Posts Tagged ‘ጤንነት’
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 23, 2020
የደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ወአቡነ ሃብተማርያም የማእጠንት ፀሎት በተወሰኑ የቨርጂንያ መንደሮችና ጎዳናዎች
[የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ ፰፤]
፩ ሰባተኛውንም ማኅተም በፈታ ጊዜ እኵል ሰዓት የሚያህል ዝምታ በሰማይ ሆነ።
፪ በእግዚአብሔርም ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ፥ ሰባትም መለከት ተሰጣቸው።
፫ ሌላም መልአክ መጣና የወርቅ ጥና ይዞ በመሰዊያው አጠገብ ቆመ፤ በዙፋኑም ፊት ባለው በወርቅ መሰዊያ ላይ ለቅዱሳን ሁሉ ጸሎት እንዲጨምረው ብዙ ዕጣን ተሰጠው።
፬ የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ።
ሌላ የሚገርመው ነገር፤ ልክ እዚህ አካባቢ ነበር ባለፈው ጊዜ የሚከተለው የተከሰተው፦
_______________________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith, Health | Tagged: መንፈሳዊ ሕይወት, ቃሌ, ቨርጂኒያ, አሜሪካ, አቡነ ሀብተ ማርያም, አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ, እስትንፋስ, እጣን እና ከርቤ, ዋሽንግተን, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን, ገዳም, ጋኔን, ጤንነት, Ethiopia, Frankincense & Myrrh, Holy Water, Water | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 23, 2020
[የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፳፥፲፮]
“እንዲሁ ኋለኞች ፊተኞች፥ ፊተኞችም ኋለኞች ይሆናሉ፤ የተጠሩ ብዙዎች፥ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸውና።”
ይህን ሳይ የሚሰማኝ፤ “እግዚአብሔር እኛ ኢትዮጵያውያንን በመላው ዓለም በስደትም ሆነ በሌላ አጋጣሚ ከአገራችን አውጥቶ የሚልከን በርገር እየበላን በከንቱ እንድናውደለድል ሳይሆን እንደዚህ እጣኑን እያጨስን መንፈሳዊ ውጊያውን እንድንመራለት፣ ከጠፉት ጋር አብረን እንድንጠፋ ሳይሆን፣ ሁሉም እንዲድን መድኃኒቱን እንድናሳይ ነው።” የሚለው ነው። በእውነት ነው የምለው፤ እኛ ኢትዮጵያውያን በከንቱ ሌላውን ለመምሰል ብንታገልም ምናልባት 90% መንፈሳውያን ሰዎች ነን።
እንግዲህ ያውልሽ አሜሪካ፤ ግብጻውያን አውሮፕላን አብርረው ከሰማይ–ጠቀስ ፎቆችሽ ጋር በማላተም ሦስት ሺህ ዜጎችሽን ገደሉብሽ፣ ፕሬዝደንትሽ ለጉብኝት ወደ ግብጽ ሲመጡ በንቀት ጫማቸውን ወረወሩባቸው…ዛሬ የከዳሻቸው ኢትዮጵያውያን የተዋሕዶ ልጆች ግን መቅሰፍቱ ሁሉ ከምድርሽ እንዲርቅ ክቡር እጣኑን ከደመናው ጋር አዋሐዱልሽ። ይህን ውለታ አትርሺ፤ አሜሪካ!
የፃድቁ አባታችን አቡነ ሃብተማርያም ቃል ኪዳናቸው ይጠብቀን የመጣውን መቅሰፍት ከአገራቸን ኢትዬጵያና ከመላው ዓለም ይሰውርልን!
መምህር ዘመድኩን እንዳካፈለን፦
• መፍትሄው እግዚአብሔር ብቻ ነው።
ጭንቅ ውስጥ በገባችው አሜሪካ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየአደባባዩ፣ በየመንደሩ፣ እየዞረች የጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያምን ዕጣን እንድታጥን ተጠይቃ ይኸው ቃሏን አክብራ በጻድቁ አቡነ ኃብተ ማርያም ጸሎት ምድሪቱን እያጠነች ነው።
ዛሬ መጋቢት ፲፫ / ፪ሺ፲፪ /13/2012 ዓ.ም (Mar.22/2020)
በአሜሪካን ሀገር በሀገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ 5:00 PM ላይ በኸረንደን ቨርጂንያ 2472 Centreville Rd.Herndon, VA 20171 የደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ወአቡነ ሀብተማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ካህናቱ የጻድቁ የአቡነ ሀብተ ማርያም ሥዕላቸው ተይዞ
•በኸረንደን፣
•በረስተን፣
•በቻንትሊን፣
•በእስትርሊንግና በሌሎችም ከተሞች የሚገኙ አደባባዮችና አውራ ጎዳናዎች በማጠን ላይ ይገኛሉ።
• ለዚሁ የአሜሪካን ከተሞችና መንደሮች የማዕጠንት አገልግሎት
• መልአከ ሰላም ቀሲስ ሰሎሞን
• መጋቤ ካህናት መ/ር ቀሲስ ዮናስ ፍቅረ
• ሊቀ ስዩማን መ/ር ቀሲስ ኢዮብ ደመቀ
• ሊቀ ልሳናት መ/ር ቀሲስ ጌቱ ተገኑ
• ሊቀ ማዕምራን መ/ር ዮሐንስ ለማ
• ሊቀ ትጉሀን ዲ/ን አብርሐም ቶማስ
• ሊቀ ዲያቆን ገረመው ተዘጋጅተው አገልግሎቱን ጀምረዋል።
አሜሪካ ደንግጣለች። ቤተ ጸሎቶች በሙሉ ተዘግተዋል። የመኪና መንገድ አውራ ጎዳናዎች ሁሉ ጭር ብለዋል። ነገር ግን በእኒህ ሞት ባጠላባቸው የአሜሪካ ጎዳናዎች ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናት አባቶቻችን ጸሎት እንዲያደርጉ የአሜሪካ መንግሥት ፈቅዶላቸዋል። በእውነት ከዚህ ውጪ ሌላ አማራጭ የለም። ይሄ ምልክት ነው። ወደድንም ጠላንም መጪው ዘመን የኦርቶዶክስ ነው። ኦርቶዶክሳዊነት የዓለሙ ሁሉ ሃይማኖት ይሆናል። ሰዎች ሁሉ ወደ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ እምነት ይተምማሉ። የኢትዮጵያ ሃይማኖት የዓለም ሃይማኖት ይሆናል የሚባለው የአበው የትንቢት ቃል በቅርቡ ፍጻሜውን ያገኛል።
ከኢትዮጵያ ውጪ ብቸኛው የጻድቁ አቡነ ሃብተ ማርያም ታቦት የሚገኘውም እዚሁ ቦታ ነው። በቦታውም ብዙ ህሙማን እየተፈወሱ መካኖች መወልዳቸው ብዙዎችን ሲያስደንቅ መኖሩም ተነግሯል። በእውነት “መንክር እግዚአብሔር በላዕለ ቅዱሳኒሁ” እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው፤ የእስራኤል አምላክ እርሱ ኃይልን ብርታትንም ለሕዝቡ ይሰጣል “(መዝሙረ ዳዊት 68:35፤)
በጻድቁ ዜና ገድል (ገድለ አቡነ ሀብተማርያም ገጽ.117) ላይ ተጽፎና ተመዝግቦ እንደምናገኘው ልዑል እግዚአብሔር ለጻድቁ በሰጣቸው ቃል ኪዳን መሰረት ስማቸው፣ በተጠራበት፣ ማዕጠንታቸው በታጠነበት፣ ዜና ገድላቸው በተነበበትና ባለበት፣ ጠበላቸው በተረጨበት ሥፍራ ፭ቱ መቅሰፍታት ማለትም :-
፩ኛ.መብረቅ
፪ኛ.ቸነፈር
፫ኛ.የረኀብ ጦር
፬ኛ.ወረርሽኝና
፭ኛ.ሰደድ እሳትና የመሳሰሉት ቦታ የላቸውም። ዜና ገድላቸው እንደሚነግረን በአንድ ወቅት ቅዱስ አባታችን ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ልጆቻቸው በእነዚህ ፭ቱ መቅሰፍታት እንዳይጠቁና እንዳይጎዱ ጻድቁ አቡነ ሀብተማርያምን በቃል ኪዳናቸው ልጆቻቸውን እንዲጠብቁላቸው ሲማጸኑዋቸው የጻድቁ የአቡነ ሀብተማርያም መልስ የነበረው “ወዳጄ ተክለሃይማኖት ሆይ፤ በእኔ ስም ልጆችህና ወዳጆችህ በቃል ኪዳኔ የሚድኑ ከሆነ ይሁን ብለው ቃል እንደገቡላቸው ተመዝግቧል። ይህ ቃል ኪዳን ደግሞ ዘመን ተሻጋሪና ጊዜ የማይሽረው ነው። በእውነት ያለ ሀሰት። እንጠቀምበት።
በኢትዮጵያም በትናንትናው ዕለት የቃሌ አቡነ ሃብተማርያም ገዳም ካህናት አዲስ አበባ ቃሌ አከባቢ ሲያጥኑ መዋላቸው ተዘግቧል። ትናንት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የዐድዋውን ዘማች ታቦተ ጊዮርጊስን ይዛ ማዕጠንቱን ብታካሂድ ወረርሽኙ ድራሹ ይጠፋል በማለት ያሳሰብኩትም ማሳሰቢያዬም መልስ አግኝቷል። የአራዳ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን መጋቢት 20 ታቦቱን ይዘው ሊወጡ ነው። የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከትም መጋቢት 13 በአዲስ አበባም የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራትም በጋራ ከንጋቱ 12 ሰዓት ላይ አዲስ አበባን እንዲያጥኑ መመሪያ ተላልፏል።
በጣልያን ሊቀጳጳሱን ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስን አናግሬያለሁ። የጣልያን መንግሥት ፈቃድ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆነ እኛ ዝግጁ ነን ብለዋል። የጀርመኑን ሊቀጳጳስ ብፁዕ ዲዮናስዮስንም እንዲሁ አግኝቼ አውርተናል። ፈቃዱ ከመንግሥት ካለ እኛ ዝግጁ ነን።
____________________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith, Health | Tagged: መንፈሳዊ ሕይወት, ቃሌ, ቨርጂኒያ, አሜሪካ, አቡነ ሀብተ ማርያም, አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ, እስትንፋስ, እጣን እና ከርቤ, ዋሽንግተን, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን, ገዳም, ጋኔን, ጤንነት, Ethiopia, Frankincense & Myrrh, Holy Water, Water | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 23, 2020
በዚህ በጣም ተደስቼ ነው የዋልኩት፤ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን!
ትንሽ ቅር ያለኝ ነገር ግን እዚህ ድንቅ ገዳም ተራራ ጫፍ ላይ አንጋፋውን መስቀል ለማስተከል መስነፋችን ነው።
የፃድቁ አባታችን አቡነ አብተማርያም ቃል ኪዳናቸው ይጠብቀን የመጣውን መቅሰፍት ከአገራቸን ኢትዬጵያና ከመላው ዓለም ይሰውርልን!
________________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith, Health | Tagged: መንፈሳዊ ሕይወት, ቃሌ, አቡነ ሀብተ ማርያም, አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ, እስትንፋስ, እጣን እና ከርቤ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን, ገዳም, ጋኔን, ጤንነት, Ethiopia, Frankincense & Myrrh, Holy Water, Water | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 21, 2020
ቫይረሱ ጋኔን መሆኑን አረጋገጠልን!
ምን እንደሆነ አላውቅም እስከ አለፈው ነሃሴ ወር ድረስ ምናልባት በወር አንዴ ብቻ ነበር እጣን የማጤሰው፤ ካለፈው ጥቅምት ወር አንስቶ ግን በቤትም በመሥሪያ ቤትም በጣም አዘውትሬ አጤሳለሁ፤ የእግዚአብሔር ሥራ ድንቅ ነው፤ ቅዱስ መንፈስ ማድረግ የሚገባንንና የሚጠቅመንን ነገር ሳናስበውና ሳንዘጋጅበት እንድናደርገው ወደ በጎው ነገር ይመራናል።
ዛሬ ወደዚህ አይሁድ ቪዲዮ እንዴት እንደገባሁ ሁሉ አላውቅም፣ ያውም እጣንን በሚመለከት የገባሁበት ገጽ አልነበረም ፤ ግን ያው! ለኮሮና ጋኔን መፍትሄ ይሆናሉ ብዬ ሳስባቸው ከነበሩት ከጸበል፣ ከጸሎት ጎን እጣን እና ከርቤ እንደሚኖሩበት አረጋገጠለን። አሁን በዚህ በጣም እርግጠኛና ደስተኛ ነኝ።
ደካሞችና ምስጋና ቢሶች ሆነን ነው እንጂ አምላካችን እኮ የሚጠቅሙንን ነገሮች ሁሉ ሰጥቶናል፤ ጸበሉንም፣ ጸሎቱንም፣ እጣኑና ከርቤውንም በነጻ ሰጥቶናል። እጣንና ከርቤ ከወርቅ በላይ የሆኑበት ዘመን ላይ ደርሰናል። ለብዙ በሽታዎች ፈውስ እንደሆኑ ሳይንሱ ሳይቀር እያረጋገጠልን ነው። Seeing the Unseen of the Combination of Two Natural Resins, Frankincense and Myrrh

እጣኑን በአግባቡ እናጢስ፤ ወገኖቼ፤ ነገር ግን ከተለመደው የቡና ስነ ሥርዓት ወቅት፣ በተለይ ከኦጋዴን እና አረብ ዕጣኖች ጋር አብሮ ማጤሱን ዛሬውኑ ማቆም አለባችሁ! አባቶች ይህን አስመልክቶ አንድ ይበሉን!
አየን አይደለም?! ጠላት ዲያብሎስ ለብዙ ሳምንታት በቂ የኮሮና ቫይረስ በአውሮፕላን እንዲረጭ ካደረገ በኋላ ወሮበላው መንግስት “በረራዎችን አቁሜአለሁ ፣ ይቅርታ ቅብጥርሴ” አለን። ቫይረሱ ልክ እንደ አንበጣ እስኪፈለፈል የሁለት ሳምንታት ጊዜ ይወስድበታል ተብሏል። ስለዚህ አባቶች ልክ እንደ ጆርጂያ ኦርቶዶክስ አባቶች በተለይ አዲስ አበባን በመኪና እና በሄሊኮፕቶር እየዞሩ ዛሬውኑ ደጋግመው ጸበል ቢረጩና እጣን ቢያጤሱ ትልቅ ሥራ ይሆን ነበር። በተለይ ምዕመናን ለቅዳሴ የማይመጡ ከሆነ ይህ መደረግ አለበት። ቀዝቃዛዎቹ የጉንፋን ወራት ከመጀመራቸው በፊት አስቀድሞ መደረግ ያለበት አንዱ ተግባር ይህ ሊሆን ይገባል።
UPDATE
የመንፈስ ቅዱስን ሥራ እያየን ነው፡ ወገኖቼ? ዋው! የሚገርም ነው፦ ያው መምህር ጳውሎስም እንዲህ ይለናል፦
“የማዕጠንት ጊዜ ነው፤ ማዕጠንት ጥሩ ነው፤ በሽታ የሚያርቅ ነው፤ እጣኑንን እያሸተታችሁ…ካህናት በየቤቱ በመዞር ጸሎተ ማርያም እየደገሙና ማዕጠንት እያደረጉ ቢያልፉ በሽታው ያልፋል …ከተማው ይታጠላንል አስፈላጊ ከሆነ”።
ወደ እዚህ እንግባና ሙሉውን እናዳምጥ፦
“አስደናቂ ስብከት በሽታው የሚርቀው በማዕጠንት ነው መምህር ጳውሎስ መልካሥላሴ ክፍል፪
ቃለ ሕይወት ያሰማልን!
___________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith, Health | Tagged: መንፈሳዊ ሕይወት, መጽሐፍ ቅዱስ, አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ, እስትንፋስ, እጣን እና ከርቤ, ኮድ, ውሀ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን, ጋኔን, ጠበል, ጤንነት, ጸበል, Ethiopia, Frankincense & Myrrh, Holy Water, Water | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 12, 2019
መቼም ሕዝባችን ይህን ዜና መጀመሪያ ሲሰማ፡ “ዋው! ይሄማ ለበጎ ነው፤ አልኮል እኮ መጥፎ ነው፤ ማንም ይከልክለው ማን፤ ዋናው ጤናችን ነው”ይለናል፤ በጉዳዩ ላይ ሳያንፀባርቅበት።
ግን ይህ ትልቅ ስህተት ነው። ይህን ሕግ እንዲጸድቅ የገፋፋው የግራኝ አህመድ ቲም አባል የጤና ጥብቃ ሚንስቴር ሚንስትር ዶ/ር አሚር አማን ነው።(በአገራችን የማያክመው ዶ/ር በዛ)።
ስለ እስልምና ጠለቅ ያለ እውቀት ያለው ወገን ሥልጣን ቦታ ላይ የተቀመጡትን ሙስሊሞችን በጭራሽ ማመን የለብንም፤ በተለይ የወይን ጠጅ እና ሰባ ሁለት ልጃገረዶች በጀነት ተስፋ የሚያደርጉትን የመሀመድ ተከታዮችን።
“ለሕዝባችን ጤና አስቤ ነው” አለን ዶ/ር አሚር፤ መቼም ይህን ከአለቃው ከ ዶ/ር አህመድ የተማረው መሆን አለበት። እነዚህ ሰዎች ለኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን ምንም ዓይነት በጎ ነገር እንደማያመጡ እርግጠኛ ሆኜ ነው የምናገረው። “ለሕዝቡ መስማት የሚፈልገውን እየነገርከው አንት ሥራህን ሥራ” ብሎ የለም በግልጽ በመጸሐፉ፤ አዎ! የምዕራብ ኒዎ–ሊበራሎች /ለዘብተኞች የሚባሉት ሞግዚቶቹ ሹክ ብለውት እንዲጽፍ ባዘዙት መጽሐፉ ላይ። ኢትዮጵያውያን ይህን ትርኪ ምርኪ የተሰበሰበበትን መጽሐፉን አንብቡትማ፤ በኢትዮጵያውያን ላይ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ያለውን ንቀት ያሳየብት መጽሐፍ ነው። እነ አፄ ቴዎድሮስ፣ አፄ ዮሐንስን እና ሌሎች የተዋሕዶ አባቶችን ከግራኝ አህመድ ጋር በአንድ ረድፍ ያቆመበት ጽንፈኛ መጽሐፍ ነው።
ችግር – ምላሽ – መፍትሔ / “Problem – Reaction – Solution” ብሎታል፡ ተንኮለኛው ፈላስፋ ሄገል።
እንጀራ በሚበላባት ሃገራችን ጠላ ወይንም ጠጅ እና የወይን–ጠጅ እንጅ፡ ውስኪ፣ ቮድካና ቢራ ከጨጓራ እና ስኳር በሽታ ሌላ ለአገራችን ሰው የሚያስገኝለት ሌላ ምንም ነገር የለም። ታዲያ ይህ እየታየና እየታወቀ ባለፉት ዓመታት በአገራችን የቢራ፣ የአልኮል እና መርዛማ ለስላሳ መጠጦች ፋብሪካዎች እንደ አሸን ነበር የፈሉት፤ ከውጭ ድጎማ እየተደረጉ።
ታዲያ እነዚህ መጠጦች ትውልድን እያበላሹ መሆናቸው ግልጽ እየሆነ ሲመጣ እንደ መፍትሔ ነው በማለት ማስታወቂያዎችን አሁን ለመከልከል ወሰኑ። ግብዞች! እስከ መቼ ይህን ሞኝ ሕዝብ ያታልሉታል?
ዶ/ር አህመድን ሉሲፈራውያኑ ሥልጣን ላይ ሲያወጡት የመጀመሪያው ተግባሩ እንዲሆን ያደረጉት ወደ ትግራይ አምርቶ ተዋሕዶ ኢትዮጵያውያንን ልብ በትግርኛ ቋንቋ ለመሳብ መሞከር ነበር። ያ ሳይሳካ ሲቀር ወደ አሜሪካ በማምራትና ተዋሕዶ አባቶችን “አስታርቂያቸዋለሁ” በማልት አቡነ መርቆርዮስን ወደ ኢትዮጵያ ይዞ መጣ። አቡነ መቆርዮስ በእነ ሲ አይ ኤ እና ዲያስፐራ ፖለቲካ ፓርቲዎች ግፊት ነው ወደ ኢትዮጵያ የተመለሱት፤ እነርሱ ፈቅደውላቸው ነው እንጅ የዶ/ር አህመድ ፍልጎት ወይም ጥረት ስለነበረበት አይደለም። መቼ ነው የዋቄዮ አላህ ልጅ ለተዋሕዶ አስቦ የምያውቀው? በፍጹም!
ሁሉም ነገር ቀስበቀስ ነው፤ የእነዚህ እባቦች የሚቀጥለው እርምጃቸው አልኮል በአደባባይ እንዳይሸጥ ማድረግ ነው፤ ልክ እንደ ሳውዲ አረቢያ። አልኮል እና አደንዛዥ እጽ በሰፊው በመጠቀም በዓለማችን የሚታወቁት ሃገራት የሻሪያ ህግ የሰፈነባቸው ሙስሊም ሃገራት ናቸው። በአደባባይ ባይፈቀድም በድብቅ ግን አደገኛ በሆነ መልክ/ በጓዳ ብዙ አልኮሆል እና አደንዛዥ እፅ ይመረታል። ሻሪያ ኢራን ለምሳሌ በአደንዛዥ እፅ ፍጆት በዓለም የመጀመሪያውን ቦታ ይዛለች።
አንታለለ፤ ወገኖች! የክርስቶስ ተቃዋሚዎቹ ዒላማቸው ሕዝበ ክርስቲያኑ ነው፤ ጦርነቱም በጌታችን ቅዱስ ስጋና ክቡር ደም ላይ ነው፤ በቤተክርስቲያን በህብስት አምሳል የምንቀበለው የክርስቶስ ስጋ በወይን አምሳል የምንቀበለው የክርስቶስ እውነተኛ ደም እንደሆነ አምነን እና ተቀብለን የመዳናችን ሚስጢር የሚፈፀምበትን አምላካዊ ጸጋ ስለምናገኝበት፡ በጣም ስለሚቀኑ መድኃኒታንን ሊነጥቁን ይሻሉ። ሙስሊሙ የጤና ጥበቃ ሚንስትር“የሕዝባችን ጤና ያሳስበኛል” ሲል በተቃራኒው “ሕዝቡን ማኮላሸት አለብኝ” እንደሚል አድርገን መውሰድ አለብን።
ለህፃናቱ ሲባል ብቻ እነዚህ ሰዎች ብዙ ጥፋት ሳያመጡ ከያዙት ቦታ ቶሎ መነሳት ይኖርባቸዋል።
_____________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: ሙስሊም ሚንስትር, ማስታወቃያዎች, ሜዲያ, ሻሪያ, ቢራ, አሚር አማን, አብይ አህመድ, አዋጅ, ኢትዮጵያ, እገዳ, የአልኮል, ጤንነት | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 6, 2019
አሜሪካዊው የ ‘PEW’ ሉላዊ ጥናት አዲስ ባወጣው መረጃ መሠረት፤ እምነት ያላቸው ሰዎች ወይም ክርስቲያኖች ኢ–አማናያን እና አህዛብ ከሆኑ ሕዝቦች ጋር ሲነፃጸሩ፤
-
+ በጣም ደስተኞች ናቸው፣
-
+ ረዘም ላለ ጊዜ ነው የሚኖሩት፣
-
+ ለመንፈሳዊ ጭንቀት እና ራስን ማጥፋትን አደጋ አይጋለጡም፣
-
+ በግኑኝነቶች ያላቸው ታማኝነት ከፍ ያለ ነው፣
-
+ በቤተሰባዊ ህይወታቸው የበለጠ እርካታ አላቸው፣
-
+ በይበልጥ ደስተኛ የሆኑ ልጆች አሏቸው።
ጥናቱን ያካሄዱት አለማውያኑ እራሳቸው ይህን ሲመሰክሩ ማየቱ ደስ ይላል!
ምንም የሚያጠራጥር ነገር አይደለም፤ በመካከላችን በየቀኑ የምናየው ነው። ኢትዮጵያ በጥናቱ ባትካተትም፤ በኢትዮጵያውያን መካከል እንኳ አማኝ የሆኑት ካልሆኑት በደንብ ይለያሉ። ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ!
አማኝ ያልሆኑት ወገኖች፣ መሀመዳውያኑንም ጨምሮ፤ ሙሉ ሕይወታቸውን ከመንፈሳዊው ሕይወት በመራቅ፡ እራሳቸውን እያታለሉ ሥጋዊ እና ዓለማዊ በሆኑ ነገሮች ላይ ብቻ ደስታቸውን ለመግዛት ሲታገሉ እናያለን። እነዚህ ወገኖቻችን ደስተኞች፣ ጤናማዎችና ታማኞች አይደሉም። ክርስቲያኑ ግን፡ ምንም እንኳን እነዚህ ደስተኛ ያልሆኑ ወገኖቹ ሊበክሉት፣ ሊያሥሩት፣ ሊጎትቱት እና እያታለሉ ደስታውን ሊነጥቁት ቢሞክሩም ክርስቲያኑ ግን በእግዚብሔር ኃይል፣ በቅዱሳን እርዳታና በ ቤተክርስቲያን ሞግዚትነት ከእነዚህ ነጣቂዎች ይድናል። ክርስቲያኑ ከቡና፣ ጥምባሆና ጫት ከመሳሰሉት አታላይ ጉርብትናዎች ከራቀ ሁሌ ደስተኛና ጤናማ የሆነ እንዲሁም ታማኝነት የተሞላበትን ስኬታማ ኑሮ መኖር ይችላል።
አንድ የሚገረም ገጠመኝ፤ በመስቀል ዕለት፤ ከአክስቴ ልጆች ጋር ሆነን ወደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ሄድን፤ በጣም ደስ ይል ከነበረው ዓመታዊ ክብረ በዓል በኋላ፡ አምቦ ውሃ ነገር እንጠጣ ብለን ከቤተክርስቲያኑ ፊት ለፊት በምትገኘው “ቡና” / ምግብ ቤት በረንዳ ላይ ወንበሮች ያዝን (ቢዲዮው ላይ በከፊል ይታያል)። ከጎናችን አንዲት የተሸፋፈንች ሙስሊም ወገናችን ብቻዋን ቁጭ ብላለች፤ ቁና ቋና እየተነፈሰች እግሮቿንና እጆቿን እያንቀሳቀሰች ትቁነጠነጣለች፤ ደስተኛ አትመስልም። ለማንም ሳልናነገር፡ ምን ይሆን ብዬ፡ በጥሞና እከታተላት ጀመር፤ በጣም ያዘኑ የሚመስሉት አይኖቿ ወደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ላይ ነው ያተኮሩት፦ ምን ታስብ እንደሆነ ለማወቅ ያዳግታል፤ ነገር ግን የተዋሕዶ ልጆች በደስታና በፍቅር የቤተክርስቲያኑን ደረጃ ሲወጡና ሲወርዱ ማየቷ አስከፍቷታል…አንዴ ወደ ቤተክርስቲያኑ ላለማየት ወደ ጎን ዘወር ትላለች…አላስችል ሲላት መሀል ግንባሮቿን ሰብሰብ ታደርጋለች… ሁኔታውን በቃላት ለመሳል አይቻልም፤ ግን እኔ እርግጠኛ ነበርኩ፤ ለዘመዶቼም ቀስ ብዬ ይህን እንዲያረጋግጡ ሹክ አልኳቸው…በአምስት ደቂቅ ውስጥ እነርሱም የተገነዘቡት ነገር ይህን ነበር።
— Pew: Actively Religious People More Likely to Be ‘Very Happy’
_________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith, Life | Tagged: ቤተክርስቲያን, ታማኝነት, ኢ-አማንያን, ክርስቲያኖች, ደስታ, ጤንነት, Believers, Christians, Church, Happiness, Healthyness, PEW | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 28, 2019
“ሃጂ” የተባለው የዓለማችን በጣም ቆሻሻው ሰው ለ60 ዓመታት ያህል አልታጠበም
ለ 80 ዓመቱ አረጋዊ ኢራናዊ ቆሻሻነቱ በጣም ያስደስተዋል። ለዚያም ነው ባለፉት 60 ዓመታት ውስጥ ፈጽሞ ታጥቦ የማያውቀው። በደቡባዊ የኢራናውያን አንድ መንደር ውስጥ ብቻውን መቀመጥ ይወዳል።
ሃጂ ከውኃ ጋር ያለውን ግንኙነት ይጠላል። የመታጠብ ሀሳቡ ብቻ ሲነሳ በጣም ያናድደዋል።
የሃጂ ቆዳ የምድር ቀለም ይመስላል። ከአካባቢው ጋር ሙሉ በሙሉ ተደምሮ መኖር ችሏል። እንዲያውም ብዙ ከተቀመጠ ስለማይነቀናቅ ድንጋይን ወይም የዓለት ቅርፅን ይመስላል።
ሃጂ እምብዛም የማይታየው ገላ መታጠብ ብቻ አይደለም። ንጹሕ ምግብን እና ንጹሕ መጠጥን በጣም ይጸየፋቸዋል። በምትኩ ግን የሚወደው የበሰበሰና የገማ ስጋ ነው። ለጤንነት ሲል በቀን 5 ሊትር ያህል ውሃ ይጠጣል፥ ነገር ግን የነዳጅ ዘይት በነካው ጣሳ። በጥንባሆ ይልቅ የማጨሻ ቱቦውን በእንስሳት ፋንድያዎች በመሙላት ማጨስ ይወዳል። ፀጉሩን ለመቆርጥ መቀስን አይጠቀምም፤ በእሳት ነበልባል ላይ ያቃጥለዋል። በክረምት ወቅት በአሮጌ የጦርነት ቆብ ጭንቅላቱን ያሞቃል።
ሃጂ በእውነቱ ቤት የለውም ፤ ምድር የእርሱ መኖሪያ ናት። በመቃብር እንዳለ ሆን በዋሻ ውስጥ ይኖራል። አንዳንድ ጊዜ የመንደሩ ነዋሪዎች በሚሠሩት ክፍት የጡብ ጉድጓድ ውስጥ ይተኛል። በአካባቢው ነዋሪዎች “አሙ ሃጂ” ይባላል። «አሙ» በፋርስኛ ቋንቋ፡ አረጋዊ ደግ ሰው ማለት ነው።
የሃጂ የአኗኗር ዘይቤ በጣም ልዩ ነው። የመንደሩ ነዋሪዎች በወጣትነት ዕድሜው ከባድ የስሜት መጎሳቆል ደርሶበት እንደነበር ይናገራሉ። ይህም እነዚህን የከፉ ምርጫዎች እንዲፈጽም አድርጎታል። እንደዚያም ሆኖ በትላልቅ ቤቶች ውስጥ በምቾትና በመንደላቀቅ ከሚኖሩ ሰዎች ይልቅ ደስተኛ ይመስላል። ሃጂ ለዚህም አለም ግድ የለውም። ምንም የሚጎድልበት ነገር የለም፣ ምንም ፍርሃት የለውም።
_________
Like this:
Like Loading...
Posted in Curiosity, Ethiopia, Infotainment | Tagged: ሃጂ, ምግብ, ቆሻሻ, ንጽሕና, አረጋዊ, አፈር, ኢራን, እንስሳት, ውሃ, ጤንነት | Leave a Comment »