Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ጰራቅሊጦስ’

የጰራቅሊጦስ ዕለት የጽዮን ቀለማትና እርግቦች ተዓምር | Miracle of The Colors of Zion + Doves on The Day of Paraclete

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 4, 2023

🌞 የንጋት ጸሐይዋ ብሩህ ሆና ትታያለች፤ ከቤተ ክርስቲያን ከወጣሁ በኋላ ወንበር ላይ ሆኜ ፀሐይዋን እየሞቅኩ ጸሎት ሳደርግ ርጥበት ወይንም እንባ የያዘው አይኔ በግማሽ ተከፍቶ ወደ ፀሐያዋ ሲያተኩር ብሩህ የሆኑት የማርያም መቀነት ቀለማት ዓይኔ ውስጥ ያንጸባርቁ ነበር። ድንቅ ነው! በጸሎት ጊዜ በተደጋጋሚ ይከሰታል። መሞከር የሚሻ ቢሞክረው ጥሩ ነው።

  • የጽዮን (ኢትዮጵያ) ቀለማት / የማርያም መቀነት
  • የማርያም መቀነት ወርደሽ ንገሪያቸው
  • ወራሪና ባንዶች ካለ ባህሪያቸው
  • አይቶ ለመረዳት የታወሩ ናቸው
  • የኢትዮጵያ ሰንደቅ እኔ ነኝ በያቸው
  • በሠማዩ ላይ ሲታይ ቀለም
  • የሷ ነው እንጂ ሌላ አይደለም

______________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ጴንጤው-ሙስሊም ግራኝ በጰራቅሊጦስ ማግስትና በአቡነ አረጋዊ + ጾመ ሐዋርያት ዕለት ‘ምርጫ’ ያደርጋል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 20, 2021

👉 በዚህ ምርጫየሚሳተፉት አህዛብ + መናፍቃን + አማራ + ኦሮሞ ብቻ ናቸው። ምርጫቸው ከዲያብሎስ እና ሳጥናኤል፣ ከዋቄዮ እና አላህ፣ ከባርነትና ሞት እንዲሁም ከኮሌራና ወረርሽኝ መካከል መሆኑ ነው።

💭 A picture tells a thousand words/ አንድ ምስል አንድ ሺህ ቃላትን ይናገራል

👉 ግራኝ ሰኔ ፲፬/14ትን ለ’ምርጫው’የመረጠበት ‘ምስጢር’አቡነ አረጋዊ + ጾመ ሐዋርያት (የሰኔ ጾም)

💭 ዘንድሮም እባቡ ግራኝ እና መንጋው ኢትዮጵያን በብርሃን ፍጥነት እያፈራረሱ በሚያንቀላፋው ሕዝብ ላይ ተመሳሳይ ድራማዎችን በመሥራት ላይ ይገኛሉ። ልክ ከወር በኋላ በኦሮማራ ቃኤላውያኑ ተከታዮቹ “ተመርጫለሁ” የሚሉበትን “የምርጫ ቀን” ሆን ብሎ በማዛወር ሰኔ ፲፬/14 የሰኞ ዕለትን መርጠዋል። አዎ! ተዋሕዶ ክርስቲያኖች ከቤታቸው እና ከቤተ ክርስቲያናቸው የማይርቁበትን የጻድቁ አባታችን የአቡነ አረጋዊ ዕለትን። ጾመ ሐዋርያት (የሰኔ ጾም) የሚገባውም በዚሁ ዕለት ነው።

___________________________________

Posted in Ethiopia, Faith, News/ዜና, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

መንፈስ ቅዱስ በሰው ላይ አድሮ ጥበብን ይገልጣል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 7, 2020

እንኳን ለበዓለ ጰራቅሊጦስ በሰላም አደረሰን!

ጰራቅሊጦስ› የሚለው ቃል ከሦስቱ አካላት አንዱ የኾነው የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ስም ሲኾን፣ ትርጕሙም በጽርዕ (ግሪክ) ቋንቋ

  • 👉 ናዛዚ (የሚናዝዝ)
  • 👉 መጽንዒ (የሚያጸና)
  • 👉 መስተፍሥሒ (የሚያስደስት) ማለት ነው።

መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት በወረደበት ዕለት በቤተ ክርስቲያን የሚከበረው ይህ በዓል ‹በዓለ ጰራቅሊጦስ› ወይም ‹በዓለ ጰንጠቆስጤ› በመባል ይታወቃል። ‹ጰንጠቆስጤ› በግሪክ ቋንቋ በዓለ ኀምሳ፣ የፋሲካ ኀምሳኛ ዕለት፣ በዓለ ሠዊት (የእሸት፣ የመከር በዓል) ማለት ነው (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፱፻፮፱፻፯)

ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ዐሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት፣ ሰባ ሁለቱ አርድእት፣ አምስት መቶው ባልንጀሮች እና ሠላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አንስት በኢየሩሳሌም ከተማ በአንድነት ኾነው በጸሎት ይተጉ ነበር።

ጌታችን በሚያርግበት ጊዜ እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ፤ሲል ለሐዋርያቱ በሰጣቸው የተስፋ ቃል መሠረት በዐረገ በዐሥረኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል (ሉቃ. ፳፬፥፵፱)። ዅሉም በአንድ ቦታ ተሰባስበው ሳሉ በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማለዳ እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ድንገት ከሰማይ ወርዶ የነበሩበትን ቤት ሞላው። ከዚያም የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎች በዅሉም ላይ አረፉባቸው። በዚህ ጊዜ ዅላቸውም መንፈስ ቅዱስ ባደላቸው መጠን በየአገሩ ቋንቋዎች ዅሉ ተናገሩ (ሐዋ.፪፥፩)

ጌታችን መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት የላከበት ይህ ዐቢይ በዓል ዐሥራቱን፣ በኵራቱን፣ ቀዳምያቱን ካህናተ ኦሪት ስለሚቀበሉበት በብሉይ ኪዳን በዓለ ሠዊት ተብሎ ይከበር ነበር። በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ስለ ተቀበሉበት በበዓለ ሠዊት ምትክ በዓለ ጰራቅሊጦስ ገብቶበታል። የበዓለ ትንሣኤ መነሻው የአይሁድ የፋሲካ በዓል ማለትም በግብጽ፣ እስራኤል ከሞት የዳኑበት የመታሰቢያ በዓል እንደ ኾነው ዅሉ፣ ለበዓለ ጰራቅሊጦስም መነሻው ይኸው የአይሁድ የፋሲካ በዓል ነው። የአይሁድ ፋሲካ ከተከበረ ከሰባት ሳምንታት በኋላ በኀምሳኛው ቀን የሩቆቹ ከከተሙበት ወጥተው፣ የቅርቦቹ ከተሰባሰቡበት ተገናኝተው ለበዓሉ ፍጻሜ የሚኾነውን በዓለ ሠዊት (የእሸት በዓል) ያከብሩ ነበር።

ሐዋርያት በጽርሐ ጽዮን ተሰባስበው ሳሉ መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል ወርዶ ሰማያዊ ሀብትን፣ ዕውቀትና ጸጋን አድሏቸዋል መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላም በአእምሮ ጐልምሰዋል፤ ጥቡዓን (ቈራጦች)፣ ጽኑዓን ኾነዋል፤ ለስብከተ ወንጌል የሚፋጠኑበትንና ለሰማዕትነት የሚዘጋጁበትን ልቡና ታድለዋል

ቅድስት በኾነች በጽርሐ ጽዮን በሐዋርያት ላይ የወረደው የእግዚአብሔር አብ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር ወልድ ፍቅር፣ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አንድነት በዅላችን ላይ ይደር፤ እጽፍ ድርብም ይኹን

___________________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

ጰራቅሊጦስ | መንፈስ ቅዱስ በሰው ላይ አድሮ ጥበብን ይገልጣል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 15, 2019

እንኳን ለበዓለ ጰራቅሊጦስ በሰላም አደረሰን!

እግዚአብሔር መንፈስ በሰው ላይ አድሮ ጥበብን ይገልጣል

ጰራቅሊጦስ› የሚለው ቃል ከሦስቱ አካላት አንዱ የኾነው የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ስም ሲኾን፣ ትርጕሙም በጽርዕ (ግሪክ) ቋንቋ

  • ናዛዚ (የሚናዝዝ)
  • መጽንዒ (የሚያጸና)
  • መስተፍሥሒ (የሚያስደስት) ማለት ነው።

መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት በወረደበት ዕለት በቤተ ክርስቲያን የሚከበረው ይህ በዓል ‹በዓለ ጰራቅሊጦስ› ወይም ‹በዓለ ጰንጠቆስጤ› በመባል ይታወቃል። ‹ጰንጠቆስጤ› በግሪክ ቋንቋ በዓለ ኀምሳ፣ የፋሲካ ኀምሳኛ ዕለት፣ በዓለ ሠዊት (የእሸት፣ የመከር በዓል) ማለት ነው (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፱፻፮፱፻፯)

ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ዐሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት፣ ሰባ ሁለቱ አርድእት፣ አምስት መቶው ባልንጀሮች እና ሠላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አንስት በኢየሩሳሌም ከተማ በአንድነት ኾነው በጸሎት ይተጉ ነበር።

ጌታችን በሚያርግበት ጊዜ ‹‹እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ፤›› ሲል ለሐዋርያቱ በሰጣቸው የተስፋ ቃል መሠረት በዐረገ በዐሥረኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል (ሉቃ. ፳፬፥፵፱)። ዅሉም በአንድ ቦታ ተሰባስበው ሳሉ በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማለዳ እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ድንገት ከሰማይ ወርዶ የነበሩበትን ቤት ሞላው። ከዚያም የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎች በዅሉም ላይ አረፉባቸው። በዚህ ጊዜ ዅላቸውም መንፈስ ቅዱስ ባደላቸው መጠን በየአገሩ ቋንቋዎች ዅሉ ተናገሩ (ሐዋ.፪፥፩)

ጌታችን መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት የላከበት ይህ ዐቢይ በዓል ዐሥራቱን፣ በኵራቱን፣ ቀዳምያቱን ካህናተ ኦሪት ስለሚቀበሉበት በብሉይ ኪዳን በዓለ ሠዊት ተብሎ ይከበር ነበር። በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ስለ ተቀበሉበት በበዓለ ሠዊት ምትክ በዓለ ጰራቅሊጦስ ገብቶበታል። የበዓለ ትንሣኤ መነሻው የአይሁድ የፋሲካ በዓል ማለትም በግብጽ፣ እስራኤል ከሞት የዳኑበት የመታሰቢያ በዓል እንደ ኾነው ዅሉ፣ ለበዓለ ጰራቅሊጦስም መነሻው ይኸው የአይሁድ የፋሲካ በዓል ነው። የአይሁድ ፋሲካ ከተከበረ ከሰባት ሳምንታት በኋላ በኀምሳኛው ቀን የሩቆቹ ከከተሙበት ወጥተው፣ የቅርቦቹ ከተሰባሰቡበት ተገናኝተው ለበዓሉ ፍጻሜ የሚኾነውን በዓለ ሠዊት (የእሸት በዓል) ያከብሩ ነበር።

ሐዋርያት በጽርሐ ጽዮን ተሰባስበው ሳሉ መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል ወርዶ ሰማያዊ ሀብትን፣ ዕውቀትና ጸጋን አድሏቸዋል መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላም በአእምሮ ጐልምሰዋል፤ ጥቡዓን (ቈራጦች)፣ ጽኑዓን ኾነዋል፤ ለስብከተ ወንጌል የሚፋጠኑበትንና ለሰማዕትነት የሚዘጋጁበትን ልቡና ታድለዋል

ቅድስት በኾነች በጽርሐ ጽዮን በሐዋርያት ላይ የወረደው የእግዚአብሔር አብ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር ወልድ ፍቅር፣ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አንድነት በዅላችን ላይ ይደር፤ እጽፍ ድርብም ይኹን።

___________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

መታየት ያለበት | ከኢየሱስ ክርስቶስ የመጣልንን መንፈስ ቅዱስ ያገኘንበት የመጀመሪያው ቤተክርስቲያን ይህ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 26, 2018

ይህ የሚመስጥና የሚያስለቅስ ታሪክ ነው።

ክርስትና እዚህ ቦታ ላይ ነው የተወለደው! ጰራቅሊጦስ ወይም ጰንጠቆስጤ ዕለት ከኢየሱስ ክርስቶስ የመጣልንን መንፈስ ቅዱስ ያገኘነው እዚህ ቦታ ላይ ነው።

በዓለም በጣም አስፈላጊ/ ተፈላጊ ከሆኑት ቦታዎች መካከል አንዱ ይህ ነው።

በዓለም የመጀመሪያው የቤ/ ክርስቲያን ህንፃ በጽዮን ተራራ ድብቅ በሆነ ቦታ መሬት ሥር ውስጥ ተቀብሮ ነው የሚገኘው።

በእየሩሳሌም የሚገኘው ይህ እጅግ በጣም ታሪካዊ ቦታ በግሪክ ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስቲያን ቁጥጥር ሥር ነው።

በዚህ ቅዱስ ቦታ፡ ልክ በኢየሱስ ዘመን እንደነበረው አሁንም በተከታዮቹ ላይ በደል ሲደርስባቸው

ማየቱ በጣም የሚያስገርም ነገር ነው።

ከ ሮማውያን ወታደሮች ለማምለጥ መሬት ውስጥ ተደብቀው ነበር ጸሎት ሲያደርጉ የነበረው። (ልክ እንደ ላሊበላ ዓብያተክርስቲያናት)

/ ያዕቆብ የመጀመሪያዋ የዚህች ቤ/ክርስቲያን ሐዋርያ ነበር።

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደዚህ ቤተክርስቲያን ትመጣ ነበር።

ኢየሱስ የ ያዕቆብ ወንድም ነበር። ያዕቆብ የኢየሱስን ትንሣኤ ካየ በኋላ አመነ፡ ከዚያም የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን ሐዋርያ ለመሆን በቃ።

የመጀማሪያዎቹ ክርስቲያኖች በ44 .ም አካባቢ ለሮማውያኑ ህገ ወጥ ነበሩ፡ ስለዚህ ያሳድዷቸውና ይበድሏቸው ነበር። ለዚህም ነበር በመሬት ውስጥ ተደብቆ እንዲሠራ የተደረገው።

በዚህም ዘመን ቢሆን ቤተክርስቲያኑ ታሥሯል፤ ልክ በኢየሩሳሌም እንዳለው፡ ወይም በአገራችንም እንዳሉት ገዳማትና ቅዱሳን ቦታዎቻችን፡ ይህም ቤተክርስቲያን አሁንም ድረስ ፈተናዎች ይበዙበታል። የቤተክርስቲያኑን በር ለመክፈት እንኳን ልዩ ፈቃድ ያስፈልጋል፤ ለጎብኚዎች ዝግ ነው፣ ማደስና መጠገንም አይፈቀድም። እንዲያውም ጽንፈኛ የሃይማኖት አክራሪዎች ወደዚያ እየሄዱ፡ በመስክቶት በኩል፡ ውስጥ ድረስ ቆሻሻ ይደፉበታል። ፀረክርስቶሱ ነው ኢየሩሳሌምንም የሚቆጣጠራትና።

ልክ በኢየሱስ ዘመን እንደነበረው አሁንም በተከታዮቹ ላይ በደል ሲደርስባቸው ማየቱ በጣም የሚገርም ነገር ነው።

በእውነትም፡ ይህ የሚያነቃቃና የሚመስጥ ድንቅ ቦታ ነው።

ይህ የመጀመሪያው ቤ/ ክርስቲያን የመጨረሻው ቤ/ ክርስቲያን ይሆንን?

እግዚአብሔር መንፈስ በሰው ላይ አድሮ ጥበብን ይገልጣል

ጰራቅሊጦስ የሚለው ቃል ከሦስቱ አካላት አንዱ የኾነው የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ስም ሲኾን፣ ትርጕሙም በጽርዕ (ግሪክ) ቋንቋ

  • ናዛዚ (የሚናዝዝ)
  • መጽንዒ (የሚያጸና)
  • መስተፍሥሒ (የሚያስደስት) ማለት ነው፡፡

መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት በወረደበት ዕለት በቤተ ክርስቲያን የሚከበረው ይህ በዓል ‹በዓለ ጰራቅሊጦስ› ወይም ‹በዓለ ጰንጠቆስጤ› በመባል ይታወቃል፡፡

በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት የተማረኩ አሕዛብም ‹‹ምን እናድርግ?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ከክፋታቸው ተመልሰው፣ ንስሐ ገብተው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንዲጠመቁ ነገሯቸዋል፡፡ በዚያችም ሰዓት ሦስት ሺህ ሕዝብ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ ተጠምቋል (ሐዋ.፪፥፩፵፩)፡፡

አዳምና ልጆቹን ከዲያብሎስ ተገዢነት እና ከሲኦል ባርነት ያወጣው ቸሩ መድኃኔ ዓለም የወደቁትን ወገኖቻችን ያንሳቸው፣ ጰራቅሊጦስንም ያውርድላቸው።

እንኳን አደረሰን!

______

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

በዓለ ጰራቅሊጦስ | የእግዚአብሔር መንፈስ በሰው ላይ ሲያድር ጥበብን ይገልጣል በአእምሮ ያጐለምሳል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 3, 2017

በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው: ግንቦት ፳፮ ቀን ፳፻፱ ዓ.

ጰራቅሊጦስ የሚለው ቃል ከሦስቱ አካላት አንዱ የኾነው የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ስም ሲኾን፣ ትርጕሙም በጽርዕ (ግሪክ) ቋንቋ

  • ናዛዚ (የሚናዝዝ)
  • መጽንዒ (የሚያጸና)
  • መስተፍሥሒ (የሚያስደስት) ማለት ነው፡፡

መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት በወረደበት ዕለት በቤተ ክርስቲያን የሚከበረው ይህ በዓል ‹በዓለ ጰራቅሊጦስ› ወይም ‹በዓለ ጰንጠቆስጤ› በመባል ይታወቃል፡፡ ‹ጰንጠቆስጤ› በግሪክ ቋንቋ በዓለ ኀምሳ፣ የፋሲካ ኀምሳኛ ዕለት፣ በዓለ ሠዊት (የእሸት፣ የመከር በዓል) ማለት ነው (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፱፻፮፱፻፯)፡፡

ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ዐሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት፣ ሰባ ሁለቱ አርድእት፣ አምስት መቶው ባልንጀሮች እና ሠላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አንስት በኢሩሳሌም ከተማ በአንድነት ኾነው በጸሎት ይተጉ ነበር፡፡ ጌታችን በሚያርግበት ጊዜ ‹‹እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ፤›› ሲል ለሐዋርያቱ በሰጣቸው የተስፋ ቃል መሠረት በዐረገ በዐሥረኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል (ሉቃ. ፳፬፥፵፱)፡፡ ዅሉም በአንድ ቦታ ተሰባስበው ሳሉ በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማለዳ እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ድንገት ከሰማይ ወርዶ የነበሩበትን ቤት ሞላው፡፡ ከዚያም የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎች በዅሉም ላይ አረፉባቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ዅላቸውም መንፈስ ቅዱስ ባደላቸው መጠን በየአገሩ ቋንቋዎች ዅሉ ተናገሩ (ሐዋ.፪፥፩)፡፡

ጌታችን መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት የላከበት ይህ ዐቢይ በዓል ዐሥራቱን፣ በኵራቱን፣ ቀዳምያቱን ካህናተ ኦሪት ስለሚቀበሉበት በብሉይ ኪዳን በዓለ ሠዊት ተብሎ ይከበር ነበር፡፡ በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ስለ ተቀበሉበት በበዓለ ሠዊት ምትክ በዓለ ጰራቅሊጦስ ገብቶበታል፡፡ የበዓለ ትንሣኤ መነሻው የአይሁድ የፋሲካ በዓል ማለትም በግብጽ፣ እስራኤል ከሞት የዳኑበት የመታሰቢያ በዓል እንደ ኾነው ዅሉ፣ ለበዓለ ጰራቅሊጦስም መነሻው ይኸው የአይሁድ የፋሲካ በዓል ነው፡፡ የአይሁድ ፋሲካ ከተከበረ ከሰባት ሳምንታት በኋላ በኀምሳኛው ቀን የሩቆቹ ከከተሙበት ወጥተው፣ የቅርቦቹ ከተሰባሰቡበት ተገናኝተው ለበዓሉ ፍጻሜ የሚኾነውን በዓለ ሠዊት (የእሸት በዓል) ያከብሩ ነበር፡፡

ከግብጽ እስከ ከነዓን ምድር የደረሰው የእንስሳት መሥዋዕት ሲጠናቀቅ በኀምሳኛው ቀን ይሰባሰብ የነበረው የአይሁድ ጉባኤም መንፈስ ቅዱስ ከወረደበት ዕለት ጀምሮ ተበትኗል፡፡ መሥዋዕተ ኦሪቱ በአማናዊው መሥዋዕት በኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋና ደም እንደ ተለወጠ ዅሉ ጉባኤ አይሁድም በኢየሩሳሌም ከተማ በተሰበሰቡ በቅዱሳን ሐዋርያት ጉባኤ ተለውጧል (ተቀይሯል)፡፡ ይህችውም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ከጉባኤያት ዅሉ ከፍ ከፍ ያለች የመንፈስ ቅዱስ ቤት ናትና፡፡ ‹‹ከዅሉ በላይ በምትኾን፣ ሐዋርያት በሰበሰቧት፣በአንዲት፣ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን፤›› እንዳሉ ሠለስቱ ምእት በጸሎተ ሃይማኖት፡፡

ሐዋርያት በጽርሐ ጽዮን ተሰባስበው ሳሉ መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል ወርዶ ሰማያዊ ሀብትን፣ ዕውቀትና ጸጋን አድሏቸዋል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላም በአእምሮ ጐልምሰዋልጥቡዓን (ቈራጦች)፣ ጽኑዓን ኾነዋል፤ ለስብከተ ወንጌል የሚፋጠኑበትንና ለሰማዕትነት የሚዘጋጁበትን ልቡና ታድለዋል፡፡ ቀድሞ ይናገሩት ከነበሩት ቋንቋ በተጨማሪ ፸፩ ቋንቋዎች ተገልጠውላቸው ምሥጢራትን በልዩ ልዩ ቋንቋ መተርጐም ጀምረዋል፡፡ ሐዋርያት በየገአሩ ቋንቋ ሲናገሩ የሰሙ በዚያ የነበሩ ሰዎችም በሐዋርያት ተገረሙ፡፡ አንዳንድ የአይሁድ ወገኖች ግን በሐዋርያት ላይ ያዩት ክሥተት አዲስ ነገር ስለኾነባቸው ‹‹ጉሽ ጠጅ ጠጥተው ሰክረው የኾነ ያልኾነውን ይቀባጥራሉ›› እያሉ ሐዋርያትን ያሟቸው ነበር፡፡

ቅዱስ ጴጥሮስም ይህንን ዐሳባቸውን በመንፈስ ቅዱስ አውቆ ‹‹ሰክረዋል የምትሉ

እናንተ እንደምትጠራጠሩት አይደለም፡፡ ጊዜው ማለዳ፣ ሰዓቱም ገና ሦስት ሰዓት ነውና፡፡ ዳሩ ግን በነቢዩ ኢዩኤል ‹ከዚህም በኋላ እንዲህ ይኾናል፤ መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ዅሉ ላይ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ› (ኢዩ.፪፥፳፰) ተብሎ የተነገረው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ፣ ይህንን ድንቅ ተአምር ያደረገው እናንተ የሰቀላችሁት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤›› በማለት ሰፊ ትምህርተ ወንጌል ሰጥቷቸዋል፡፡

በትምህርቱም ነቢያት ትንቢት የተናገሩለት፣ ምሳሌ የመሰሉለት አምላክ ወልደ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ መነሣቱን፣ ማረጉንና ዳግም በክብር በምስጋና መጥቶ በሕያዋንና በሙታን ላይ የሚፈረድ መኾኑን ሐዋርያት እንደሚመሰክሩ በአይሁድ ፊት አሰምቶ ተናገረ፡፡ በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት የተማረኩ አሕዛብም ‹‹ምን እናድርግ?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ከክፋታቸው ተመልሰው፣ ንስሐ ገብተው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንዲጠመቁ ነገሯቸዋል፡፡ በዚያችም ሰዓት ሦስት ሺህ ሕዝብ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ ተጠምቋል (ሐዋ.፪፥፩፵፩)፡፡

ቅዱሳን ሐዋርያት፡– ‹‹በዚህች ቀን በሦስት ሰዓት ኢየሱስ ክርስቶስ ጰራቅሊጦስን ልኮልናልና በላያችን ኃይልን ሞላ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ በሕያዋንና በሙታን ይፈርድ ዘንድ ሥልጣን እንዳለው በአዲስ ቋንቋ ተናገርን፤›› በማለት በዕለቱ ያዩትንና የተደረገላቸውን፣ እንደዚሁም የበዓሉን ታላቅነት ከመሰከሩ በኋላ ይህንን በዓል ማክበር እንደሚገባ አዝዘዋል፤ በዚህ ወቅት መጾምና ማዘን ተገቢ አለመኾኑንም ተናግረዋል (ዲድስቅልያ ፴፥፴፰፴፱፤ ፴፩፥፷፱)፡፡

ከዚህ ላይ ማስተዋል የሚገባን ቁም ነገር ‹መንፈስ ቅዱስ ወረደ› ሲባል፣ በሰዉኛ ቋንቋ መንፈስ ቅዱስ ከከፍታ ወደ ዝቅታ፣ ከሩቅ ወደ ቅርብ መምጣቱን ወይም መምጣቱን ለመናገር አይደለም፡፡ የእግዚአብሔር መንፈስ በሐዋርያት ላይ አድሮ ሰማያዊ ሀብትን፣ ዕውቀትን፣ ጥበብንና ልዩ ልዩ ጸጋን ማደሉን ለማስረዳት ነው እንጂ፡፡ ይኸውም ሥራዉን በሰው ላይ መግለጡን፣ ጸጋዉንም ማብዛቱን ለማመልከት የሚያገለግል ቋንቋ ነው፡፡ ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ ወረደ የሚለው ትምህርት መንፈስ ቅዱስን በቦታ፣ በጊዜና በወሰን መገደቡን አያመለክትም፡፡ የእግዚአብሔር መንፈስ በዓለሙ ዅሉ የሞላ ነውና፡፡ በሰው ላይ አድሮ ጥበብን ሲገልጥ ግን ‹ሞላ፤ አደረ፤ ወረደ› ተብሎ ይነገራል፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ለጊዜው ለሐዋርያት ቢሰጥም፣ በእነርሱ ላይ ብቻ ሳይገደብ እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ በምእመናን ላይም አድሮ ይኖራልና፡፡

በዓለ ትንሣኤውን በደስታ እንድናሳልፍ ፈቅዶ እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ጠበቀን፣ አሁን ደግሞ በጾም፣ በጸሎት ኾነን እርሱን የምናመሰግንበትን ወቅት ስላመጣልን አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ለዘለዓለሙ የተመሰገነ ይኹን፡፡

የዘመነ ጰራቅሊጦስ ምንባባት

በዓለ ጰራቅሊጦስ ሀብተ መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት የተሰጠበት፤ ብዙ ሺሕ ምእመናን የሥላሴን ልጅነት ያኙበት ዕለት በመኾኑ ‹የቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን› ተብሎ ይጠራል፡፡ በዓሉ ከዘጠኙ የጌታችን ዐበይት በዓላት አንዱ ሲኾን፣ በያዝነው ዓመትም ግንቦት ፳፯ ቀን ይዘከራል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከወረደበት ሰንበት (ከኀምሳኛው ቀን) ጀምሮ እስከሚቀጥለው ሰንበት ያለው ጊዜም (ስምንቱ ቀናት) ‹ዘመነ ጰራቅሊጦስ› ወይም ‹ሰሙነ ጰራቅሊጦስ› ይባላል፡፡ ይህም መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ ስለ መውረዱና በምእመናን ላይ ስለ ማደሩ የሚነገርበት ወቅት ነው፡፡ በዚህ ሰሙን በቤተ ክርስቲያን የሚነገረው ቃለ እግዚአብሔር፣ የሚሰጠውም ትምህርት የመንፈስ ቅዱስን በሐዋርያት ላይ መውረድ የሚመለከት ነው፡፡

በበዓለ ጰራቅሊጦስ ዕለት ‹ይትፌሣሕ› የሚለው የትንሣኤ መዝሙር በቤተ ክርስቲያን ይዘመራል፡፡ በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ የቅዱሳት መጻሕፍት ክፍሎችም በትንሣኤ ዕለት የተነበቡት ናቸው፡፡ ምንባባቱ ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ በመነሣቱ፣ በማረጉና መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት በመላኩ፤ እንደዚሁም ሥጋውን ቈርሶ፣ ደሙን አፍስሶ የሰውን ልጅ ከዘለዓለም ሞት በማዳኑ የሰው ዘር ብቻ ሳይኾን የሰማይ መላእክት፣ የምድር ፍጥረታት ሳይቀሩ ሐሤት እንደሚያደርጉ፤ ምድርም በክርስቶስ ደም በመንጻቷ የጌታችንን ትንሣኤ በደስታ እንደምታከብር የሚያስረዳ መልእክት አላቸው፡፡

ከበዓለ ጰራቅሊጦስ በኋላ ባሉት ሰንበታት (እሑዶች) የሚዘመሩ መዝሙራትም ትንሣኤን፣ ዕርገትን፣ የመንፈስ ቅዱስን መውረድ የሚያስረዱ ሲኾኑ፣ ምሥጢራቸውም ከሙታን ተለይቶ ለተነሣው፣ አዳምና ልጆቹን ከዲያብሎስ ተገዢነት እና ከሲኦል ባርነት ላወጣቸው ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ማቅረብ እንደሚገባ ያስተምራል፡፡ ከኀምሳኛው ቀን (ከበዓለ ጰራቅሊጦስ) ቀጥሎ በሚመጣው እሑድ (በስምንተኛው ቀን) የሚዘመረው መዝሙር፡– ‹‹ወረደ መንፈስ ቅዱስ ላዕለ ሐዋርያት ከመ ዘእሳት ወተናገሩ በነገረ ኵሉ በሐውርት …›› የሚል ሲኾን፣ ትርጕሙም መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል በሐዋርያት ላይ መውረዱንና በእርሱ ኃይል በዓለሙ ዅሉ ቋንቋዎች መናገራቸዉን የሚያስረዳ ነው፡፡

በዚህ ዕለት በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች፡ኤፌ.፬፥፩፲፯፤ ፩ኛዮሐ.፪፥፩፲፰፤ ሐዋ.፪፥፩፲፰፤ መዝ.፷፯፥፲፰ (ምስባክ)፤ ዮሐ.፲፬፥፩፳፪ ሲኾኑ፣ የምንባባቱ ፍሬ ሐሳብም የሚከተለው ነው፤

የጳውሎስ መልእክት፡እያንዳንዳችን መንፈስ ቅዱስ በገለጸልን መጠን የየራሳችን ልዩ ልዩ ጸጋ እንዳለን፤ የዮሐንስ መልእክት፡የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚፈጽም ለዘለዓለም ሕያው እንደ ኾነ፤ የሐዋርያት ሥራ፡መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ እንደ ወረደና በዓለሙ ዅሉ ቋንቋዎች መናገር እንደቻሉ፤ መዝሙረ ዳዊት (ምስባኩ)እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ልዩ ልዩ ጸጋን እንደሚሰጥ፤ የዮሐንስ ወንጌል፡እግዚአብሔር እኛን ልጆቹን እንደ ወላጅ አልባ እንደማይተወን ያስረዳሉ፡፡ ቅዳሴው ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ ሲኾን፣ ይህም ምሥጢረ ሥላሴን፣ የጌታችንን ሰው መኾን፣ ሕማሙን፣ ሞቱን፣ ትንሣኤዉን፣ ዕርገቱንና መንፈስ ቅዱስን መላኩን ይናገራል፡፡

ቅድስት በኾነች በጽርሐ ጽዮን በሐዋርያት ላይ የወረደው የእግዚአብሔር አብ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር ወልድ ፍቅር፣ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አንድነት በዅላችን ላይ ይደር፤ እጽፍ ድርብም ይኹን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

ምንጭ

በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት የተማረኩ አሕዛብም ‹‹ምን እናድርግ?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ከክፋታቸው ተመልሰው፣ ንስሐ ገብተው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንዲጠመቁ ነገሯቸዋል፡፡ በዚያችም ሰዓት ሦስት ሺህ ሕዝብ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ ተጠምቋል (ሐዋ.፪፥፩፵፩)፡፡

አዳምና ልጆቹን ከዲያብሎስ ተገዢነት እና ከሲኦል ባርነት ያወጣው ቸሩ መድኃኔ ዓለም የወደቁትን ወገኖቻችን ያንሳቸው፣ ጰራቅሊጦስንም ያውርድላቸው

__

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

በ ዓ ለ ጰ ራ ቅ ሊ ጦ ስ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 19, 2016

Peraclitos2

*ጰራቅሊጦስ* የሚለው ቃል ከሦስቱ አካላት አንዱ ለኾነው ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ስሙ ሲኾን፣ ትርጕሙም በጽርዕ (ግሪክ) ቋንቋ ናዛዚ (የሚናዝዝ)፣ መጽንዒ (የሚያጸና)፣ መስተፍሥሒ (የሚያስደስት) ማለት ነው፡፡ በዓለ ጰራቅሊጦስ በሌላ ቃል በዓለ ጰንጠቆስጤ በመባልም ይታወቃል፡፡ ይኸውም በግሪክ ቋንቋ በዓለ ኀምሳ፣ የፋሲካ ኀምሳኛ ዕለት፣ በዓለ ሠዊት (የእሸት፣ የመከር በዓል) ማለት ነው /ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፱፻፮ እና ፱፻፯/፡፡

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ፲፪ቱ ደቀ መዛሙርት፣ ፸፪ቱ አርድእት፣ ፭፻ው ባልንጀሮችና ፴፮ቱ ቅዱሳት አንስት በኢሩሳሌም ከተማ በአንድነት ኾነው ለጸሎት ይተጉ ነበር፡፡ በሚያርግበት ጊዜም *እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ፤* /ሉቃ. ፳፬፥፵፱/ ሲል ለሐዋርያቱ በገባላቸው ቃል መሠረት ባረገ በ፲ኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል፡፡

በሐዋርያት ሥራ እንደ ተጻፈው በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማለዳ ኹሉም በአንድ ቦታ ተሰብስበው ሳሉ እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ድንገት ከሰማይ መጣና የነበሩበትን ቤት ሞላው፡፡ ከዚያም እንደ እሳት የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎች በኹሉም ላይ ተቀመጡባቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ኹላቸውም መንፈስ ቅዱስን ከተሞሉ በኋላ መንፈስ ቅዱስ ባደላቸው መጠን በየአገሩ ቋንቋዎች ኹሉ መናገር ጀመሩ /ሐዋ.፪፥፩/፡፡ ጌታችን መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት የላከበት ይህ ዐቢይ በዓል ጰራቅሊጦስ ይባላል፡፡

ጌታችን ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ ከ፶ኛው፤ ከዐረገ ከ፲ኛው ቀን ጀምሮ እስከሚቀጥለው እሑድ ድረስ ያለው ወቅትም ዘመነ ጰራቅሊጦስ ተብሎ የሚጠራ ሲኾን፣ ይህ በዓል ካህናተ ኦሪት ዐሥራቱን፣ በኵራቱን፣ ቀዳምያቱን ይቀበሉበት ነበርና በብሉይ ኪዳን በዓለ ሠዊት ይባል ነበር፡፡ በበዓለ ጰራቅሊጦስም ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለውበታልና በበዓለ ሠዊት ምትክ በዓለ ጰራቅሊጦስ ገብቶበታል፡፡

የበዓለ ትንሣኤ መነሻው የአይሁድ የፋሲካ በዓል ማለትም በግብፅ እስራኤል ከሞት የዳኑበት የመታሰቢያ በዓል እንደ ኾነው ኹሉ፣ ለበዓለ ጰራቅሊጦስም መነሻው ይኸው የአይሁድ የፋሲካ በዓል ነው፡፡ የአይሁድ ፋሲካ ከተከበረ ከሰባት ሳምንታት በኋላ በ፶ኛው ቀን የሩቆቹ ከከተሙበት ወጥተው፣ የቅርቦቹ ከተሰባሰቡበት ተገናኝተው ለበዓሉ ፍጻሜ የሚኾነውን በዓለ ሠዊት ያከብሩ ነበር፡፡

ከግብፅ እስከ ከነዓን ምድር የደረሰው የእንስሳት መሥዋዕት ሲጠናቀቅ በ፶ኛው ቀን ይሰባሰብ የነበረው የአይሁድ ጉባኤም መንፈስ ቅዱስ ከወረደበት ዕለት ጀምሮ ተበትኗል፡፡ መሥዋዕተ ኦሪቱ በአማናዊው መሥዋዕት በኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋና ደም እንደ ተለወጠ ኹሉ ጉባኤ አይሁድም በኢየሩሳሌም ከተማ በተሰበሱ በቅዱሳን ሐዋርያት ጉባኤ ተለውጧል (ተቀይሯል)፡፡ ይህችውም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ *ከኹሉ በላይ በምትኾን፣ ሐዋርያት በሰበሰቧት በአንዲት፣ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን፤* እንዳሉ ሠለስቱ ምእት /ጸሎተ ሃይማኖት/፡፡

ሐዋርያት በጽርሐ ጽዮን ተሰብስበው ሳሉ መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል ወርዶ ሰማያዊ ሀብትን፣ ዕውቀትና ጸጋን አድሏቸዋልና ቀድሞ ይናገሩት ከነበሩት ከዕብራይስጥ ቋንቋ በተጨማሪ ፸፩ ቋንቋዎች ተገልጸውላቸው ምሥጢራትን መተርጐም ጀምረዋል፡፡ ሐዋርያት በየገአሩ ቋንቋ ሲናገሩ የሰሙ ከአይሁድ ወገን አንዳንዶቹም ሐዋርያት ጉሽ ጠጅ ጠጥተው ሰክረው የኾነ ያልኾነውን ይቀባጥራሉ ይሏቸው ነበር፡፡

ቅዱስ ጴጥሮስም ይህንን ዐሳባቸውን በመንፈስ ቅዱስ አውቆ *ሰክረዋል የምትሉ እናንተ እንደምትጠራጠሩት አይደለም፡፡ ጊዜው ማለዳ፣ ሰዓቱም ገና ሦስት ሰዓት ነውና፡፡ ዳሩ ግን በነቢዩ ኢዩኤል ከዚህም በኋላ እንዲህ ይሆናል፤ መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ አፈስሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፤ /ኢዩ.፪፥፳፰/ ተብሎ የተነገረው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ይህንን ድንቅ ተአምር ያደረገው እናንተ የሰቀላችሁት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤* በማለት ሐዋርያት ኢየሱስ ክርስቶስ ነቢያት ትንቢት የተናገሩለት፣ ምሳሌ የመሰሉለት አምላክ ወልደ አምላክ መኾኑን፣ ከሙታን ተለይቶ መነሣቱን፣ ማረጉንና ዳግም በክብር በምስጋና መጥቶ በሕያዋንና በሙታን ላይ የሚፈረድ መኾኑን እንደሚመሰክሩ በአይሁድ ፊት አሰምቶ ተናገረ፡፡

በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት የተማረኩ አሕዛብም ምን እናድርግ ብለው በጠየቁት ጊዜ ከክፋታቸው ተመልሰው፣ ንስሐ ገብተው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንዲጠመቁ ነገራቸው፡፡ በዚያችም ሰዓት ሦስት ሺህ ሕዝብ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ ተጠምቋል /ሐዋ.፪፥፩፵፩/፡፡ ይህም ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላ ያደረባቸው የማሳመን ጸጋና ተአምራትን የማድረግ ኃይላቸው እንደ በዛላቸው ያመላክታል፡፡

ይህ ዕለት ሀብተ መንፈስ ቅዱስ የተሰጠበት፤ ብዙ ሺሕ ምእመናን የተገኙበት ዕለት በመኾኑ ሊቃውንት የቤተ ክርስቲን የልደት ቀን በማለት ይጠሩታል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላ ሐዋርያት በአእምሮ ጎለመሱ፤ ጥቡዓን (ቈራጦች)፣ ጽኑዓን ኾኑ፤ ለስብከተ ወንጌል የሚፋጠኑበትንና ለሰማዕትነት የሚዘጋጁበትን ልቡና ታደሉ፡፡

ቅዱሳን ሐዋርያት *በዚህች ቀን በሦስት ሰዓት ኢየሱስ ክርስቶስ ጰራቅሊጦስን ልኮልናልና በላያችን ኃይልን ሞላ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ በሕያዋንና በሙታን ይፈርድ ዘንድ ሥልጣን እንዳለው በአዲስ ቋንቋ ተናገርን፤* በማለት በዕለቱ ያዩትንና የተደረገላቸውን፣ እንደዚሁም ስለ በዓሉ ታላቅነት መስክረው ይህንን በዓል ማክበር እንደሚገባ ወስነዋል፡፡ እንደዚሁም በዚህ ወቅት (በበዓለ ኀምሳ) መጾምና ማዘን እንደማይገባ አዝዘዋል /ዲድስቅልያ ፴፥፴፰፴፱፤ ፴፩፥፷፱/፡፡

የጰራቅሊጦስ መዝሙርና ምንባባት

በዓለ ጰራቅሊጦስ ከዘጠኙ የጌታችን ዐበይት በዓላት አንዱ ሲኾን በዕለቱ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የሚዘመረው የቅዱስ ያሬድ መዝሙርም ይትፌሣሕ የሚለው የትንሣኤ መዝሙር ነው፡፡ እንደ መዝሙሩ ኹሉ በጰራቅሊጦስ በዓል በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ የቅዱሳት መጻሕፍት ክፍሎችም በትንሣኤ ዕለት የተነበቡ ምንባባት ናቸው፡፡

እነዚህም ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ በመነሣቱ፣ በማረጉና መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት በመላኩ፤ እንደዚሁም ሥጋውን ቈርሶ፣ ደሙን አፍስሶ የሰውን ልጅ ከዘለዓለም ሞት በማዳኑ የሰው ዘር ብቻ ሳይኾን የሰማይ መላእክት፣ የምድር ፍጥረታት ሳይቀሩ ሐሤት እንደሚያደርጉ፤ ምድርም በክርስቶስ ደም በመንጻቷ የጌታችንን ትንሣኤ በደስታ እንደምታከብር ያስረዳሉ፡፡

ከበዓለ ጰራቅሊጦስ በኋላ ባሉት ሰንበታት (እሑዶች) የሚዘመሩ መዝሙራት ትንሣኤን፣ ዕርገትን፣ የመንፈስ ቅዱስን መውረድ የሚያስረዱ ሲኾኑ፣ ዓላማቸውም ከሙታን ተለይቶ ለተነሣው፣ አዳምና ልጆቹን ከዲያብሎስ ባርነትና ከሲኦል ላወጣቸው ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ማቅረብ ነው፡፡

ከዚሁ ኹሉ ጋር ለማሳሰብ የምንፈልገው ቁም ነገር በዓለ ጰራቅሊጦስን ተከትለው ሁለት ዐበይት አጽዋማት እንደሚጀመሩ ማስታዎስ ነው፡፡ እነዚህም ጾመ ሐዋርያት እና ጾመ ድኅነት (ረቡዕና ዓርብ) ናቸው፡፡ ቍጥራቸውም ከሰባቱ አጽዋማት ውስጥ ነው፡፡ ስለኾነም ኹላችንም ልንጾማቸው እንደሚገባ በቤተ ክርስቲያን ሕግ ታዝዟል፡፡ ይህም ከቀደሙ አባቶቻችን ጀምሮ የመጣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥርዓት እንጂ እንግዳ ሕግ አይደለም፡፡

ምንጭ

__

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , | Leave a Comment »

Elder Paisios – The Holy War

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 7, 2014

The spirit of lukewarmness reigns. There’s no manliness at all! We’ve been spoiled for good! How does God still tolerate us? Today’s generation is the generation of indifference. There are no warriors The majority are fit only for parades.”

 
SpiritualBattle
 
There’s a war on today, a holy war…”
 
If the Metropolitans are silent, then who will speak?”
 
That unsettles me is the reigning mood of tranquility. Something is in the works. We still haven’t understood properly either what’s going on, or the fact that we will die. I don’t know what will come of this. The situation is very complicated. The fate of the world depends on just a few people, but God is still putting on the brakes. We have to pray a lot, and with pain in our hearts, so that God will intervene: our times are very hard to understand. A lot of ash, rubbish, and indifference has accumulated, and a strong wind will be needed to blow it all away.
 
It’s frightening! The Tower of Babel is upon us! Divine intervention is needed: Great upheavals are happening. What a bedlam! The minds of whole nations are in confusion. But in spite of the ferment I feel a certain consolation inside, a certain confidence. God still dwells in a part of the Christians. God’s people, people of prayer, still remain, and God in his all-goodness still tolerates us and will put everything in order. Don’t be afraid! We’ve gone through many storms, and still haven’t perished. So should we be afraid of the storm which is now gathering? We’ll not perish this time either”
 
God loves us. In Man there’s a hidden power which comes out when necessary. The difficult years will be few. Just a lot of thunder.
 
Don’t get upset in the least, for God is above everything. He rules everyone and will bring all to the defendant’s bench to answer for what they’ve done, according to which each will receive his just desserts from God. Those who’ve in some way helped the cause of good will be rewarded, and those who do evil will be punished. God will put everyone in their place in the end, but each of us will answer for what they did in these difficult years, both in prayer and in deeds.
 
Today they’re trying to destroy faith, and for the edifice of faith to fall they quietly pull out one stone, then another. But we’re all responsible for the destruction; not just those who destroy but we who see how faith is being undermined and make no effort to strengthen it. As a result the seducers are emboldened to create even greater difficulties for us, and their rage against the Church and the monastic life increases.
 
Today’s situation can be resisted only spiritually, not by worldly means. The storm will continue to rage a bit, will throw all the flotsam, everything unnecessary, onto the shore, and then the situation will become clearer. Some will receive their reward, while others will have to pay their debts.
 
Today there are many who strive to corrupt everything: the family, the youth, the Church. In our day it’s a true witness to speak up for one’s people, for the state is waging war against divine law. It’s laws are directed against the Law of God.
 
But we are responsible for not letting the enemies of the Church corrupt everything. Though I’ve heard even priests say: “Don’t get involved in that. It’s none of your business!” If they had reached such a non-striving condition through prayer I would kiss their feet. But no! They’re indifferent because they want to please everyone and live in comfort.
 
Indifference is unacceptable even for laymen, and all the more so for the clergy. An honest, spiritual man doesn’t do anything with indifference. “Cursed be he that doeth the work of the Lord deceitfully”, says the Prophet Jeremiah (Jer. 48:10). There’s a war on today, a holy war. I must be on the front lines. There are so many Marxists, so many Masons, so many Satanists and assorted others! So many possessed, anarchists and seduced ones! I see what awaits us, and it’s painful for me. The bitter taste of human pain is in my mouth.
 
The spirit of lukewarmness reigns. There’s no manliness at all! We’ve been spoiled for good! How does God still tolerate us? Today’s generation is the generation of indifference. There are no warriors The majority are fit only for parades.
 
Godlessness and blasphemy are allowed to appear on television. And the Church is silent and doesn’t excommunicate the blasphemers. And they need to be excommunicated. What are they waiting for? Let’s not wait for someone else to pull the snake out from its hole so that we can live in peace.
 
They’re silent out of indifference. What’s bad is that even people who’ve got something inside have begun to grow cool, saying: “Can I really do anything to change the situation?” We have to witness our faith with boldness, because if we continue to be silent we’ll have to answer in the end. In these difficult days each must do what’s in their power. And leave what’s out of their power to the will of God. In this way our conscience will be clear.
 
If we don’t resist, then our ancestors will arise from their graves. They suffered so much for the Fatherland, and we? What are we doing for it?.. If Christians don’t begin to witness their faith, to resist evil, then the destroyers will become even more insolent. But today’s Christians are no warriors. If the Church keeps silent, to avoid conflict with the government, if the metropolitans are silent, if the monks hold their peace, then who will speak up?
 
Give thanks to God for everything. Try to be manly. Pull yourself together a bit. Do you know what Christians are suffering in other countries? There are such difficulties in Russia! But here many exhibit indifference. There’s not enough disposition to kindness, love of devotion.
 
You see, if we don’t begin to make war against evil, to expose those who tempt believers, then the evil will grow larger. If we throw aside fear then the faithful will be emboldened a bit. And those who wage war against the Church will have a harder time.
 
In the past our nation lived spiritually, so God blessed her, and the saints helped us in miraculous fashion. And we were victorious against our enemies, who always outnumbered us. Today we continue to call ourselves Orthodox Christians, but we don’t live Orthodox lives.
 
A lukewarm clergy lulls the people to sleep, leaves them in their former condition so they won’t be upset. “Look”, they say. “By all means don’t say that there’ll be a war, or the Second Coming, that one must prepare oneself for death. We must not make people alarmed!”
 
And others speak with a false kindness, saying: “We mustn’t expose heretics and their delusions, so as to show our love for them.” Today’s people are water-soluble. There’s no leaven in them.
 
If I avoid upsetting myself to protect my fleshly comfort then I’m indifferent to holiness! Spiritual meekness is one thing, and softness and indifference are quite another. Some say: “I’m a Christian and therefore I have to be joyful and calm.” But they’re not Christian. They’re simply indifferent. And their joy is only a worldly joy.
 
He in whom these worldly seeds are present is no spiritual person. A spiritual person consists of nothing but pain. In other words, he’s in pain at what’s going on, he’s in pain for people’s condition. And divine comfort is bestowed upon him for his pain.
 
Elder Paisios was a gentle ascetic who lived out his monastic life, until he became ill, on Mount Athos. After a few days of suffering following surgery, he gave up his spirit on July 12, 1994.
 
Source
 
Pentecost / ጰራቅሊጦስ Reading

__

 

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

በዓለ መንፈስ ቅዱስ / ጰራቅሊጦስ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 22, 2013

Paraclete22አጋጣሚ? የእንግሊዙ ቴሌግራፍ ስለ ደብረ ዳሞ ይህን አቀረብገለባገለባውሲኤን ኤንእንኳን ያልተለምዶው ስለ ገዳማቶቻችን የሚለው አለ። ይህን ጽሑፍ በማቀርብበት በዚህ ሰዓት፡ ምስሉ ላይ የገባችው እርግብበመስኮቴ ብቅ ብላ ቁልጭ ቁልጭ ትልብኝ ጀመር። ቀስ ብዬ ፎቶ ካነሳኋት በኋላ፡ ጥሬ ስንዴ ለማምጣት ወደ መዓድ ቤት ገባሁ። ከፊሉን ስንዴ ለንፍሮ፣ ከፊሉን ደግሞ ለርግቧ ወስጄ ጣል ጣል ማድረግ ስጀምር እርግቧ ተንስታ በረረች። የበረረችበት አቅጣጫ ወደ ደቡብ ምስራቅ (የኢትዮጵያ አቅጣጫ) እንዲሁም ከኔ አንድ ኪሎሜትር ያህል እርቃ ልክ በዚያው አቅጣጫ ወደምትገኘው የመንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያንነው። ነገ ተነስተህ ወደዚያ መሄድ አለብህበማለት እርግቧ ምልክት እየሰጠችኝ መሆኑ ታወቀኝ። ወገኖቼን ይወደ ቤተክርስቲያኗ አመራለሁ፡ ከተቀቀለውም ስንዴበአብ፣ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እንቀምሳለን ማልተ ነውስብሐት ለእግዚአብሔር!

በዓለ መንፈስ ቅዱስ / ጰራቅሊጦስ

ይህች ታላቅ ዕለት ከቅድስት ሥላሴ አንዱ አካል የሆነው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ለቅዱሳን ሐዋርያት፣ ለቅዱሳን አርድእትና ለቅዱሳት ሴቶች የተገለጠባት ዕለት ናት፡፡ እነዚህ ሁሉ በጸሎት ተግተው በሚጸልዩበት ወራት መንፈስ ቅዱስ በተከፋፈሉ የእሳት ልሳን አምሳል የወረደበት ቅዱስ ቀን ነው፡፡

አስቀድሞ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳን ሐዋርያት ደብረ ዘይት በተባለ ታላቅ ተራራ ላይ ሳሉ እንዲህ ብሎ አስተምሯቸው ነበር “ኀይልን ከላይ ከአርያም እስክልክላችሁ ድረስ በኢየሩሳሌም በጸሎት ቆዩ፡፡”/ሉቃ 2436/ መቶ ሃያው ቤተሰብም በኢየሩሳሌም ሀገር በምትገኝ በቤተ መቅደስ በአንድነት ሆነው በጸሎት በመትጋት ቆዩ፡፡ ልጆችዬ መቶ ሃያው ቤተሰብ የሚባሉት 12ቱ ሐዋርያት፣ 72ቱ አርድእት/አገልጋዮች/ እና 36ቱ ቅዱሳን አንስት/ሴቶች/ ናቸው፡፡

ከዕርገት በኋላ በአሥረኛው ቀን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሐዋርያት ወዳሉበት፣ በጸሎትና በምሥጋና ወደ ሚተጉበት ሥፍራ በእሳት አምሳል /ምሳሌ/ ወርዶ በእያንዳንዳቸው ላይ ተቀመጠባቸው፡፡ ይሄንንም ሁኔታ ተከትሎ ምስጢር ተገለጠላቸው፣ ይፈሩ የነበሩት ሐዋርያትም ወንጌልን ለማስተማር ደፋሮች ሆኑ፣ በተለያየ ቋንቋዎች እንዲናገሩ እውቀት ተሰጣቸው፤ የእግዚአብሔርንም ጸጋ ተቀበሉ፡፡ ይህንን ታላቅ ኀይል እና ሰማያዊ ስጦታን የሰጣቸውን እግዚአብሔርን በታላቅ ዝማሬና እልልታ አመሰገኑት፡፡

በዓለ ሃምሳ የሚባለውን የአይሁድን በዓል ለማክበር ከተለያዩ ሀገራት የመጡ በጊዜው የነበሩ ቁጥራቸው በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የሐዋርያቱን ታላቅ የዝማሬና የእልልታ ድምፅ ሰሙ፡፡ ከመቶ ሃያው ቤተሰብ መካከል አንዱ የሆነው ቅዱስ ጴጥሮስ የተሰበሰቡት ሁሉም እንዲሰሙት ድምፁን ከፍ አድርጎ ቃለ እግዚአብሔርን እንዲህ ብሎ አስተማራቸው፡፡ “እናንተ የእስራኤል ሰዎች ሆይ እኛን የሰው ልጆችን ለማዳን እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ወደ ምድር መጥቶ ከክፉ ሥራ ተመለሱ፣ ኀጢአትን አታድርጉ፣ በቅድስና ኑሩ፣ ወደ እኔም ተመለሱ ቢላችሁ፤ እናንተ ግን ምንም በደል ሳይኖርበት ገረፋችሁት፣ አንገላታችሁት፣ በመስቀል ላይም ሰቀላችሁት፡፡ እርሱ ግን እግዚአብሔር ነውና ሞትን ድል አድርጎ ተነሣ፡፡ እርሱ ግን አሁንም ይቅር ባይ ነውና ከኀጢአታችሁ ተመለሱ ንስሐም ግቡ ፡፡” በማለት አስተማራቸው፡፡

የተሰበሰቡት ሰዎች ሁሉ ተገረሙ፡፡ ምክንያቱም ሐዋርያት በፊት የሚያውቁት አንድ ቋንቋ ብቻ ነበረ፡፡ በዚህ ሰዓት ግን ሰባ ሁለት ቋንቋን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ገልጦላቸው ለሁሉም በየቋንቋቸው አስተማሯቸው፡፡ ይህንንም ድንቅ ተአምር ከተመለከቱት ብዙዎች እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡ ወደ ሐዋርያትም ቀርበው “አባቶቻችን እናንተ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ናችሁና ምከሩን፡፡ እንደ እናንተ የእግዚአብሔር ልጆች እንድንሆንና በቅድስና እንድንኖር ምን እናድርግ?”በማለት ጠየቁ፡ በዚያች ቀን ቁጥራቸው ሦስት ሺ ያህል ሰዎች በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት አምነው ክርስቲያን ለመሆን ቀረቡ፡፡

ቅዱስ ጴጥሮስም እንዲህ አላቸው፡፡ “እነሆ ሁላችሁም ንስሐ ግቡ፡፡ በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት አምናችሁ ተጠመቁ፡፡” አላቸው በዚያው ዕለትም ሦስት ሺ ሰዎች ወደ ሐዋርያት በመቅረብ ኀጢአታቸውን ተናገሩ፤ ሐዋርያትም እግዚአብሔር ይፍታችሁ እያሉ ልጅነትን የሚያሰጣቸውን ጥምቀት አጠመቁዋቸው፡፡

ከዚያ ቀን ጀምሮም በየዓመቱ ይህችን ታላቅ የቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን የምትባለውን በዓለ ጰራቅሊጦስን ክርስቲያኖች በታላቅ ደስታና ምሥጋና እናከብራታለን፡፡ እናንተም ልጆችዬ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት በቤተ ክርስቲያን ተገኝታችሁ ቅዳሴ በማስቀደስ፣ መዝሙር በመዘመር እና በመጸለይ ይህችን ታላቅ በዓል ልታከብሯት ይገባል፡፡

የእግዚአብሔር አብ ጸጋ የእግዚአብሔር ወልድ ቸርነት የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አንድነት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን፡፡

ምንጭ

_

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: