Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ጾመ ነነዌ’

በደቡብ ኢትዮጵያ እሳት ከሰማይ ዘነበ | ነብያት ሙሴና ዮናስ አስተምረውናል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 12, 2020

ዘነበ ለዘንባራተቤራ

ይህ አካባቢ የተጠለፉት እህቶቻችን አሳዛኝ ጉዳይ የተፈጸመበት አካባቢ ነው፤ ለጅማ ቅርብ ነው፤ አጋቻቸው አብዮት አህመድ “ሰበርናቸው/ የተሰረቁት ሃያ አበቦች (ልጃገርድ ተማሪዎችን በማለት እንደለመደው መሳለቁ ይሆናል)” ትናንታና ወደ ጂሃድ ጅማ በማምራት የድል አቀባበል እንዲደረግለት አዘጋጅቶ ነበር። ነገ ደግሞ አረብ ሞግዚቶቹ ፊት ለመምበርከክ ወደ ጂሃድ አረቢያ ያመራል። በደቡብ የወረደው እሳት በሄደበት ይከተለው!

የእግዚአብሔርም እሳት በመካከላቸው ስለነደደች የዚያን ስፍራ ስም “ተቤራ” ብሎ ጠራው”

[ኦሪት ዘኍልቍ ምዕራፍ ፲፩,፥፩፡፫]

ሕዝቡም ክፉ ሆነው በእግዚአብሔር ላይ አጕረመረሙ፤ እግዚአብሔርም ሰምቶ ተቈጣ፤ የእግዚአብሔርም እሳት በመካከላቸው ነደደች፥ የሰፈሩንም ዳር በላች። ሕዝቡም ወደ ሙሴ ጮኹ፤ ሙሴም ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፥ እሳቲቱም ጠፋች። የእግዚአብሔርም እሳት በመካከላቸው ስለነደደች የዚያን ስፍራ ስም ተቤራ ብሎ ጠራው።”

በደቡብ ኢትዮጵያ በከምባታ ጠምባሮ ዞን ዱሬ፣ ሲገዞ፣ “ለዘንባራ” እና ሆዶ ቀበሌዎች ዓርብ ለቅዳሜ አጥቢያ ከሰማይ ወረደ በተባለ እሳት ሰላሳ በላይ የሳር ቤቶች የተቃጠሉ ሲሆን ስድስት ከብቶች እና የጢርፍ ክምርም የጉዳቱ ሰለባ ሆኗል።

የእሳቱ መንስዔ በግልጽ ባይታወቅም የአካባቢው ኅብረተሰብ በተመሳሳይ ሰዓት ከሰማይ ወርዶ ጉዳት እንዳደረስ እና ተፍጥሯዊ ነው ብለዋል።

______________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ነብዩ ዮናስ አይደለሁም ሆኖም ይህ ትናንት የታየኝ ሌላ አስገራሚ ክስተት ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 12, 2020

ጾመ ነነዌ (የኢትዮጵያ ጾም) ዘመነ ዮሐንስ፤ ዛሬ ረቡዕ ፬ – ፪ሺ፲፪ ዓ.ም ነው፤ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ነው።

ነቢዩ ዮናስ ነነዌ መሬት ላይ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ከእግዚአብሔር መሸሽ አለመቻሉን ተረዳ። የነነዌ ሰዎችንም ንስሐ ግቡ እያለ መስበክ ማስተማር ጀመረ፡፡ የነነዌ ሰዎችን የዮናስን ትምህርት ሰምተው ንስሐ በገቡ ጊዜ እግዚአብሔር አምላክ ይቅር ብሎ ከጥፋት አድኗቸዋል፡፡ነቢዩ ዮናስም ሐሰተኛ እንዳይባል እሳቱ እንደ ደመና ሆኖ ከላይ ታይቷል።

ዮናስ ማለት የስሙ ትርጉም ርግብ ማለት ነው።

በጾማችን እግዚእብሔር አምላክ መዓቱን በምሕረቱ ቁጣውን በትዕግስቱ መልሶ በኃጢአት ለጠፋው ዓለም ይቅርታውን ይላክልን፡፡

___________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

የሃበሻ እንባ፡ ምነው ተሞኘን? ተጨቃከንን?

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 19, 2014

ከአራት ዓመታት በፊት፡ በጾመ ነነዌ ዕለት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በእርኩስ ኃይሎች ቤይሩት ከተማ ተቃጠለ፣ ከዚህ ድርጊት በኋላ በየዓመቱ በነነዌ የፆም ሰሞን ከአየር ጋር / ከአውሮፕላን ጋር የተያያዙ አደጋዎች በየቦታው ተከስተዋል። ለምሳሌ፦

2011ቱ ነነዌ

አውሮፕላኖች ተከስክሰው ተሳፋሪዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል

2012ቱ ነነዌ

2013ቱ ነነዌ

አሁን በጾመ ነነዌ ሳምንት (መስቀል ኢየሱስ) በአየር መንገዳችን ላይ በጣም ግራ የሚያጋባ ድርጊት ተፈጸመ።

ረዳት ፓይለቱ ጠላፊ መሆኑን ስሰማ ወዲያው የመጣልኝ፡ ምናልባት የሕሊና በሽታ ደርሶበት ይሆናል! እንዲያውም የ “Manchurian Candidate” ሊሆን ይችላልየሚለው ሃሳብ ነበር።

 

ይህ የጠለፋ ተግባር በሱዳን ዓየር፡ በዓባይ ወንዝ ከፍታ ላይ እንደተካሄደ ተገልጿል። ታዲያ በዚህ ወቅት በረዳት ፓይለቱ ላይ ምን አይነት ድርጊት ተፈጽሞበት ይሆን? “Hypnotize” ተደርጎ ይሆን? “Manipulate” ተደርጎ ይሆን? ጣልያናዊው ፓይለትስ ምን ዓይነት ሚና ተጫውቶ ይሆን?

ግለሰቡ ጤናማእንደሆነ፡ ነገር ግን በአጎቱ ሞት ተጨንቆ / ተረብሾ እንደነበር ተገልጧል። ምንም እንኳን አስቀድሞ መፍረድ ተገቢ ባይሆንም፣ ግለሰቡ የፈጸመው ተግባር ግን የወንጀለኛነት፣ የከዳተኝነት ባሕርይ የያዘ ነው። በአገሩ ላይ ይህን መሰሉን ጥራዝነጠቅ የከዳተኝነት ተግባር የሚፈጽም፣ አብዛኛው የአገራችን ሕዝብ ያላገኘውን ዕድልና ገፀበረከት አግኝቶ አሳፋሪ በሆነ መልክ በፈቃዱ ወደገደል የሚጥል ምስጋናቢስ ግለሰብ ነው። ከጀግኖቹ የምድር ባቡሮቻችን / ሯጮጫችን ጎን በአፍሪቃ አየር ለመላው አፍሪቃውያን መኩሪያ የሆነውን አየርመንገዳችንን ባላጋጩ አለም ዘንድ እንድንዋረድበት ማድረጉ እጅግ በጣም፡ በጣም የሚያሳዝን ነው። በተለይ፡ አሁን እንደ ግብጽ የመሳሰሉት ጠላቶቻችን የተንኮል መርዛቸውን ባገራችን ላይ ከያቅጣጫው በመርጨት ላይ በሚገኙበት ወቅት ይህን መሰሉን ተግባር መፈጸሙ ምሕረት የሚያስከለክለው ይሆናል። ይህ ጠለፋ፣ በሕዳሴው ግድብ ላይ ጥቃት ለማድረስ ከሚሻ የግብጽ ቅጥረኛ ጋር ተነጻጻሪ ነው።

በተለያዩ አጋጣሚዎች ከብዙ አገር ሰዎች ጋር አብሬ ለመማር፣ ለመሥራትና ለመኖር፡ አገሮቻቸውንም ለመጎብኘት እድሉ ነበረኝ፤ ታዲያ ከዚህ ሁሉ ለመማር የበቃሁት፤ እንደ አገር ሰው ማንም እንደማይሆነን፣ እንደ አገራችን የትም ሌላ አገር ተድላ፣ ደስታና የመንፈስ ተሃድሶ ልናገኝ እንደማንችል ነው። ሆኖም፤ በአገራችን እንደምንደሰት ሁሉ እንደ አገራችን በይበልጥ የምንከፋበት ሌላ ቦታ የለም። በተለይ መጨረሻ ጊዜ በአንዳንድ ወገኖቻችንን ዘንድ ትህትና፣ መተማመን እና መከባበር እየጠፋ፣ ፍቅር እየቀዘቀዘች መምጣታቸው በጥልቁ ያሳስበኛል።

ባለፈው ዓመት፣ ከአንድ አነስተኛ የፍራፍሬ መደበር ፊት ለፊት በሚገኘው የጫማ መጥረጊያ ቦታ ቁጭ ብዬ በመደብሩ የሚካሄደውን መስተንግዶ እከታተል ነበር። አንድ ወገናችን ቆሞ እንዲያስተናግዱት ወደ 10 ደቂቃ ያህል ቆሟል፣ ከእርሱ በኋላ ሁለት አረቦች/ቱርኮች እንደመጡ የእስላም ቆብ የደፋው የመደብሩ ባለቤት ቶሎ ቀርቧቸው ሲያስተናግዳቸው አየሁ። አላስቻለኝም፣ ከጫማ መጥረጊያው ተነስቼ ፍራፍሬው የተቀመጠበትን መደርደሪያ ወርውሬ በመጣል፣ በባለቤቱ ላይ ያልተለምዶዬ ጩኽቴን ጀመርኩ፤ ለምንድን ነው ወገናችሁን የማታስቀድሙት?” “ቱርኩም አረቡም የራሱን ወገን እንጂ ሌላውን በፍጹም አስቀድሞ አያስተናግድም እኮ፡ ምናለ ወገናችሁን ብታከብሩ?!” አልኩ። የባለመደብሩ ሚስት መሰለችኝ እየተጸጸተሽ፡ አዎ! አዎ!” አለች። ይህን መሰሉ ኩፉኝ በየሱቁ፣ በየምግብ እና ቡና ቤቱ፣ በየሆቴሉ ሁሉ በጣም እንደተስፋፋ ከብዙ ሰዎች ሰምቻለሁ። ይህ በጣም አሳሳቢና አሳዛኝ ጉዳይ ነው።

የረዳት ፓይለቱም ተግባር በጣም የሚያሳስብ ነው። ከጠለፋው ሌላ የሚያስገርመው ነገር፡ ክሣምንት በፊት በስደተኞች ላይ ጥብቅ ሕግ ለማውጣት ሬፈረንደም ወዳካሄደችበት ወደ ስዊትዘርላንድ ሄዶ የፖለቲካ ጥገኝነት ለማግኘት መሻቱ ነው።

ይህ ጠለፋ የሚያሳያን ሌላው ነገር፣ ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ እንደምንሰማው ድኽነትለኢትዮጵያውያን መሰደድ ዋናው ምክኒያት አለመሆኑን እና ከፊሉ ሕዝባችን ለከፍተኛ የመንፈሣዊ ቀውስ መጋለጡን ነው።

ሌላ የሚያሳዝነው፡ ጠላፊው ይህን ቅሌታማ ተግባር ከፈጸመ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ፣ የጠላፊው ማንነት ከመታወቁ በፊት፣ ቀደም ሲል ከዋሃቢ ጠላቶቻችን ጎን ሰልፍ ሲወጡ የነበሩት የ ሰማያዊፓርቲ መሪ የኢትዮጵያውያንን ውድቀት ከሚሹት የውጭ መገናኛ ብዙኃን ወኪሎች ጋር የአንድ ንጹህኢትዮጵያዊ ስነምግባር መንጸባረቂያ ያልሆነ መግለጫ መስጠታቸው ነው። በእውነት ይህ ተግባራቸው ግብዝ! ቅሌታም!” ያሰኛቸዋል።

ስዊዘርላንዶችን በጣም እያጠያየቀ ያለው ነገር በስዊትዘርላንድ የአየር ክልል የኢትዮጵያ አየር መንገድን ያጀቡት የጦር አውሮፕላኖች የስዊትዘርላንድ ሳይሆኑ የጣልያንና የፈረንሳይ መሆናቸው ነው። ለካስ የስዊትዘርላንድ ተዋጊ አውሮፕላን ፓይለቶች ገና እንቅልፍ ላይ ነበሩ፤ ከጠዋቱ 2 ሰዓት በፊት ሥራቸውን አይጀምሩም ነበርና።

በሌላ በኩል ግን፡ ይህን የጠለፋ ክስተት በሚመለከት አንድ የምጠይቀው ጥያቄ አለ፦

  • ድኻዋአገራችን ያሰለጠነቻቸው የአየርመንገዳችን ፓይለቶችና ቴክኒሻኖች ለተሻለ የምሥር ወጥሲሉ አገራቸውን በመክዳት ወደ ሃብታምየአረብ አገራት በብዛት ይጎርፋሉ፣ በተቃራኒው ደግሞ አውሮፓውያን ፓይለቶች የኢትዮጵያን አውሮፕላኖች እንዲያበሩ ይደረጋሉ። ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ? ይህ ጠለፋ በዕጥፍ እንድንዋረድበት ካደረጉን ተግባሮች መካከል፣ ፓይለቱ ጣልያናዊ መሆኑን መላው ዓለም መስማቱ ነው። ኢትዮጵያ አውሮፕላን አላት እንዴ?’ ‘አህ፡ ኢትዮጵያውያን ማብረር ስለማይችሉ ፈረንጅ ቀጥረዋል!” የሚሉትን የጭፍኖች ትችት በየቦታው በማንበብ ላይ ነን። ከ50 ዓመታት በፊት እነ ኔልሰን ማንዴላ የኮሩበት ዓየር መንገዳችን አሁን እንዴት ፈረንጆችን ለመቅጠር በቃ?

በዚያን ጊዜም ብዙዎች ይሰናከላሉ እርስ በርሳቸውም አሳልፈው ይሰጣጣሉ እርስ በርሳቸውም ይጣላሉ፤ ብዙ ሐሰተኞች ነቢያትም ይነሣሉ ብዙዎችንም ያስታሉ፤ ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች። እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል” [ማቴዎስ ፳፬᎓፲፥፲፫]

Tears of Eritrea — የሀበሻ እምባ

__

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

ጾመ ነነዌ 2005 በ ዓባይ ዙሪያ ያሳያቸው ምልክቶች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 2, 2013

  • ሰኞ የካቲት 18፦ የዓለም አቀፍ ቢሲኪሌት ስፖርት ህብረት፡ 2013 .ም የኢትዮጵያውያን ዓመት ነውን? በሚል ጥያቄ ይጀምርና፡ ኢትዮጵያውያን በቢሲኪሌት ስፖርት በጣም ሊበለጽግ የሚችል ችሎታ እንዳላቸው ያስታውቃል

አንመኝላቸውም! ግን መሆን ያለበት ይሆናል፤ በሰሜን አፍሪቃና በሳዑዲ አረቦች፡ እንዲሁም በተባባሪዎቻቸው ላይ ከፍተኛ መቅሰፍት እየመጣባቸው ነው! የመቅሰፍቱ ምንጭም ልክ ከሙሴ ጊዜ ጀምሮ እንደነበረው ሁሉ የኢትዮጵያ ተራሮች ነው የሚሆነው።

trinityስለ ግብጽ የተነገረ ሸክም። እነሆ፥ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና እይበረረ ወደ ግብጽ ይመጣል፤ የግብጽም ጣዖታት በፊቱ ይርዳሉ፥ የግብጽም ልብ በውስጥዋ ይቀልጣል።

ግብጻውያንን በግብጻውያን ላይ አስነሣለሁ፤ ወንድምም ወንድሙን፥ ሰውም ባልንጀራውን፥ ከተማም ከተማን፥ መንግሥትም መንግሥትን ይወጋል።

የግብጽም መንፈስ በውስጥዋ ባዶ ይሆናል፥ ምክራቸውንም አጠፋለሁ፤ እነርሱም ጣዖቶቻቸውን በድግምት የሚጠነቍሉትንም መናፍስት ጠሪዎቻቸውንም ጠንቋዮቻቸውንም ይጠይቃሉ።

ግብጻውያንንም በጨካኝ ጌታ እጅ አሳልፌ እሰጣለሁ፤ ጨካኝ ንጉሥም ይገዛቸዋል ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።

ውኆችም ከባሕር ይደርቃሉ፥ ወንዙም ያንሳል ደረቅም ይሆናል።

ወንዞቹም ይገማሉ፥ የግብጽም መስኖች ያንሳሉ ይደርቃሉም፤ ደንገልና ቄጤማ ይጠወልጋሉ።

በዓባይ ወንዝ ዳር ያለው መስክ በዓባይም ወንዝ አጠገብ የተዘራ እርሻ ሁሉ ይደርቃል፥ ይበተንማል፥ አይገኝምም።

ዓሣ አጥማጆቹ ያዝናሉ፥ በዓባይም ወንዝ መቃጥን የሚጥሉት ሁሉ ያለቅሳሉ፥ በውኆችም ላይ መረብ የሚዘረጉት ይዝላሉ። [ትንቢተ ኢሳያስ 191-8]

__

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: