Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ጥንባሆ’

ሐረሪዎች የኦሮሞዎች የጥላቻ እና የዘረኝነት ጥቃት ሰለባ እንደሆኑ ለአውሮፓውያኑ አሳወቁ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on June 15, 2020

አውሮፓውያኑ ኦሮሞዎችን የፈጠሯቸውና ያዘጋጇቸው እነርሱ እራሳቸው በመላው ዓለም ሲፈጽሙት የነበረውን ዓይነት ጭፍጨፋና የዘር ዕልቂት እንዲፈጽሙላቸው ነው። ስጋዊ የጥፋት ልጆች መሆናቸውን እኮ እነ አፄ ዮሐንስ በደንብ ያውቁት ነበር ፣ ሞኙ የእኛ ትውልድ ነው እንጅ ይህን ያልተገነዘበው። በተመሳሳይ መልክ ስጋዊ የሆኑት ነጮቹም ይህን በሚገባ ነው የሚያውቁት፤ ለዚህም ነው እነ ዮሃን ክራፕፍ ኦሮሞ ብሎ የጠራቸውን ወራሪዎች “ለማሰልጠን” የተነሳሳው።

ክርስቲያን ኢትዮጵያ ማየት ያለባትን ሙሉውን ቪዲዮ በሌላ ጊዜ እናቀርበዋለን።

በዚህ ቁራጭ ቪዲዮ ግን “ሪት እና ሶዚት” የተባሉትን ሁለት እህትማማቾች ታሪክ እንመለከታለን።

እህትማማቾቹ ከሐረሪ ወይም ጌይኡሱእ ነገድ ናቸው የሚኖሩትም በአረብ ኤሚራትስ ነው (ልብ በሉ፦ እንደ ሌሎቹ አልተሸፋፈኑም)። ኦሪት እና ሶዚት አዲስ አበባ “ተንደላቀው” ከሚኖሩት ቤተሰባቸው

ጋር ሆነው የቡና የውጭ ንግድ ያካሂዳሉ። ደንበኞቻቸውም የአረብ ሃገራት ናቸው።

ኦሪት እና ሶዚት ወደ ትውልድ ከተማቸው ወደ ሐረር በሚመላለሱበት ወቅት ግን ላለፉት ሁለት ዓመታት በሐረር እየተካሄደ ያለው የኦሮሞዎች የዘር ማጥፋት ዘመቻ በጣም እያሳሰባቸው ነው። ሐረሪዎች በገዛ ከተማቸው አናሳ ነገድ እየሆኑ እና በወራሪዎቹ ኦሮሞዎች ከሐረር እየተፈናቀሉና እየተባረሩ ነው።

ይህን በጣም ሙያዊ የሆነ እና በጥበብ የተሠራ ጥናታዊ ፊልም ሰሞኑን ያቀረበው “አርቴ”(ARTE) “Association Relative à la Télévision Européenne” የተሰኘው የጀርመንፈረንሳይ የቴሌቪዥን ጣቢያ ነው። GEO-Reportage“ በተሰኘው ተወዳጅ ተከታታይ ሪፖርቱ “ኢትዮጵያ፤ የቡና መገኛ” የሚለውን ርዕስ ይዞ ቀርቧል። ዋናው ትኩረት “ለቡና፣ ጥንባሆና ጫት”የተሰጠ መስሎ ቢታየንም ፥ በውስጠኛውና በጥልቁ ንዑስ አእምሯችን እንዲቀረጽ የተደረገው ምስል ግን “የሃይማኖት እና የዘር ግጭትን” የተመለከተ ነው። ካሜራው በተቻለ መጠን ከእስልምና ጋር የተያያዙትን (ቡና፣ ጥንባሆ፣ ጫት፣ መስጊድና አረብኛ) ነገሮች ብቻ መርጦ ለማሳየት ነው የፈለገው።

ሐረር” ያለምክኒያት አልተመረጠችም፤ ምክኒያቱም ከግራኝ ወረራ ጋር በተያያዘ ከአምስት መቶ ዓመታት በፊት በመንፈሳዊ ኢትዮጵያ ላይ የጀመረው ጂሃድ ላለፉት 150 ዓመታት “በሰላማዊ” መልክ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የተደረገው ከሐረር ከተማ ነው። አፄ ኃይለ ሥላሴንም የመረጧቸው ሐረሬ ሰለነበሩ ነው። ተከታዩ ቪዲዮ ይህን ሃሳብ ያጠናክረዋል።

ባጠቃላይ የቪዲዮው ስውር መልዕክት ፤ “ዕቅዳችን እየሠራ ነው፤ ኢትዮጵያን አገኘናት!” የሚለው ነው።

_________________________________

Posted in Ethiopia, Infos, Life | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ኢቫንካ ትራምፕ የኢትዮጵያ ጉብኝቷን በቡና ስነ ሥርዓት / 666 መስዋዕት ጀመረች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 14, 2019

ለአውሬው ፍየል መሆኑ ነው፤ ዋው! የቡናው ቤት ውስጥ ካልዲን እና ፍየሉን ለማስተዋወቅ ተሞክሯል። “ታሪኩ እንዲህ ይላል፦ አንድ ካልዲ የሚባል የፍየል እረኛ የሚጠብቃቸው ፍየሎች የሆነ ዛፍ ፍሬን በልተው ያልተገባ ባህርይ ማሳየት ጀመሩ”። የምል ጽሑፍ ግርግዳው ላይ ይነበባል።

አንዷ ፍየል ብቻ መስላኝ? ለማንኛውም በጉ ከፍየሎች የሚለይበት ዘመን ላይ ደርሰናልና ህዝበ ክርስቲያኑን አድነዝዞ ለእነ ዶ/ር አህመድ እንዲሰግድ ያደረገውን ቡናን አንጠጣ፤ ግድ የለም፤ ለፍየሎች እንተውላቸው።

ድርሳነ ጽዮን ማርያም” :- ተአምር 1 ላይ የተጻፈው በሙሉ ይህ ነው:-

ሰማያዊት የሆነች የእናታችን የጽዮን ተአምር ይህ ነው : ጸሎቷና በረከቷ ህዝበ ክርስቲያን ከምንሆን ከሁላችን ጋር ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን::

ህዝበ ክርስቲያን ሆይ ልንገራቹ ሁላችሁም ስሙ የተጻፈ መጽሃፍ ሁሉ እኛ ልንመክርበት ተጽፏል እንዳለ ጳውሎስ ሮሜ 13:4 :ከአዳም ልጆች ወገን ሴሩህ የሚባል ሰው ነበር ለሴሩህ ስሙ ብኑ የሚባል ልጅ ተወልዶ በህጻንነቱ ሞተበት በብኑ ስም በተቀረጸው ጣኦት መመለክ ተጀምሯል በመቃብሩም ላይ ሰይጣን የሚወዳት ከሱስ የተነሳ ጾምን የምታሽር የከፋች ዕጽ በቀለች ይህውም በስንዴ መካከል እንክርዳድ የዘራ ጠላት ዲያብሎስ ካለችበት አምጥቶ ዘራት ማቴ ፲፫: ፳፰::

በብኑ ስም ቡን ተብላለች ቡና ማለት ነው: ማክሰኞ ከተፈጠሩት ዕፅዋት መልካምና ክፉ አሉ መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ክፉም ዛፍ ክፉ ፍሬ ያፈራል እንዳለ ማቴ ፯:፲፪

እስማኤላውያን የሚያመልኳቸው የጣኦታቸው መስዋዕት ሆነች የተንባላት አለቃ የሚሆን እስከ መሃመድም ትደርሳለች ተንባላትም ያለ እርሷ ሌላ አይሰውም ተንባላት ማለት የመሃመድ ተከታዮች ናቸው: ጣኦት የሚያመልኩ ባለዛሮችም ይህችኑ ይሰዋሉ የቡና ሱስ ያዘን ብለው ጾምን የሚሽሩ በበዓል የሚወቅጡ ራሳችንን አመመን በማለት በውስጣቸው ላደረ ለሱስ ጋኔን የሚገብሩ ብዙዎች ናቸው ወደ ቅዳሴም እንዳይሄዱ በጥዋት እሷን እየጠጡ ይህችም ዕጽ ክፉ ሁና ሰውን ስታሳስት ትኖራለች::

ተአምር ፪፦

ሌላም የሚያስረዳና ልቡናን የሚያጸና ስሙ ልንገራችሁ የተንባላት መምህር የነበረ ስሙ መሀመድ የሚባል አንድ ሰው ከመካዱ የተነሳ ከአጋንንት ጋር ይውላል ከዕለታት አንድ ቀን ሲሰግድ በልጅነቱ ያመው የነበረው የራስ ምታት በሽታ ይነሳበታል በዚህ በሽታ እየተሰቃየ ሳለ ከዕለታት በአንዱ ቀን ዲያቢሎስ በተንኮሉ ያስተው ዘንድ ወደ እርሱ መጥቶ ወዳጄ መሀመድ ሆይ ምን ሆንክ ይለዋል የራስ ምታት በሽታ የሆነበት እርሱ ዲያቢሎስ ነው፡፡

መሀመድ መልሶ ከፍተኛ የራስ ምታት ነበረብኝ በዚህ ደዌ እጨነቃለው ይለዋል ዲያቢሎስም የራስ ምታት መድሀኒት ብነግርህ ታደርገዋለህን የልቦናዬን ፈቃድ ትፈጽመሀልን? ይለዋል መሀመድም ካዳንከኝ አዎ ያልከኝን ሁሉ አደርገዋለሁ ብሎ የመልስለታል፡፡

ከዚህ በኋላ ዲያቢሎስ

  • ዕጸ ጌት የተባለች ጫትን፣

  • ዕፀ ኩስራ የተባለችውን ቡናንና

  • ዕፀ ስጥራጢስ የተባለጭውን ጥንባሆን

እነዚህን ሶስቱን ዕፅዋት ከአሉበት አምጥቶ መድሀኒት ናቸው ብሎ ይሰጠዋል፡፡ይህንንም ቡና ከጠጣህ ፈጥነህ ትድናለህ ለልጅ ልጅ ዘመን በመካ መዲና መስዋዕት አድርገህ ሰዋ ብሎ ቆልቶ ያሰየዋል፡፡

መሀመድም ብረት ምጣድ አግሎ ያሳየዋል እንደመልኬ ከሰል አስመስልህ አጥቁረህ ትቆላለህ ይለዋል እንዳለው አድርጎ ከሰል አስመስሎ ይቆላል ሁል ጊዜም እንደዚሁ ካላከሰልክ መድሀኒት አይሆንህም ይለዋል ራስ ምታቱም ለጊዜው የተወው ይመስለዋል ኋላ ግን ሰዓት እየጠበቀ ይነሳበታል።

በመሓመድ ሥርዓትና ሕግ የሚጓዙ አወል ፤ ቶና ፤ በረካ የሚባሉ ሦስት ሰዎች ለንግድ የመጡ መስለው ከአምስት ተከታዬቻቸው ጋር እነዚህን ዕፅዋት ይዘው ይመጣሉ እነዚህም «ጫት፤ ቡና ፤ ጥንባሆ» ናቸው አህዛብ ለሰይጣን የሚያቀርቡዋቸው የጣኦት መስዋዕት ናቸው። የእግዚአብሔር መስዋእት ግን፤ 

  • ስንዴ
  • ዘቢብ
  • እጣን

ናቸው።

አርብ እና እሮብ ብዙ ሰዎችን እያዛጋ ከቅዳሴ የሚያስቀረው እኮ ቡና ነው። በፆም ሰዓት ብዙ ሰዎችን በራስ ምታት የሚቀውር ቡና ነው። ቡና ካልጠጡ ደስታቸውን የሚያጡ፣ የሚነጫነጩ፣ የሚሳደቡ፣ የሚደብራቸው ቤቱ ይቁጠራቸው። ቡና ቁጭ ተብሎ የሰው ሥጋ በሃሜት የሚበላበት ወሬ እንቶ ፈንቶ የሚሰለቅበት ነው። ሥራ ፈቶች እስከ 3ኛ የሚያንቃርሩት ቡና ቤተክርስትያን እስከምታወግዘው መጠበቅ የለብንም። እግዚአብሔር የሰጠንን አእምሮ መጠቀም ብቻ በቂ ነው።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

___________________

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የነነዌ ጾም መልዕክት | ዲያቢሎስ ጫትን፣ ቡናንና ጥንባሆን ለመሀመድ ሰጠው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 28, 2018

ቸሩ እግዚአብሔር፡ አምላኬ ሆይ፡ ለዚህ ዕለት ብቻ “ዮናስ” እንድሆን ፍቀድልኝ።

የቡና ጉዳይ ለብዙ ዓመታት ሲያሳስበኝ የነበረ ጉዳይ ነው። እስካሁንም ስለ “ድርሳነ ጽዮን” ምንም ዓይነት እውቀት አልነበረኝም፡ ይህ ድንቅ ድርሳን፡ ሳስብባቸው ከነበሩት ነገሮች ጋር ሙሉ በሙሉ ይጣጣማል፤ የሚገርም ነው። አሁን 100% እርግጠኛ ነኝ፡ መንፈስ ቅዱስ የተሞላባቸው ክርስቲያኖች፤ እንኳን ጫት፣ ሲጋራና ሺሻ (አጋንንት መሳብ ነው)፤ ቡና እንኳን መጠጣት የለብንም።

በሚገባ ተምረን ቢሆን ኖሮ፡ እነዚህን ሱስ አስያዥ ነገሮች በመላው ዓለም ለማሰራጨት የበቁት መሀመዳውያኑ አረቦችና ቱርኮች መሆናቸው ብቻ በቂ ምክንያት ሊሆነን ይገባ ነበር።

ከፋ” የሚለው ቃልም “ኩፋር / ካፊር” ከሚለው የአረብኛ ቃል የመጣ ነው። እነዚህ ክፉ ሰዎች በዲያብሎስ አባታቸው እየተመሩ ወደ ከፋ አምጥተው ተክለውት ይሆን?

ድርሳነ ጽዮን ማርያም” :- ተአምር 1 ላይ የተጻፈው እንዲህ ይላል:-

ሰማያዊት የሆነች የእናታችን የጽዮን ተአምር ይህ ነው : ጸሎቷና በረከቷ ህዝበ ክርስቲያን ከምንሆን ከሁላችን ጋር ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን::

ህዝበ ክርስቲያን ሆይ ልንገራቹ ሁላችሁም ስሙ የተጻፈ መጽሃፍ ሁሉ እኛ ልንመክርበት ተጽፏል እንዳለ ጳውሎስ ሮሜ 13:4 : ከአዳም ልጆች ወገን ሴሩህ የሚባል ሰው ነበር ለሴሩህ ስሙ ብኑ የሚባል ልጅ ተወልዶ በህጻንነቱ ሞተበት በብኑ ስም በተቀረጸው ጣኦት መመለክ ተጀምሯል በመቃብሩም ላይ ሰይጣን የሚወዳት ከሱስ የተነሳ ጾምን የምታሽር የከፋች ዕጽ በቀለች ይህውም በስንዴ መካከል እንክርዳድ የዘራ ጠላት ዲያብሎስ ካለችበት አምጥቶ ዘራት ማቴ 13: 28::

ብኑ ስም ቡን ተብላለች ቡና ማለት ነው: ማክሰኞ ከተፈጠሩት ዕፅዋት መልካምና ክፉ አሉ መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ክፉም ዛፍ ክፉ ፍሬ ያፈራል እንዳለ ማቴ 7:12

እስማኤላውያን የሚያመልኳቸው የጣኦታቸው መስዋዕት ሆነች የተንባላት አለቃ የሚሆን እስከ መሃመድም ትደርሳለች ተንባላትም ያለ እርሷ ሌላ አይሰውም ተንባላት ማለት የመሃመድ ተከታዮች ናቸው: ጣኦት የሚያመልኩ ባለዛሮችም ይህችኑ ይሰዋሉ የቡና ሱስ ያዘን ብለው ጾምን የሚሽሩ በበዓል የሚወቅጡ ራሳችንን አመመን በማለት በውስጣቸው ላደረ ለሱስ ጋኔን የሚገብሩ ብዙዎች ናቸው ወደ ቅዳሴም እንዳይሄዱ በጥዋት እሷን እየጠጡ ይህችም ዕጽ ክፉ ሁና ሰውን ስታሳስት ትኖራለች

በሰለሞን ምሳሌያት ትርጉም 13:10 ክፉን ሰው ወንድሜ እንደዚህ ያለ ነገር ለምን ታደርጋለህ ቢሉት እንደፈለግሁ ልሁን ለራስህ እወቅ እያለ ይነቅፋል ይላል እኛስ መንቀፍ ትተን ከቶ ብንተው ምን ይጎዳናል: “ትርጓሜ ወንጌልም የማያሰክር ቡን አልጠጣም መንፈስቅዱስ አድሮበታል እና ይላል አንድምታ ሉቃ 1:15 እኛም በአርባ ቀን መንፈስቅዱስን ተቀብለን የለምን ? የመንፈስቅዱስ ማደርያ አካላችን የሱስ ጋኔን መደርያ ለምን ይሆናል::„

ተአምር 2

ሌላም የሚያስረዳና ልቡናን የሚያጸና ስሙ ልንገራችሁ የተንባላት መምህር የነበረ ስሙ መሀመድ የሚባል አንድ ሰው ከመካዱ የተነሳ ከአጋንንት ጋር ይውላል ከዕለታት አንድ ቀን ሲሰግድ በልጅነቱ ያመው የነበረው የራስ ምታት በሽታ ይነሳበታል በዚህ በሽታ እየተሰቃየ ሳለ ከዕለታት በአንዱ ቀን ዲያቢሎስ በተንኮሉ ያስተው ዘንድ ወደ እርሱ መጥቶ ወዳጄ መሀመድ ሆይ ምን ሆንክ ይለዋል የራስ ምታት በሽታ የሆነበት እርሱ ዲያቢሎስ ነው፡፡

መሀመድ መልሶ ከፍተኛ የራስ ምታት ነበረብኝ በዚህ ደዌ እጨነቃለው ይለዋል ዲያቢሎስም የራስ ምታት መድሀኒት ብነግርህ ታደርገዋለህን የልቦናዬን ፈቃድ ትፈጽመሀልን? ይለዋል መሀመድም ካዳንከኝ አዎ ያልከኝን ሁሉ አደርገዋለሁ ብሎ የመልስለታል፡፡

ከዚህ በኋላ ዲያቢሎስ

  • ዕጸ ጌት የተባለች ጫትን፣

  • ዕፀ ኩስራ የተባለችውን ቡናንና

  • ዕፀ ስጥራጢስ የተባለጭውን ጥንባሆ

እነዚህን ሶስቱን ዕፅዋት ከአሉበት አምጥቶ መድሀኒት ናቸው ብሎ ይሰጠዋል፡፡ይህንንም ቡና ከጠጣህ ፈጥነህ ትድናለህ ለልጅ ልጅ ዘመን በመካ መዲና መስዋዕት አድርገህ ሰዋ ብሎ ቆልቶ ያሰየዋል፡፡

መሀመድም ብረት ምጣድ አግሎ ያሳየዋል እንደመልኬ ከሰል አስመስልህ አጥቁረህ ትቆላለህ ይለዋል እንዳለው አድርጎ ከሰል አስመስሎ ይቆላል ሁል ጊዜም እንደዚሁ ካላከሰልክ መድሀኒት አይሆንህም ይለዋል ራስ ምታቱም ለጊዜው የተወው ይመስለዋል ኋላ ግን ሰዓት እየጠበቀ ይነሳበታል።”

አይን አይደል፡ ምን ዓይነት ከባድ ወጥመድ ውስጥ ኢትዮጵያውያን እንደገባን?!

ቡና ኢትዮጵያ ነው የተገኘው በማለት ብሔራዊ መጠጥ እንዲሆን በማድረግ ዲያብሎስ ኢትዮጵያን ከጽዮን ለማራቅ መሞከሩ ይሆን? ልክ፡ የመጀመሪያዋ ሴት “ሉሲ” ናት በማለት ሙዚየም ሳይቀር እንዲሠራና የዓለማቱ መሪዎች ሁሉ እየመጡ እንዲሳለሟት እንደተደረገው? የሚገርም ነው!

______

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: