Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 4, 2022
👉 ገብርኤል 👉 ማርያም 👉 ኡራኤል 👉 ጊዮርጊስ 👉 ተክለ ሐይማኖት 😇 ዮሴፍ 👉 መድኃኔ ዓለም
💭 የመጭውን የጌታችንን የልደት በዓል ተከትሎ በሚቀጥሉት ቀናት በመላው ዓለም ትልቅ ትኩረት ልንሰጣቸው የሚገቡንን ክስተቶች እናያለን
❖ ኢትዮጵያ = የአዲስ ኪዳን ርስት ምድር = እስራኤል ዘ–ነፍስ❖
💭 “ቅዱስ ጳውሎስ” ከሚለው ፊልም የተወሰደው ምስል የሚያሳየን ትክክለኛው ክርስቲያናዊ አለባበስ ኢትዮጵያኛው አለባበስ መሆኑን ነው።
[የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ፲፩፥፳፫]
“ከእኔ ጋር ያልሆነ ይቃወመኛል ከእኔ ጋርም የማያከማች ይበትናል።”
ሰባዓሰገል መጥተው ለጌታ ሲሰግዱ ዮሴፍ አየ አምላክ ነህ ሲሉ እጣን ንጉሥ ነህ ሲሉ ወርቅ ፍቅር ነህ ሲሉ ከርቤ ለጌታ ሲገብሩ ዮሴፍ አየ ለካ ይሔ የተወለደው ሕፃን ተራ አይደለም ነገሥታት የሰገዱለት የነገሥታት ንጉሥ ቢሆን ነው ብሎ ድንግል ማርያም የንጉሥ እናት ኢየሱስን የነገሥታት ንጉሥ አምላክ መሆኑን የበኩር ልጅዋን ስትወልደው አወቀ።
ዮሴፍ ታላቅ ነገር ተመለከተ ደማቅ ኮከብ ከሰማይ ዝቅ ከምድር ከፍ ብሎ በቤተልሔም ዋሻ ፊት ለፊት ሲቆም አየ አሀ ልክ ኢያሱ አሞራውያንን በገባዖን ሲዋጋ በጸሎቱ ፀሐይን እንዳቆማት ኢየሱስ ገና በሕፃንነቱ በቤተልሔም ኮኮብን አቁሟል ስለዚህም ይህ ኮከብ የተገዛለት የጌቶች ጌታ ቢሆን ነው ብሎ ኢየሱስ ጌታ ፈጣሪ ድንግል ማርያም እመ ፈጣሪ የጌታ እናት መሆንዋን አወቀ።
________
________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith, Saints/ቅዱሳን, War & Crisis | Tagged: Abiy Ahmed, Addis Ababa, Aksum, Anti-Ethiopia, Axum, ሉሲፈራውያን, ሤራ, ረሃብ, ቅዱስ ዮሴፍ, ቅዱስ ጳውሎስ, ቅድስት ማርያም, ባፎሜት, ትግራይ, አለባበስ, አመፅ, አረመኔነት, አብይ አህመድ, አዲስ አበባ, ኢሳያስ አፈወርቂ, ኢትዮጵያ, ኢየሱስ ክርስቶስ, ኦሮሞ, ወንጀል, የክርስቶስ ተቃዋሚ, የዘመን ፍጻሜ, የጌታ ልደት, የጦር ወንጀል, ይቅርታ, ድንበር, ግራኝ አህመድ, ግድያ, ግፍ, ጠላት, ጥላቻ, ጦርነት, ጭካኔ, ጭፍጨፋ, ጽዮናውያን, ጾመ ነብያት, ፀረ-ኢትዮጵያ, ፍርድ, ፍትሕ, Blockade, Famine, Genocide, HumanRights, Rape, St.Joseph, St.Paul, Starvation, Tigray, War Crimes | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 17, 2020
በጾመ ነብያት ሙስሊሞች ቅዳሴ ላይ የነበሩትን ክርስቲያኖች ደበደቧቸው፤ ቤተ ክርስቲያኑን አቃጠሉ። በሌላ በኩል በእስክንድርያ ከተማ በኮፕት ወገኖቻችን ላይ በደረሰ ሌላ ጥቃት አንድ ክርስቲያን ሲገደል ሁለቱ ቆስለዋል። የክርስቶስ ተቃዋሚው እርኩስ መንፈስ በጥንታውያኑ የኢትዮጵያ፣ የአርሜኒያና የግብጽ ሕዝቦች ዙሪያ እየተሸከረከረ ነው፤ አጋንንት ተለቅቀዋል!
https://premierchristian.news/en/news/article/christian-man-murdered-two-injured-in-egypt-attack
__________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: ሙስሊሞች, ስደት, ኢስላም, ክርስቲያኖች, ኮፕቶች, የክርስቶስ ተቃዋሚ, ጂሃድ, ግብጽ, ጥላቻ, ጾመ ነብያት | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 5, 2020
👉 ገብርኤል 👉 ማርያም 👉 ኡራኤል 👉 ጊዮርጊስ 👉 ተክለ ሐይማኖት 👉 ዮሴፍ
ሰባሰገል መጥተው ለጌታ ሲሰግዱ ዮሴፍ አየ አምላክ ነህ ሲሉ እጣን ንጉሥ ነህ ሲሉ ወርቅ ፍቅር ነህ ሲሉ ከርቤ ለጌታ ሲገብሩ ዮሴፍ አየ ለካ ይሔ የተወለደው ሕፃን ተራ አይደለም ነገሥታት የሰገዱለት የነገሥታት ንጉሥ ቢሆን ነው ብሎ ድንግል ማርያም የንጉሥ እናት ኢየሱስን የነገሥታት ንጉሥ አምላክ መሆኑን የበኩር ልጅዋን ስትወልደው አወቀ።
ዮሴፍ ታላቅ ነገር ተመለከተ ደማቅ ኮከብ ከሰማይ ዝቅ ከምድር ከፍ ብሎ በቤተልሔም ዋሻ ፊት ለፊት ሲቆም አየ አሀ ልክ ኢያሱ አሞራውያንን በገባዖን ሲዋጋ በጸሎቱ ፀሐይን እንዳቆማት ኢየሱስ ገና በሕፃንነቱ በቤተልሔም ኮኮብን አቁሟል ስለዚህም ይህ ኮከብ የተገዛለት የጌቶች ጌታ ቢሆን ነው ብሎ ኢየሱስ ጌታ ፈጣሪ ድንግል ማርያም እመ ፈጣሪ የጌታ እናት መሆንዋን አወቀ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዱቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
_________________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: ሐዋርያው ጳውሎስ, ቅዱስ ዮሴፍ, ቅድስት ማርያም, ኢየሱስ ክርስቶስ, የኢትዮጵያ ልብስ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት, የጌታ ልደት, ጾመ ነብያት, Ethiopian Orthodox Tewahedo Faith | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 1, 2019
ድንቅ ነው፤ አረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀይ ቀለማቱ ወደ ሙሉ ቀይ ከመለወጣቸው በፊት በደንብ ቁልጭ ብለው ይታዩ ነበር፤ ልክ ፀሐይ ስትወጣ ነበር ይህ የታየኝ፤ ካሜራየን እስካወጣ ትንሽ ድብዝዝ አለ ሆኖም ቀለማቱ ይታያሉ፤ ብርሃኑም አለ። ፀሐይ ስትወጣ ነጋ ፥ ጨለማው ጠፋ!
ነቢያት የአምላክን ማዳን ከጠበቁባቸው እና ከገለጡባቸው መንገዶች አንዱ ብርሃን ነው፡፡ ዘመነ ብሉይ መከራ ሥጋ፣ መከራ ነፍስ የፀናበት፣ ሁሉ ነገር አስጨናቂ የሆነበት፣ ሰው ብርሃን ከሆነው አምላክ ጋር የተራራቀበት ስለነበር ያሉበትን ዘመን «ጨለማ» ብለው በመግለጥ ይህንን ጨለማ የሚያስወግድና ወደ ትክክለኛው መንገድ የሚመራ ብርሃን እንዲመጣ እንዲህ እያሉ ይፀልዩ ነበር፡፡ “ብርሃንህንና ጽድቅህን ላክ፤ እነርሱም ይምሩኝ፡፡ አቤቱ ወደ መቅደስህ ተራራና ወደ ማደራያህ ይውሰዱኝ፤” [መዝ. ፵፪፥፫]፡፡ ጌታችንም ወደዚህ ዓለም በመጣ ጊዜ “እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ” በማለት ለዚህ ጸሎት ምላሽ ሰጥቷል (ዮሐ. ፰፥፲፪)፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ስለ ብርሃንነቱ መስክረዋል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ስለ ጌታችን ሰው መኾን (ምሥጢረ ሥጋዌ) በተናገረበት በወንጌሉ የመጀመሪያ ክፍል ጌታችንን ብርሃን ብሎታል፡፡ ‹‹ሕይወት በእርሱ ነበረ፤ ሕይወትም የሰው ብርሃን ነበረ፡፡ ብርሃንም በጨለማ ያበራል፤ ጨለማም አላሰነፈውም፤” [ዮሐ. ፩፥፬–፭]፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ ጌታችን በሚያንጸባርቅ ብርሃን አምሳል እንደ ተገለጠበት ተናግሯል፡፡ “እኩል ቀን በኾነ ጊዜ በመንገድ በሔደ ከፀሐይ ይልቅ የሚበራ መብረቅ በእኔና ከእኔ ጋር ይሔዱ በነበሩት ላይ ከሰማይ ሲያንጸባርቅ አየሁ … አንተ የምታሳድደኝ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ አለኝ፤” [ሐዋ. ፳፮፥፲፫]፡፡
በፈርንጆቹ ዘንድ ዛሬ የወሩ መጀመሪያ ታህሣሥ ፩ ነው፤ እነርሱ ከሚያከብሩት የልደት በዓል በፊት ባሉት ሦስቱ የጾመ ነቢያት ሳምንታት የመጀመሪያ ሰንበትና በጨለማማው የክረምት ወር ሻማ የሚያበሩበት ዕለት የሚጀምረው ዛሬ ነው።
ያው እንግዲህ፤ ጌታችን የዓለም ብርሃኑ ምልክቱን እያሳያቸው/ እያሳየን ነው። በማርያም መቀነት ላይ፣ በኢትዮጵያ ቀለማት ላይ ግልጽ የሆነ ጦርነት እየተካሄደ ነው፤ የዚህ ጦርነት ቀስቃሾችም የዲያብሎስ የግብር ልጆች የሆኑት ዔሳውያን (ምዕራባውያን) እና እስማኤላውያን (ምስራቃውያን) ናቸው።
ለሃገራችን ለኢትዮጵያ ሰላምን ለህዝባችን ፍቅር በረከትን ያዉርድልን፡፡ ጽዮን በምልጃዋ ለሁላችንም ትድረስልን!!!
________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: መስቀል, ሰማይ, ቅድስት ማርያም, ብርሃን, ኢትዮጵያ, ኢየሱስ ክርስቶስ, የማርያም መቀነት, የኢትዮጵያ ቀለማት, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት, የጌታ ልደት, ገዳም, ጽዮን ማርያም, ጾመ ነብያት, Ethiopian Orthodox Tewahedo Faith | Leave a Comment »