እንደሆነ ያሳያል።

ቅዱስ ማቴዎስ የጌታን ነገር በእብራይስጥ ቋንቋ ጽፏል።

የማቴዎስ ስሙ በራሱ ወንጌል “ማቴዎስ” ተብሎ ሲጠራ በማርቆስ እና በሉቃስ ወንጌላት ውስጥ በሚገኘው ትይዩ ታሪክ ደግሞ “ሌዊ” ተብሎ ተጠርቷል።

ከትንት ጀምሮ ባለው ታሪክ እና ትውፊት መሠረት “ማቴዎስ” እና “ሌዊ” ከቀድሞ ጀምሮ ይጠራበት የነበረው ስሙ “ማቴዎስ” ደግሞ ጌታን ከተከተለ በኋላ የተጠራበት ስሙ እንደሆነ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ያስረዳሉ።

የማቴዎስ ነገድ

ከይሳኮር ነገድ የሆነ፤ ከናዝሬት ሃገር የሆነ

የአባቱ ስም ዲቁ

የእናቱ ስም ካሩትያስ

በዚህ ታሪክ መሰረት የማቴዎስ ነገዱ ነገደ ይሳኮር ሃገሩ ደግሞ ናዝሬት እንደሆነ ስለቤተሰቡ ደግሞ አባቱ ዲቁ እናቱ ደግሞ ከሩትያስ እንደምትባል ተገልጧል

ነገር ግን በማርቆስ ወንጌል ውስጥ የማቴዎስ አባቱ “እልፍዮስ” እንደሆነ ተመዝግቧል (ከዚያ አልፎም በመቅረጫው የተቀመጠ የእልፍዮስ ልጅ ሌዊን አየው የሚል ነው) ማር 214 ስለዚህ በመቅድመ ወንጌል የተገለጠው “ዲቁ” የሚለው ስም ምናልባት “የማቴዎስ” አባት “እልፍዮስ” ሌላ ስሙ ሊሆን ይችላል።

ምንጭ

__

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , | Leave a Comment »

Ethiopia: The First Christian Nation?

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 5, 2013

CreationBible2

My note: Our forefathers were confident enough to answer it with YES! But the question whether Pope Pius XI was defender of Ethiopia — historical sources indicitae the contrary, that Pope Pius XI recognised Italian sovereignity over Ethiopia

For centuries, historians have widely accepted the argument that Armenia was the first Christian nation. This important claim has become a source of national pride for Armenians and has remained virtually undisputed for centuries — until now.

Armenians will likely be up at arms when they learn that a new book — “Abyssinian Christianity: The First Christian Nation?” — is challenging their claim, presenting the possibility that Abyssinia (modern-day Ethiopia and Eritrea) was the first Christian nation.

The Acts of the Apostles describes the baptism of an Ethiopian eunuch shortly after the death of Christ. Eusebius of Caesaria, the first church historian, further tells of how the eunuch returned to his land to diffuse the Christian teachings.

And the earliest Ethiopian monastic tradition is linked to the account of the Holy Family visiting Ethiopia, centuries before the Christian monastic movement emerged. According to the legend, the Child Jesus and the Virgin Mary were transported from Egypt on a silver cloud. Their arrival symbolized the renewal of the Covenant, which began when Menelich brought the Ark from Jerusalem to Ethiopia.

Continue reading…

__

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | 2 Comments »

 
%d bloggers like this: