Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • March 2023
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    2728293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘Alem Dechasa’

ርግቢቱ ዓለም – The Scared Pigeon

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 19, 2012

 

ዓለምእህታችን እ. . አ በማርች 14 2012 .ም ከንጋቱ 1200 ሰዓት ላይ ነው ያረፈችው ተብሏል። ወገኖቻችንና አንዳንድ ብሩክ የሆኑትን የዓለማችን ነዋሪዎችን ያሳዘነው የዓለም አሟሟት እጅግ በጣም ልዪ የሆነ ነገር በሁላችን ዘንድ ሊፈጥር ችሏል። ከሁለት ወራት በፊት ወደ ቤይሩት ከተማ ብቅ ያለችው እህታችን ኃይለኛ የሆነ መልዕክት ይዛልን ነበር ወደዚያኛው ዓለም ያለፈችው። በዓለማችን በመከራ ማዕበል የማይንገላታ ሰው የለም፤ አረመኔ በሆኑት የአረብ ሕዝቦች እጅ የተያዘ ደግሞ ከየተኛውም የዓለም ክፍል በይበልጥ በሥጋም ሆነ በነፍስ እየተቀጠቀጠ ነው ለመኖር የሚበቃው። መከራ የምንቀበለው ነገ በገሃነም እሳት ሳይሆን ዛሬ በምድር ሳለን መሆኑ ትንሽ ሊያጽናናን ይገባል። ለዚህም ነው እህታችን ዓለም በዚህች ምድራዊ ሲኦል በእግረ አጋንንት ተረገጠው ለሚኖሩት እህቶቻችን ሁሉ አሁን መልዕክተኛ ሆና የቀረብችልን። መቼም በመከራና ችግር ጊዜ ድንቅ ነገር ይመጣልና እምብዛም መደነቅ የለብንም። የፈጣሪ ክብር ሲገለጥ ሐሴት በማድረግ ደስ ሊለን ይገባል፡ መንፈሱ በኛ ላይ አርፏልና።

ላይ ቪዲዮው ላይ የምትታየውን ርግብ ያነሳኋት ባለፈው ሣምንት፡ በማርች 14፡ ልክ ከቀኑ 1200 ሰዓት ላይ ነበር። ርግቢቱ በመኖሪያ ቤቴ በመስኮት በኩል ገብታ ጋራጅ መውረጃ ላይ ቁጭ ብላ ነበር ያገኘኋት። እኔን ስታይ እየተንደፋደፈች ወደላይ በመብረር ከቤቱ ለመውጣት መስኮቱ ጋር ትጋጭ ነበር። እኔም ቆም ብየ ለ10 ደቂቃ ያህል ከታዘብኳት በኋላ ልረዳት ጠጋ አልኩኝ። መጀመሪያ ላይ ለመሸሽ ብትሞክርም በመጨረሻ ይዣት በመስኮቱ ላወጣት ችያለሁ።

የርግቢቱ ሁኔታ፡ በዚያ ቀን በጣም ስታሳስበኝ የነበረችውን የእህታችንን፡ የዓለምን ሁኔታ ያሳየኝ መስሎ ነበር የታየኝ። ርግቢቱ ከአካባቢዋ አምልጣ የሆነ ነገር ለማግኘት ወደ ቤቱ ገባች፡ ግን ቤቱ ውስጥ ምንም ነገር ስላላገኘች ወደ መጣችበት ለመመለስ ፈለገች፡ ሆኖም የገባችበት መስኮት ዘንበል ብሎ በጠባቡ የተከፈተ ስለነበር በቀላሉ ከቤቱ መውጣት አልቻለችም። ቆም ብዬ በታዘብኳት ወቅት ርግቢቱ ስታሳየው የነበረው የጭንቀትና የመረበሽ ሁኔታ እጅግ በጣም ያሳዝን ነበር፣ ከታች ጠብጠብ ታደርጋለች፣ በቂ አየር ስላልነበረም ክንፎቿን ዘርግታ እንደልቧ መብረር አልቻለችም፣ ስለደከመችም አፎቿን በጣም ከፍታ አየር ትስብ ነበር። መስኮቱ ላይ ሆና ከውጭ ሌሎች እርግቦችን ሲበሩ ስታይ ከነርሱ ጋር ለመሆን በመንደፋደፍ ከመስተዋቱ ጋር ትጋጫለች። በመጨረሻም ምንም ማድረግ እንደማትችል ስለተገነዘበች ጠጋ ብዬ እንድይዛት ፈቀደችልኝ። በመስኮቱ በኩል እጄን አውጥቼ ስለቃት ከመቅጽበት ነበር ነፃ ሆና እየበረረች ወደሰማይ ለመውጣት የበቃቸው።

እንደ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ ፤ ማክሰኞ ማርች 14ለረቡዕ አጥቢያ እህት ዓለምን የምትከታተላት ነርስ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ተኝታ አየቻት፡፡ 11 ሰዓት ላይም ተኝታ ነበር፡፡ ለሦስተኛ ጊዜ በ12 ሰዓት ስትጎበኛት ለአየር ማስገቢያ በተከፈተ ኮሪደር ላይ አንሶላ ቀዳ ራሷን አጥፍታ ተገኘች፡ ስለዚህ የሞተቸው ረቡዕ ማርች 14 ከንጋቱ 12 ሰዓት ላይ እንደሆነ ተገልጧል።

ይህን ዜና ካገኘሁ በኋላ ርግቢቱን ያገኘኋት በ12 ሰዓት ላይ መሆኑ ባጋጣሚ እንዳልሆነ አሁን ገባኝ። ርግብ የ መንፈስ ቅዱስ፥ የሰላምና የነፃነት ምልክት ናት። 12 ቁጥርም ቅዱስ ቁጥር ነው። እህት ዓለም ከእርጉሞች እጅ ነፃ ወጥታለች የእግዚአብሔርን ሰላም አግኝታለች። የበደሏት እርጉም ሕዝቦች ግን የሚቀጡበት ጊዜ ደርሷል፣ አምላክ የሰጣቸውን ዕድል ባለመጠቀማቸውም ተፈርዶባቸዋል ፤ የዘሯትን የጥላቻ ሰብል በቅርቡ ያጭዷታል።

መዝሙር 12

5 ስለ ድሆች መከራ፥ ስለ ችግረኞች ጩኸት እግዚአብሔር፤ አሁን እነሣለሁ ይላል፤ መድኃኒትን አደርጋለሁ፥ በላዩም እገልጣለሁ።

6 በምድር ላይ እንደ ተፈተነ ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ ብር። የእግዚአብሔር ቃላት የነጹ ቃላት ናቸው።

7 አቤቱ፥ አንተ ጠብቀን፥ ከዚህችም ትውልድ ለዘላለም ታደገን።

8 በሰው ልጆች ዘንድ ምናምንቴ ከፍ ከፍ ባለ ጊዜ ክፉዎች በዙሪያው ሁሉ ይመላለሳሉ።

 

A well-written song by David, when he was in the cave; a prayer.

Psalm 142

1 To the LORD I cry out; to the LORD I plead for mercy.

2 I pour out my lament before him; I tell him about my troubles.

3 Even when my strength leaves me, you watch my footsteps. In the path where I walk they have hidden a trap for me.

4 Look to the right and see! No one cares about me. I have nowhere to run; no one is concerned about my life.

5 I cry out to you, O LORD; I say, “You are my shelter, my security in the land of the living.”

6 Listen to my cry for help, for I am in serious trouble! Rescue me from those who chase me, for they are stronger than I am.

7 Free me from prison, that I may give thanks to your name. Because of me the godly will assemble, for you will vindicate me.

_________________________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

They Killed Our Sister!

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 15, 2012

They beat her in broad daylight, in front of the camera, on the very day when the International Women’s Day was supposed to be celebrated — and nobody was there to stop them, they took her, wherever they took her, but no one was there to look after her, to take care of her, to comfort her. We alarmed the so-called human ‘rights’ agents , we send the videos to many news organizations, they all turned a blind eye to the horrific brutality our dear sister, Alem had to experience. Now, a week later, she is dead!

You murdered her, Lebanon!

You murdered her, Ethiopian Consulate!

You murdered her, the Main Stream Media!

You murdered her, Amnesty International!

You murdered her, Human Rights Watch!

You murdered her, The Feminist Movement!

Shame on you all — you prefer to protect animals to humans, you give more attention to a woman who dumps her cat in trash than an innocent human soul.

You all will be judged, Alem will judge you!

R.I.P my sister — The God of Abraham, Isaac and Jacob, The Lord of Ethiopia will comfort you now!

______________________________

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , , , | 9 Comments »

 
%d bloggers like this: