Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • March 2023
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    2728293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ፓትርያርክ ኪሪል’

Russian Patriarch Kirill Calls for Orthodox Christmas Truce – Antichrist Zelenskiy Rejects it

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 6, 2023

💭 የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቀዱስ አቡነ ኪሪል ለኦርቶዶክስ የገና በዓለ በዩክሬይን ተኩስ እንዲቆም ጥሪ አቀረቡ ፥ ፀረክርስቶስ የዩክሬይን ፕሬዚደንት ግን ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ ግን ጥሬውን ውድቅ አደረገው።

ልክ እንደ ቆሻሻው ግራኝ አብዮት አህመድ ኦርቶዶክስ ወንደማማቾችን በመከፋፈል ላይ ያለው የዚህ ወስላታ መሪ ደጋፊዎች የሆኑት ኤዶማውያኑ ምዕራባውያንም (ግራኝና ዜሊንስኪ ወደ ዋሽንግተኑ ነጩ ቤት በአንድ ሰሞን መጋበዛቸው ያለምክኒያት አልነበረም) በዚህ የሰላም ጥሪ ላይ በመሳለቅ ላይ ናቸው። በኢትዮጵያ ግን “ተደራደሩ! ሰላም ፍጠሩ፣ ተኩስ አቁሙ!” እያሉ አረመኔዎቹን ወኪሎቻቸውን እነ ኢሳያስ አፈቆርኪን፣ ደብረጽዮንን እና ግራኝ አብዮት አህመድ አሊን ከተጠያቂነት ለማዳን ተግተው በመስራት ላይ ናቸው። ለጊዜው ‘በበቂ’ ቁጥር ያህል ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖችን ለመጨፍጨፍ ስለበቁ ነው አሁን በኢትዮጵያ ‘ሰላሙን’ የሚሹት። በዩክሬይን እና በሩሲያ፣ በቀጣዩም በግሪክና አርሜኒያ የሚገኙት ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ግን ሉሲፈራውያኑ እንደሚመኙት ቁጥር ያህል ገና አላለቁላቸውም። መቼስ ለምዕራባውያኑ ወዮላቸው!

The Russian Patriarch Kirill, head of the Russian Orthodox Church, calls for a ceasefire in the conflict between Russia and Ukraine.

He wants both militaries to lay down their arms at midnight on January 6, when the Eastern Orthodox Church celebrates Christmas. That is reported by Patriarcha.ru.

A ceasefire would allow orthodox soldiers to attend church services on Christmas Eve and Christmas day, Kirill explained his plea. He added that the truce should remain in force until the night before next Sunday.

Eastern Orthodox Churches have traditionally celebrated Christmas on a different date than Western churches. This year, for the first time, the Ukrainian Orthodox Church allowed parishes to adhere to Western traditions by celebrating Christmas on December 25.

For much of the Western world, Christmas is celebrated on December 25, according to the Gregorian calendar. Yet in a distinction that dates back centuries, Orthodox Christians follow the Julian calendar and mark the festival on January 7 instead.

Orthodox Christmas — and the long-standing rift between the Russian Orthodox Church and other Orthodox groups — has been thrust into the spotlight this year by Russian President Vladmir Putin’s call for a temporary 36-hour ceasefire in Ukraine to allow Orthodox followers to attend Christmas services. Putin’s proposal was swiftly dismissed as “hypocrisy” and “propaganda” by Ukrainian officials, and shelling has continued from both sides.

Orthodox Christians are estimated to number between 200 and 300 million people globally.

It may be the new year, but for us, Christmas celebrations are only just beginning.

In some Eastern European countries, in Ethiopia and Egypt Christmas is officially celebrated on January 7.

That is because many Orthodox Christian churches follow the Julian calendar for religious celebrations.

The Julian calendar runs 13 days behind the Gregorian calendar, the standard international calendar in use today.

When we Orthodox Christians open the church calendar on January 7, we’re actually looking at the date December 25. So we still have that same date, we’re just using a calendar that hasn’t caught up. It’s like a clock that’s running 13 days slow.

The Julian calendar took effect under the reign of Julius Caesar in 45BC.

In 1582, Pope Gregory XIII created a new calendar to correct the discrepancy between calendar time and calculated astronomical time. It became known as the Gregorian calendar.

But to begin with only Catholic countries adopted the changes and Orthodox Christian countries remained on the Julian calendar.

Over time, those countries adopted the Gregorian calendar for secular use but the Orthodox churches continued to base their liturgical calendar on the Julian timetable.

In 1923 a revised version of the Julian calendar was introduced bringing Christmas Day in line with the Gregorian calendar, but it was only adopted by some of the Orthodox Christian countries including Greece, Cyprus and Romania.

Russia, Ukraine, Serbia, Belarus, Egypt, Ethiopia, Georgia, Kazakhstan, Macedonia, Moldova and Montenegro continue to celebrate Christmas on January 7.

Prior to Russia’s full-scale war on Ukraine, Kyiv had been pushing to establish its own independent Orthodox Church separate from Moscow, and the schism only widened in the wake of Putin’s invasion last year. In October, a branch of Ukraine’s Orthodox church announced it would allow its churches to celebrate Christmas on December 25, rather than January 7.

Edomites of The West and Ishmailites of The East are spreading strife among Orthodox Christian brothers in Russia, Ukraine, Armenia, Georgia, Syria, Iraq, Egypt and Ethiopia.

❖❖❖[Proverbs 6:16-19]❖❖❖

There are six things which the Lord hates Yes seven which are an abomination to Him:..And one who spreads strife among brothers.„

💭 For example, there was an anti-Orthodox conspiracy when the following individuals and bodies had been ‘randomly and coincidentally’ awarded by the Norwegian Nobel Committee – four years in a row:

2019 Nobel Peace Prize to evil Abiy Ahmed Ali for a Pact of War vs Orthodox Ethiopia

2020 Nobel Peace Prize to WFP in anticipation of the following genocidal war (Nov. 2020) against ancient Orthodox Christians of Tigray, Ethiopia

2021 Nobel Peace Prize to Dmitry Muratov of Orthodox Russia in anticipation of the coming war (Feb. 2022) between the two orthodox brothers; Russia-Ukraine

2022 Nobel Peace Prize to Ales Bialiatski from Belarus and the Russian human rights organisation, the Russian human rights organisation Memorial and the Ukrainian human rights organisation Center for Civil Liberties. – in anticipation of the coming nuclear war between the three orthodox brothers; Russia + Ukraine + Belarus

______________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ፈተና በኦርቶዶክሱ ዓለም | የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከእስክንድርያ ፓትርያርክ ጋር የነበራትን ግንኙነት አቋረጠች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 27, 2019

የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የዩክሬን አዲስ ገለልተኛ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እውቅና ለመስጠት ውሳኔዋን ተከትሎ በአፍሪካ ከምስራቅ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መሪ ጋር ግንኙነቱን አቋርጣለች።

በምስራቁ ግሪክ ኦርቶዶክስ የግብጽና መላው አፍሪቃ ፓትሪያርክ ለዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እውቅና መስጠታቸውን ተከትሎ ነው የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ግንኙነትን ለማቋረጥ የወሰነችው።

የ የሞስኮና መላው ሩስያ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በትናንትናው ሐሙስ መገባደጃ ላይ በግብጽ የእስክንድርያውና መላው አፍሪቃ ጳጳስ ከቴዎድሮስ ፪ኛ ጋር ያሉትን ሁሉንም ግንኙነቶች ለማቋረጥ ወስናለች፡

ሆኖም ውሳኔውን ከማይደግፉት የግብጽ ቤተክርስቲያን ቀሳውስት ጋር በህብረት እንደምትቆይ ገልጻለች፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስም በአፍሪቃ የሚገኙ የአኅጉር ስብከት አገልግሎቶች ከእስክንድርያ ፓትርያርክ መስተደዳደር እንዲወገድ እና በቀጥታ በሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ኪሪል አመራር ሥር እንዲሆኑ ወስኗል፡፡

እርምጃው የጥር ወር ውሳኔን ተከትሎ ከሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ጋር ለዘመናት የኖረችውን የዩክሬን አዲሱ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ከመላው ሩሲያ ኦሮቶዶክስ ቤተክርስቲያን እንድትገነጠልና ነፃነትም እንዲሰጣት ለማድረግ የቁስጥንጥንያውን ፓትርያርኩ ባቶሎሜው የመጀመሪያውን ውሳኔ ተከትሎ ነው፡፡

ወገኖቼ፡ ይህ የክፍፍል ወረርሽኝ ቀላል ነገር እንዳይመስለን። ሁላችንንም የሚመለከት ጉዳይ ነውና። ምንም እንኳን በእስክንድርያ ተቀማጭነት ያላት የምስራቁ ግሪክ ኦርቶዶክስ የግብጽና መላው አፍሪቃ ቤተክርስቲያን ከኮፕት ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የተለየች ብትሆንም የግብጽም ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አንዳንድ ደስ የማያሰኙ አካሄዶችን ስትራመድ ትታያለች። በአረብ ሙስሊሞች ተጽእኖ ሥር የወደቀችው ይህች ታሪካዊት ቤተክርስቲያን በጣም ብዙ ፈተናዎችን በመጋፈጥ ላይ ነች።

የግብጻውያን ትንኮሳ የቆየና የኖረ ነው። ኢትዮጵያ መንግሥቷ የደከመ ሲመስላቸው አጋጣሚውን እየተጠቀሙ የግል ንብረቶቻችንና ይዞታዎቻችንን በሙሉ ሲነጥቁን፣ አባቶቻችንን ሲያንገላቱና ሲደበድቡ (አቡነ ማትያስ ያውቁታል)የኖሩ መሆናቸው የሚታወቅ ነው።

በኢትዮጵያውያን ዘንድ በተለየ ቅድስና የሚታዩት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሳይቀር የኢትዮጵያን ገዳማት “ለመንጠቅ”ቅሽሽ ሳይላቸው አልፈዋል። አንዳንዴ ግብጻውያን በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ላይ የሚፈጽሙትን ግፍ (አር ሱልጣን)ለሚያይ ሰው የግብጻውያን ክርስትና በአፍንጫዬ ይውጣ ነው የሚያሰኘው። በአህዛብ ተጽእኖ ሥር እንደወደቁ ነው የሚያሳየው። ከአህያ ጋር የዋለችእንዲሉ። ከዱር አህያው ከእስማኤል ጋር አብሮ መኖር እንዲህ ያደርጋልና።

እኔ በግሌ በጣም የማከብራቸው የቀድሞው የግብጽ ፓትርያርክ አቡነ ሴኑዳ አማላኪቶቹን ፍልስጤማውያንንና አረብ ሙስሊሞችን ለማስደስት ሲሉ ኮፕት ግብጻውያን ወደ እስራኤል እንዳይጓዙ በአዋጅ መከልከላቸውን ስሰማ በጣም ነበር ያዘንኩባቸው፤ ብዙ ክርስቲያን ግብጻውያንም በኋላ ላይ “አይ ባባ” እያሉ ያዝኑባቸው ነበር። በሳቸው ጊዜ የአረብ ፖለቲከኞቹ በምዕራባውያኑ እርዳታ ኤርትራን ከገነጠሉ በኋላ “የኤርትራ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን” ከእናት ቤተክርስቲያኗ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እንድትገነጠል ያደረገችው የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ነበረች። እንደተገነጠለችም እውቅና ሰጥታ በሥሯ ያደረገቻት ይህችው ቤተክርስቲያን ነበረች። የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በግብጽ መንግሥት የዲፕሎማሲ ዕርዳታ የሚደገፍ ነው። በመካከለኛው ምስራቅ ላለው ፖለቲካ እስራኤል የአረብ ሙስሊሙን ዓለም ተፅዕኖ ለመቋቋም ይረዳት ዘንድ ግብጽን በአረቦች ዘንድ ተደማጭ ናት የምትባለዋን ግብፅን በእጅጉ ትፈልጋታለች። ግብፅም ለእስራኤል ድጋፏን በሰጠች ቁጥር አሜሪካ ለግብጽ የፖለቲካ፣ የውትድርና እና የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ፍላጎቷን ታሟላላታለች።

ዛሬ ሩሲያና ዩክሬንን በተመለከተ ግብጽና ቤተክርስቲያኗ እየወሰደችው ያለው እርምጃ ተመሳሳይ ነው። በአንድ በኩል ግብጽ ከሩሲያም ከአሜሪካም የጦር መሣሪያዎችን በብዛት ትሸምታለች። በቅርቡ እንኳን አባይን አስመልክቶ ፕሬዚደንት አልሲሲ በሩሲያው ሶቺ ከኢትዮጵያ ህገወጥ መሪዎች ጋር ከተገናኘ በኋላ በጥቂት ቀናት ውስጥ ተመሳሳይ ስብሰባ በአሜሪካ ለማድረግ በቅቷል። እስኪ እናነጻጽረው፦ የግብጽ መንግስት፣ የግብጽ ቤተክርስቲያንና የግብጽ ሙስሊሞች ሁሉም በአንድነት ለሃገራቸው ግብጽ የቆሙ ናቸው ፥ በተቃራኒው የኢትዮጵያ መንግስትና የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ኢትዮጵያን እየከዱ ነው፤ በግብጽና በኢትዮጵያ መካከል ጦርነት ቢቀሰቀስ ከግብጽ ጎን እንደሚሰለፉ አያጠራጥርም፤ ታሪክም የሚያስተምረን ይህ ነው።

አሁን ደግሞ፤ በሃገሩ የምትገኘው የምስራቅ ግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በቀጥታ ለማይመለከታት ለዩክሬይን ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እውቅና መስጠቷ ከአባይ ወንዝ ጋር የተያያዘ ሊሆን ይችላል። የግብጹ ፕሬዚደንት አልሲሲ በአባይ ጉዳይ የአሜሪካን ድጋፍ ለማግኘት አሜሪካ በዩክሬይን በምትከተለው የፀረሩሲያ መስመር ላይ መሰለፍ ይሻል፤ የኮፕት ኦርቶዶክስ ፓትርያርክ ቴዎድሮስም ከግብጽ መንግስት በኩል አስፈላጊውን ድጋፍ ለማግኘት ሲል ፀረሩሲያ እና ፀረኢትዮጵያ የሆነ አቋም መያዝ ይኖርባቸዋል። እነዚህ ብልሹ ባለሥልጣናት “የኦሮሚያ ቤተክህነት” የተሰኘውን የዲያብሎስ ህልምም ከማሟላት ወደኋላ እንደማይሉ ማወቅ ይኖርብናል።

በክርስቶስ ተቃዋሚዋ ቱርክ መንጋጋ ውስጥ የገባቸው የቁስጥንጥንያ ቤተክርስቲያንም እንዲሁ ከሉሲፈራውያኑ ምዕራባውያን ጋር ከተደመረች ቆይታለች፡፡ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንም ለዩክሪየን ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እውቅናዋን ሰጥታለች። ለረጅም ጊዜ፡ በሶቪየት ሕብረት ዘመን ሳይቀር በዘውገኝነት ጋኔን የተያዘችው ዩክሬንም ብዙ ውለታ የዋለችላትን እህቷን ኦርቶዶክስ ሩሲያን ለመተናኮል በሉሲፈራውያኑ ተመርጣለች። ከዝብግኒው ብረዥንስኪ እስከ ጆን ማኬንና ጆርጅ ሶሮስ ድርሰ ሁሉም ቤተክርስትያን ነፃነትን ለመስጠት የተሰጠው ውሳኔ የኦርቶዶክስ ዓለምን ለሁለት ከፍሎ የነበረ ሲሆን አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት የሚደግፉ ሲሆን ሌሎችም እንቅስቃሴውን የሚተቹ ናቸው።

የኦርቶዶክስ ሰርቢያን ዋና ከተማን ቤልግራድን በትንሣኤ ሰንበት በቦንብ ጣይ አውሮፕላኖች የደበደበው የሉሲፈራውያን ኔቶ ድርጅት በኦርቶዶክስ ክርስቲያኑ ዓለም፡ በተለይ በተራራማዋ ተዋሕዶ ኢትዮጵያ ላይ ጦሩን ለማዝመት ያው ላለፉት ሃያ ዓመታት በተራራማው አፍጋኒስታን በመለማመድ ላይ ይገኛል። ይህን ሁሉ ጊዜ በአፍጋኒስታን ምን ይሠራሉ? ብለን እንጠይቅ።

ከሁለት ዓመታት በፊት፤ የሉሲፈራውያኑ ተቋም ሲ.አይ.ኤ በግራኝ አብዮት አህመድ የሚመራውን መፈንቅለ መንግስት ገና ከማካሄዱ በፊት የሚከተለውን ጽሑፍ አቅርቤ ነበር፦

ቅዱስ ሚካኤል + ኢየሩሳሌም + ያልተባበሩት መንግሥታት + የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ልጆች ይህችን የ ቅ/ ሚካኤል ዕለት እናስታውስ፤

ወንድሞቻችንን በባርነት ከምሸጡት፣ እህቶቻችንን ከፎቅ እየወረወሩ ከሚገድሉት አርቦች ጋር ከአርቦች ጋር በማበር የኢትዮጵያን የድጋፍ ድምጽ በተባበሩት መንግሥታት እንድንሰጥ ተደርገናል። ዓጼ ኃ/ ሥላሴም ተምሳሳይ ድርጊት ከፈጸሙ በኋላ ነበር፤ ኢትዮጵያችን በጣም አስከፊ በሆነ መልክ እንድትራቆትና እንድትደቅ ሁለት ትውልድ እንዲጠፋ የተደረገው።

የግድ አሜሪካንና እስራኤልን መደገፍ የለብንም፡ ለዚህም እንደነ ቤኒን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኡጋንዳ፣ ኬንያ፣ ሌሶቱ፣ ማላዊ፣ ጊኒ ኤኳተሪያል፣ ፊሊፒንስ፣ ኮሎምቢያ፣ ፓናማ፣ አውስትራሊያ፣ አርጀንቲና፣ ቦስኒያ፣ ፖላንድ፣ ሮማኒያ ወዘተ የመሳሰሉት 15 አገሮች በገልተኝነት ድምጽ ከመስጠት መቆጠብ ነበረብን።

የሚያሳዝነው እስራኤልን ወይም አሜሪካን አለመደገፋችን ሳይሆን አረቦችን መደገፋችን ነው! አገራችን ከፍየል አገራት ጋር አብራ መሰለፍ አልነበረባትም። ያልተባበሩት መንግሥታት በሊቢያ ስለሚካሄደው የባርነት ንግድና በእስላም አገሮች የሚታየው የክርስቲያኖች ጭፍጨፋን ልክ እንደዚህ በደንብ መውገዝ ነበረበት እንጂ ኢምባሲ ተዛወረ አልተዛወረ እንደ ትልቅ ነገር ተቆጥሮ የተለየ ሤራ መጠንሰስ አልነበረበትም። ወስላቶች!

እስራኤላውያን ለክፉም ሆነ ለበጎ በተለይ በኢትዮጵያውያን ላይ ልዩ የሆነ አትኩሮት ነው ያላቸው። ግብጽም፡ ልክ እንደ ቀድሞው በደስታ ጮቤ ትረግጣለች፤ ፍርሀት የተጫነው የመረጋጋት መመሪያ ሠርቶ አያውቅም።

800 ዓመታት በፊት በመሀመዳውያን ላይ ቅስም የሚሰብር ድል የተቀዳጀቸው ስፔይን (በዚህም፤ ኢትዮጵያ፡ ስፔይንና ፖርቱጋልን በመርዳት በይፋ የማይታወቅ ከፍተኛ ሚና ተጫውታለች፤ ሌላ ጊዜ..) ያው በካታላንውያን በኩል ኃይለኛ ፈተና ገጥሟታል፤ በዛሬው ዕለት በካታሎኒያም የተካሄደው ምርጫ ብዙ መዘዝ አለው። ካታሉኒያ + ቫሎኒያ + ባቫሪያ + ኤርትራ + ኦሮሚያ + ክሮአስያ + ስኮትላንድ + ቱርክ + ዩክሬየን + ኩቤክ + እነዚህ ግዛቶች የአመጸኞቹ አለቃ ሰይጣን በክርስቲያን ሕዝቦች ላይ እንዲያምጹ ያዘጋጃቸው ግዛቶች ናቸው። በጌታችን ልደት ዋዜማም ይህ ሁሉ መከሰቱ ያለምክኒያት አይደለም።

የድምጽ ሰጪ አገሮች ሰንጠረዡም በኢትዮጵያ ሦስት ቀለሞች፤ አረንጓዴቢጫቀይ ያሸበረቀ ነው። አረንጓዴ፤ አረቦች የሰረቁት የእስላም ቀለም ሆኗል፤ ቢጫ ገለልተኞች፣ ቀይ ደግሞ አመሪካና እስራኤል የደገፉት ናቸው። በጣም አስገራሚ ነው! የ ሄጌል ThesisAntithesisSynthesis ሞዴል

ይህን የታህሳስ ፲፪ ፥ ፪ሺ፲ ዓ.ም ዕለትን በደንብ እናስታውስ።

________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የሩሲያ ፓትርያርክ፡ “ዘመናዊ ስልኮች ለፀረ-ክርስቶሱ መምጣት መንገድ ይከፍታሉ” በማለት በጥብቅ ያስጠነቅቃሉ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 11, 2019

የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ኪሪል የግና በዓልን በማስመልከት ከሩሲያ ቴሌቪዥን ጋር በተደረገ አንድ ቃለ ምልልስ ላይ የሚከተለውን ተናግረዋል፦

የክርስቶስ ተቃዋሚ፡ አሁን የተስፋፉትን ዘመናዊ ስልኮችን ወይም ስማርት ስልኮችን ለመጥለፍ የሚያስችለው ኤሌክትሮኒክ መሣሪያ አጠቃቀም ስልት በጣም ሰፊ ነው

ቤተክርስቲያኗ የቴክኖሎጂ ዕድገትን አትቃወምም፥ ነገር ግን በኢንተርኔት የተገናኙ መሳሪያዎች ለሰው ዘር ሁሉ ዓለም አቀፍ ቁጥጥርማድረግ የሚችሉበትን ሁኔታ ፈጥረዋል

ሰዎች በትክክል የት እንዳሉ ምን እንደሚፈልጉ፣ ምን እንደሚፈሩ ተከታያቾቻቸው እንዲያውቁ ያስችላቸዋል

እንዲህ ያለው መቆጣጠሪያ መንገድ፡ ፀረክርስቶሱ ከአንድ ቦታ ሆኖ አስቀድሞ እንዲመለከት ይረዳዋል።

ፀረክርስቶሱ የሰው ዘር ሁሉ የሚቆጣጠር ዓለም አቀፋዊ መሪ ይሆናል ይህም ማለት ይህን መሰሉ የቴክኖሎጂ መዋቅ እራሱ አደጋን ያመጣል ማለት ነው

የአለም ፍጻሜን ቶሎ ለማድረስ ካልፈለግን በቀር ነገሮች በአንድ ማዕከላዊ በሆነ ቦታ ቁጥጥር ሥር መውደቅ የለባቸውም፤ ማዕከላዊ ሆኖ የሚንቀሳቀስ ነገር መጥፋት አለበት።” ብለዋል።

ፓትርያርክ ኪሪል ብልህ የሆነ እና በጣም ጠቃሚ የሆነ መልዕክት ነው ያስተላለፉልን። በተለይ ሕፃናት ከስማርት ስልኮች መራቅ ይኖርባቸዋል። አሁን እንኳን ምዕራባውያኑ ሕፃናት በስማርት ስልክ ሳቢያ ዓይኖቻቸው ክፉኛ እየተጎዱ ነውእዚህ እና እዚህ ያንብቡ።

ከጥቂት ዓመታት በፊት እነ ቢል ጌትስ ከወስላታው ኮፊ አናን ጋር በማበር ለእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ሕፃን አንድ ላፕቶፕ እንሰጣልን( One Laptop Per Child) ሲሉ፡ “ኡ! ! አውሬው ሕፃናቶቻችንን ሊቆጣጠር ይሻል!” በማለት ስጋቴን ገልጬ ነበር።

ስለ ፀረክርስቶሱ፡ ብዙ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስጠንቀቂያዎች ፩ኛ የዮሐንስን ጨምሮ በሌሎችም መጻሕፍት ውስጥ እናገኛለን፦

፩ኛ የዮሐንስ መልእክት ምዕራፍ ፪ ፲፰ እንዲህ ይላል

ልጆች ሆይ፥ መጨረሻው ሰዓት ነው፥ የክርስቶስም ተቃዋሚ ይመጣ ዘንድ እንደ ሰማችሁ አሁን እንኳ ብዙዎች የክርስቶስ ተቃዋሚዎች ተነሥተዋል፤ ስለዚህም መጨረሻው ሰዓት እንደ ሆነ እናውቃለን።

ውድ ልጆች ሆይ, ይህ የመጨረሻው ሰዓት ነው; የክርስቶስ ተቃዋሚ እንደሚመጣ እንደ ሰማችሁ መጠን አሁንም ብዙዎቹ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች መጥተዋል

ኢትዮጵያ አገራችንንም በጥቂቱ ላለፉት 50 ዓመታት እየመሩ ያሉት ፀረክርስቶሶቹ ናቸው። ለመሆኑ ዶ/ር አብይ አህመድ ኢትዮጵያ መንግስት የኢንተርኔት መቆጣጠሪያ ባለሥልጣንን የገነቡ ግለሰብ መሆናቸውን እናውቅ ነበርን? ታዋቂው የስዊዘርላንድ ጋዜጣ NZZ ይህን በማስመልከት ከሁለት ወራት በፊት በሰፊው አትቶ ነበር።

በሌላ በኩል የ ጉግል ተቋምና የአሜሪካ ኤምባሲ፡ በልማት እና ስራ ፈጠራ ስም፡ ወንጀላዊ የኢንተርኔት ጠለፋና ፕሮፓጋንዳን የተመለከተ ሥልጠና በአሜሪካ ኢምባሲ በኩል ለኢትዮጵያውያን እንደሚሰጡ ባለፈው ኅዳር ላይ ተገልጾ ነበር።

በአገራችን ላይ እየተካሄደ ያለው ፀረክርስቶሳዊ ድራማ በቅደም ተከተል ነው በደንብ የተቀነባበረው። ነገሮች ሁሉ ወዴት እያመሩ እንደሆነ እያየን ነው።

______

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: