
በጥቁር ሕዝብ፡ በተለይ በኢትዮጵያውያን ላይ የተጠነሰሰው ሴራ ማለቂያ ያለው አይመስልም፡ ልክ እንደ ውቂያኖስ ሰፊ ነው። በርግጥ ይህ አዲስ ነገር አይደለም፡ ሆኖም የኢትዮጵያውያን ጠላቶች በየጊዜው መልካቸውን እየቀያየሩ ሲመጡ ግርም ሊለን፡ ሊረብሸን ይችላል፡ ጊዜው የጭንቀት ነውና። በሌላ በኩል ግን ይህን የጠላቶቻችንን ተንኮል ዘመቻ ነቅተን የምንጠነቀቅበት ከሆነ እንደ ሲሳይ ወይም ጸጋ አድርገን ልንወስደው ስለምንበቃ፡ ለጭንቀት አንጋለጥም፡ ለልዩ ተልዕኮ እንደተመረጥን ይጠቁመናልና።
በሰው ልጆች ነፍስ ላይ የሚካሄደው ጦርነት እየተጧጧፈ መጥቷል። ባጭር ጊዜ ውስጥ በቴክኒንክና ቴክኖሎጂ እየተራቀቁ የመጡት የመገናኛ ዘይቤዎች ለሁላችንም ብዙ ጠቃሚ ጎኖች እንዳላቸውም ሁሉ፡ ዲያብሎሳዊ ለሆኑ ድርጊቶችም ዓይነተኛ እርዳታ በማበርከት ላይ ይገኛሉ። ዲያብሎስን የሚወክሉት የጨለማው ሀይሎች አሁን ከምንግዜውም በላይ ተግተው በመወራጨት ላይ ይገኛሉ። ዓላማቸውም የሰውን ሕይወትና ነፍስ መግደል፥ መስረቅና ማጥፋት ነው። እነዚህን ዲያብሎሳዊ ድርጊቶች ማን እንደሚፈጽም አሁን በግልጽ ለማየት ስለበቃን፡ ለፈጣሪው ክብር፡ ፍርሃትና ፍቅር ያለው ግለሰብ ሁሉ ሳያመነታ አፍጦ የመጣበትን የዲያብሎስ ሠራዊት ተግቶ ሊዋጋው ይገባል። ጊዜው የእንቅልፍና የጨዋታ ጊዜ አይደለም።
ዓለማችንን በሽብርና በግድያ ለመውረስ ቆርጠው ከተነሱት እስላም አክራሪዎች ጎን ለጎን ግብረሰዶማውያንም የእግዚአብሔርን ፍጡር ለመዋጋት፡ ነፍስን ለማጥፋትና ለመስረቅ ባላቸው አጀንዳ የራሳቸውን መንገድ ይዘው በመጓዝ ላይ ናቸው። የእስልምናው ሠራዊት ዓለም እስልምናን ካልተቀበለ ደም ከማፍሰስና ነፍስ ከማጥፋት ወደ ኋላ እንደማይል እንዲሁም ግብረሰዶማውያንም ዓለም ሁሉ የነሱን ዓይነት አኗኗር ካልተከተለ፡ የሰውን ልጅ በድብቅ እያሳደዱ መመረዙን፡ በጨረር እየጠበሱ መዋጋቱን ሥራየ ብለው እየተያያዙት ነው። እነዚህ ሁለት ሽብር ፈጣሪ ሀይሎች የዲያብሎስ አገልጋዮች መሆናቸው የሚያጠራጥር አይደለም። ግን ሰይጣን አታላዩ ሁለቱ የተለያዩ ተልዕኮዎች ያሏቸው ኃይሎች እንደሆኑ አድርጎ ሊያሳየን ይሞክራል። በእስላሞች ዘንድ ግብረሰዶማዊነት ጸያፍ እንደሆነ፡ ግብረሰዶማውያንም እንደሚጠሉ፡ ክትትል እንደሚደረግባቸው ብሎም እንደሚገደሉ እንሰማለን፡ አዎ ይህ ትክክል ነው፡ ነገር ግን ይህ የሆነው ግብረሰዶማዊነት ነውራማና ሀጢአታማ የሆነ ተግባር ነው ብለው ስለሚያምኑ ሳይሆን፡ ግብረሰዶማዊነት የጂሃዳውያንን የተዋጊነት መንፈስ ያደክማል ከሚል ፍራቻ የተነሳ ዲያብሎስ አለቃቸው ምስጢሩን ሊያካፍላቸው ዝግጁ ስለሆነ ነው። ዲያብሎስ ለረጅም ጊዜ ለትግሉ ያዘጋጀውን ሠራዊቱን በቀላሉ አይረሳም፡ አስፈላጊውን እርዳታ ሁሉ ያበረክታል።
እምነት የጎደላቸው የሌላቸው ወይም ትክክለኛውን ሃይማኖት የማይከተሉ ሰዎች ቀስበቀስ ወደ ግብረሰዶማዊነት ሊቀየሩ ይችላሉ። ግብረሰዶማዊነት በብዙ እስላም አገሮች በድብቅ በጣም ተስፋፍቶ ይገኛል። የኢንተርኔቱ ጉግል ከሚያወጣው መረጃ ለመረዳት እንደምንችለው፡ ግብረሰዶማዊ መንፈስ ያላቸው ድህረገጾች በብዛት የሚጎበኙት፡ እንደ ፓኪስታን፡ ኢራንና ግብጽ በመሳሰሉት የእስላም አገሮች ነው። የቆሰለው ኮሎኔል ጋዳፊ በሊቢያውያን አርበኞች በተያዘበት ወቅት በጣም አጸያፊና ሰዶማዊ በሆነ መልክ ተሰቃይቶ እንዲሞት መደረጉ የመንፈሱን ባሕርይ በግልጽ ሊያሳያን ይችላል። በአሜሪካና አውሮፓ የሚገኙ ኢ–አማንያን የግብረሰዶማውያንና የሴቶች መብቶች ተሟጓቾች፡ ለእስልምና አጀንዳ ድጋፉን ለመስጠት ዝግጁነታቸውን ማሳየታቸው፤ ምንም እንኳን እስላሞች ለግብረሰዶማዊነት እና ለሴት ልጅ ያላቸውን ጥላቻና ንቀት በይፋ ቢያሳውቁም፡ ከነርሱ ጋር እየተተባበሩ ዋናውን ጠላታቸውን፤ ክርስትናን በመዋጋት ላይ መገኘታቸው አንዱ ሌላ ጥሩ ምሳሌ ነው። ለዚህ ነው ሰዶማውያንና ኢ–ዓማንያን እስልምናን ለመቃወም ግድ የሌላቸው፡ ትንፍስ አይሉም፡ የመንፈሱ ምንጭ አንድ ነውና፤ ከክርስቶስ የራቀው ነውና።
የጸረ–ክርስቶስ ኃይሎችና የግብረሰዶማውያን አጀንዳ አሁን በተለይ በአፍሪካ ላይ ነው ዋናውን ትኩረት እያደረገ ያለው። የኤድስን በሽታ የሚመለከት ስብሰባ ሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ እንዲካሄድ የተደረገው ለተንኮል መሆኑ ምንም አያጠራጥርም። እንደሚታወቀው የኤድስ በሽታ ሰው ሰራሽና በላብራቶሪ ውስጥ ተቀምሞ የተፈጠረ በሽታ ነው። ይህ በሽታ በይበልጥ እያጠቃቸው ያለው በተለይ ጥቁር ሕዝቦችን፡ ምስራቅ አውሮፓ የሚገኙትን ኦርቶዶክሳዊ ነፍሳትንና ግብረሰዶማውያንን ነው። ግብረሰዶማውያኑ የመጀመሪዎቹ የኤድስ ቫይረስ ተሸካሚዎች/አመላላሾች ነበሩ። የአመንዝራ ኑሮ የሚኖረው፣ እንዲሁም እንስሳዊ የግብረስጋ ግኑኝነቶች ወይም አስቀያሚ የወሲብ ልምዶች በብዝት የሚታዩት ባህለ–አልባ / ሃይማኖት–የለሽ በሆኑት የምዕራቡና የመካከለኛው ምስራቅ አገሮች ነው። የሚገርመው ነገር በነዚህ አገሮች ለኤይድስ በሽታ የተጋለጡት ነዋሪዎች በጣት የሚቆጠሩ መሆናቸው ነው። ሳዑዲ ዓረቢያ ደግሞ ሴቶችዋ የመኪና መንጃ ፈቃድ ማውጣት ተፈቅዶላቸው የተሸከርካሪ መሪ መያዝ ከጀመሩ የሳዑዲ ዜጎች ሁሉ ግብረሰዶማዊ ለመሆን ይበቃሉ እያለች ታጉረመርማለች። እዚህ ላይ ማንበብ ይቻላል።
ሰይጣን የእግዚአብሔርን ልጆች ተግቶ መዋጋት ይወዳልና፡ “አታመንዝር!” የሚለውን የአምላክ ትዕዛዝ የሚጥሱ ክርስቲያኖች ለዚህ የኤች አይ ቪ ኤይድስ በሽታ በቀላሉ ይጋለጣሉ። ይህን በመገንዘብ በሽታውን የፈጠሩት የሰይጣን ባለሙያዎች እራሳቸውን እንደ ፈጣሪ አድርገው በመውሰድ የእግዚአብሔርን ንብረት በዚህ መልክ ለማመንመን ይሞክራሉ። ከሳሹ ሰይጣን ቀድሞ፡ “ማን አመንዝሩ አላችሁ!” በማለት በፈጸመው ድርጊት እንዳይኮነን ይፈልጋል።
እየመጣብን ያለው የጠላት ኃይል ቀላል አይደለም። ይህ ጠላት ሲያሰኘው እርስበርሳችን እንድንጠላላ፡ እንድንነቋቋር ያደርገናል፤ ሲያሰኘው ደግሞ ትንሽ ሳቅ እያለልን ሰላሙንና ብልጽግናውን ለተወሰነ ጊዜ እንድናገኝ በመፍቀድ እያዘናጋ ሊያደክመን ይሞክራል።
ሕዝባችንን ጦርነት ሊጨፈጭፈው አልቻለም፤ ሕዝባችንን ድርቁና ረሀቡ ሊጨርሰው አልቻልም፤ ሕዝባችንን በሽታው ሊያጠፋው አልቻለም። ስለዚህ አሁን ሰይጣን ሕዝባችንን ለማንበርከክ የሚጠቀመው ስልት እንደ እባብ ለስለስ ብሎ በመግባት የተዘናጋውንና በመከፋፈል ደከም ብሎ የሚገኘውን የሕብረተሰቡን ክፍል፡ በተለይ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን መንደፍ መቻል ነው። ይህን ለማድረግ ከበቃ ኢትዮጵያ አለቀላት ማለት ነው፡ የምትጠላውም አፍሪካ እንደተቀሩት አህጉራት በእጁ ውስጥ ገባችለት ማለት ነው። ስለዚህ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ሁሉ በሃብት ምኞት ሳይጠመድ፡ ቅንጦትና ጥጋብን ሳይመርጥ ለመጪው የትግል ጊዜ ቀበቶውን ጠበቅ ሊያደርግ ይገባዋል። በእግዚአብሔር እርዳታ ድሉ የኛ እንደሚሆን የማያጠራጥር ነው!
የአምላክ ህልውና የማያውቁ ሰዶማውያን
“ሰዶማውያንና የኃጢአት ደመወዝ” ከሚለው የአባ ሳሙኤል መጽሐፍ የተወሰደ
ከታላቅ አክብሮትና ምስጋና ጋር…
ሃይማኖት ዓለምን በማናቸውም ረገድ ለመምራትና ለመተንተን የሚያልም፣ ተፈጥሮ ከራሷ በላይ በሆነ መለኮታዊ ኃይል የምትገዛ እና የምትመራ ናት በሚል ቀኖና ላይ የተመሠረተ ኢ–ሳይንሳዊ አመለካከት ነው በሚል መሠረታዊ መግባቢያቸው የአምላክን ህልውና የሚከዱ ሰዎች ተነሥተው ሃይማኖትን ተቃውመዋል ዛሬም ይቃወማሉ።
ከቀጥተኛው የክርስትና ሃይማኖት ያፈነገጡ ወይም ከተለያዩ ቦታዎች የተውጣጡ የአምላክን ህልውና የማያውቁ ሰዎች (1ዮሐ.2:19)የሚቆጣጠራቸው ሃይማኖታዊ ሕግ ስለሌላቸው ዝሙት፣ ስርቆት፣ ግድያ፣ ወንጀልን አበራክተዋል (ሄኖ. 2:1) አብዛኛዎቹ የግብረ ሰዶማዊነት ሰለባ ሆነዋል በዚህም የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ዓላማ ፊት አውራሪ በመሆን ርኵሰትን አስፋፍተዋል። (ሮሜ.1:24-27 )
መናፍቃን ሰዶማውያን
በሃይማኖት ተከልለናል በክርስትና ውስጥ አለን እያሉ ነገር ግን ከክርስቲያናዊ ስነ ምግባር ውጭ የሚንቀሳቀሱ የእግዚአብሔርን ሕግ የሚያፈርሱ መናፍቃንም ከቀድሞው ይልቅ አሁን ቁጥራቸውን እና ድርጅታቸውን ጨምሯል።
እነዚህ ሥጋዊ ፍላጎታቸውን እና እንስሳዊ ጠባያቸውን ለማደለብ ሲሉ ብቻ የመጽሐፍ ቅዱስን መልእክት አለአግባብ በመጥቀስ የቀጥተኛይቱን ሃይማኖት (ዶግማ) እና ቀኖና አፋልሰዋል።
ከሕግ በላይ ነን በሚል ኑፋቄ የርኵሰት ኃጢአት ውስጥ ሰጥመዋል።
ከነዚህም ዋነኛ እና ተቀዳሚዎቹ መናፍቃን የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻን የፈቀዱ ከፍ ብለውም ክህነት ይገባናል የሚሉት ናቸው።
እነርሱም ከሌላ የኅጢአት ዕድገት ደረጃ ላይ ደርሰዋል። እነዚህ መናፍቃን ከዚህ ቀደም በሐዋርያት ዘመን ተነሥተው እግዚአብሔር ያደራጀውን የጋብቻ ሕይወት በማርከስ ማግባትንም እንደ ኅጢአት በመቍጠር ጋብቻ የኅጢአት ውጤት መሆኑን አስተምረው ነበር። (1ጢሞ.4:3)
አበው ግን ይህንን የተዛባ የአጋንንት ትምህርት “እኛስ ጋብቻ ንጹሕ እንደሆነ መውለድም ልደትም ርኵሰት እንደሌለበት እንናገራለን…”
ብለው የሃይማኖት ውሳኔ ሰጥተው አውግዘው ለይተዋቸዋል። ታድያ “ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስ አይለቅም” እንዲሉ ዛሬም ይህንኑ የጋብቻ ምስጢር ለማዛባት ቅድስናውን ለማርከስ መልኩን በቀየረው ኑፋቄአቸው የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻን አውጀዋል።
አሁንም ቅዱስ የሆነውን የቅድስና ሕይወትነት ለማፍረስ የትላንትና ቀስታቸውን አነጣጥረዋል።
ጌታ “ምስክሮቼ ትሆናላችሁ” (የሐ.ሥ.1:8) እንዳለው ለእውነት ምስክር ለመሆን የእግዚአብሔርን ቃል ለማስተማር የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሥርዐት ለመጠበቅ ንጹሕ የሆነውን የጋብቻ ሥርዐት በረከሰ መንገድ መጠቀም ኅጢአት ክህደት መሆኑን እናረጋግጣለን።
ሰዶማውያን፣ በተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ውስጥ ያሉትም፣ የዚህ የርኩሰት ኅጢአት ሰለባ የሆኑት ሁሉ ንስሐ እንዲገቡ ጥሪ እናደርጋለን።
ግብረ ሰዶማዊነት የሰለጠነውን ዓለም አጥፍቷል
እኛ በሥጋ ያልኖርንባት በመጽሐፍ የምናውቃት ትልቅ የሰለጠነች ከተማ ነበረች (ዘፍ.6:1) ይህችን ከተማ አሁን ከበለጸጉትና ከሰለጠኑት ከተሞች ልዩ የሚያደርጋት ኅብረተሰቡ ሁሉ የአንድ ቋንቋ ተናጋሪ መሆኑ ነው። (ዘፍ.11:1 )
በተለይም የምድራችን የመጀመሪያው ተወላጅ ቃየል የቆረቆራት ከተማ ሰማይን የሚታከኩ በሚመስሉ ፎቆች፣ ሕንጻዎች አሸብርቃለች (ዘፍ.4:17፤ ኩፋ.)ጭፈራን ዳንኪራን አስተናግዳለች (ዘፍ.4:21 )
ዝሙትን፣ ምንዝርን፣ ሴሰኝነትን ወልዳ አሳድጋለች (ዘፍ.6:2-4፣ ዘፍ. 4:19) ከእዚህ ዝሙት ምንዝር፣ ሴሰኝነት የሚሉትን ቃላት ማብራራት ያስፈልጋል።
ዝሙትን ከጋብቻ ክልል ውጭ የሚፈጽም ሕገ ወጥ ድርጊትን ያሳያል (1ቆሮ 6፣9፡18) ምንዝር ሴተኛ አዳሪነት መሆንን ያሳያል። ከሥጋ ዘመድ ጋር መርከስን ያመለክታል። (ዘሌ.20፥10፣ማቴ.5፥27-30) ሴሰኝነት የተመሳሳይ የጾታ ግንኙነትንና ሌሎችንም ተዛማጅ የርኵሰት ኅጢአቶችን ያካትታል። (1ቆሮ 6፥9፣ ራእ.21፥8 )
እነዚህ ሁሉ ኅጢአቶች በዚች በሰለጠነችው ከተማ ተንሰራፍተዋል። ከብዙ ጥያቄዎች መካከል አሁን በሕሊናችን አንድ ጥያቄ ብቅ ይላል።
ይኽውም የአንድ ከተማ ሥልጣኔ መለኪያው ሰማይ ጠቀስ ፎቅ ይሆን? የሥልጣኔስ ትርጉሙ እንዲህ ይሁን! የሚል ነው?
የሰዶማውያን መብት
ሰዶማውያን እንደጥንቱ ሁሉ በሰለጠኑ ከተሞች ሕግ ተደንግጎላቸው አንቀጽ ተሠርቶላቸው “መብት” የሚሉት የኅጢአት ጉርሻ ሳይነፈጋቸው ተቃውሞ ሳይገጥማቸው እነሆ እየኖሩ ይገኛሉ።
ከዚህም አልፈው ተርፈው በሃይማኖት ስም የተፈረጁት ደግሞ መናፍቃን “በቤተ ክርስቲያን ስም” ሹመት ሽልማት እያገኙ ጳጳስ፣ ኤጲስ ቆጶስ እስከ መሆን ደርሰዋል።
ይሁንና እኛ ክርስቲያኖች ግን ይህ የድፍረት ኅጢአት ከሰማይ በታች አዲስ ሆኖ ባንሰማውም የኅጢአቱን ደረጃ እያስተዋልን። በቅድስና ሕይወት ያልረከሱት በጥንቃቄ መኖር ይገባናል።
እንግዲህ በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን “የጥፋት ርኵሰት በተቀደሰችው ስፍራ ቆሞ ስታዩ አንባቢው ያስተውል” (ማቴ.24:15) ባለው ትንቢታዊ መመሪያ መሠረት ቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ይህ የድፍረት ኅጢአት ባይታይም በሃይማኖት ስም መንሰራፋቱን እናወግዛለን። (2ጢሞ.4:1-5)
በክርስትና ትምህርትም ለሰዶማውያን ከቅዱሳት መጻሕፍት ያልተገኘ መብት መስጠት የጥፋትን ርኵሰት ማባባስ ነውና እንቃወማለን።
በመሠረቱ መብት ማለት ያለን፣ ከፈጣሪ የተሰጠን ስጦታ እንጂ ለምነን የማናገኘው ጠይቀን የምናመጣው ቁስ አይደለም። (ዮሐ.3:34 ) ሰዶማውያን ሊለምኑት ሊጠይቁት የሚገባቸው መብት ደግሞ ንስሓ መግባትን ብቻ ነው። (ሊቅ.3:14)
እነርሱ ግን ንስሓ ከመግባት ይልቅ በኢያእምሮ በሚሠራ ርኵሰት ለክህነት አገልግሎት ከአምላክ የተሰጠውን መስፈርት ወዲያ አሽቀንጥረው ክህነት ለማግኘት በእግዚአብሔር ላይ መነሳሳታቸው የድፍረት ኅጢአት ሆኖባቸዋል። (ቲቶ.1:6,8:16)
በደል ንስሓ ባለመግባቱና ምድራችን በምታስተናግደው የሥጋ ሁሉ ፍጻሜ እና የዝሙት ውጤት ነው። “ፈዋሻችሁ እግዚአብሔር እኔ ነኝ” ወደሚለው አምላክ ተመልሰው ከመፈወስ ይልቅ ለኅጢአታቸው ምክንያትን ይደረድራሉ፣ ሕግም ይቀርጻሉ። በተለይ በአሜሪካን ሀገር ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ተቀባይነትን እያገኘ እየተስፋፋ ብዙዎችን ወደሞት አፋፍ የሚያፋጥነው ግብረ ሰዶማዊነት ዋነኛ ተጠቃሽ ነው።
እነዚህ የሰለጠኑ ተብለው የሚነገርላቸው ምዕራባውያን ኮንግረሳቸውን አልይም ሰኔታቸውን ሲጀምሩ ከሁሉ አስቀድመው መጽሐፍ ቅዱስን ጸሎት ያደርሳሉ ተገልጠው በሕዝብ መዝሙራቸውም ውስጥ ባለአንድ ሰንደቅ ዓላማ ሆነው በአምላክ እጅ ያሉ እና አንድ ወገን መሆናቸውን የሚያትተውን ስንኛቸውን “one nation one flag under God” ሲሉ ያዜማሉ፣ በዶላራቸውም “We trust in God” ብለው በፈጣሪ እንደሚታመኑ ገልጸዋል።
ነገር ግን የአምላክን ስም በጠሩበት ልሳናቸው መጽሐፍ ቅዱስን ባነበቡበት አንደበታቸው ርኵሰትን አውርተውበታል። ማለትም በ“ጸሎት” በከፈቱት ኮንግረሳቸው ሲቪላይዜሽን (Civilization) እንበለውና ሥልጣኔ በሚሉት አካሄዳቸው ግብረ ሰዶማውያን በግብረ ሰዶማዊነታቸው የሕግ ከለላ እንዲያገኙ አድርገዋል፣ አሁንም ይበልጥ እያደረጉ ይገኛሉ።
ይህንን ከተፈጥሮ ሕግ ውጭ የሚተገብሩትን አካሄድ ማለት የሚቻለው ሲቪላይዜሽን (Civilization) ወይስ ኢቪላይዜሽን (Evilization)? ማለትም በሀገራችን ቋንቋ መሰልጠን እንበለው። ጥያቄ ያጭራል። (ወይም አለመሰልጠን)
በእጅጉ የሚገርመው ይህ የተዛባ አካሄዳቸው “በአፋሆሙ ይድኅሩ ወበልቦሙ ይርግሙ” በአፋቸው ያመሰግናሉ በልባቸው ግን ይረግማሉ የሚለውን የነቢዩን ቃል አስታውሶኛል።
ሁሉም ሰው ማለት ይቻላል ደግሞ “ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፣ የሰውም ሥርዐት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል” የሚለው በአይሁድ ላይ የተፈጸመው የነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት በምዕራባውያኑ በተለይ አንዳንድ በኮንግረስ አባልነታቸው ስለ ግብረ ሰዶማዊነት ትክክለኛነት በሚመሰክሩት ላይ እንደደረሰባቸው ሊያስተውል የሚችል ያስተውል።
የክርስቲያን ማንነቱ የሚገለጸው እንዲህ እንደ አሜሪካውያን የአምላክን ስም በጠራንበት ብዛት አይደለም “We trust in God” በእግዚአብሔር እንታመናለን፣ እንመካለን ማለት በጣም ቀላል ነው፣ የእምነት ማረጋገጫ መሆን ግን አይችልም የእምነት ማረጋገጫ ለአምላክ ሕግ በመታዘዝ ብቻ ይገለጻል፣ ክርስቲያኖች “እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ።” (ማቴ.5:14) ተብለው እንደተደነቁት ሐዋርያን በዕለታዊ ሥነ ምግባራቸው ይታወቃሉ እንጂ በብዙ ጎኑ ዘንድ የተለመዱ ሃይማኖታዊ ቃላትን በመጠቀማቸው ብቻ የእግዚአብሔር ሰዎች እንዲሆኑ አያስችላቸውም።
የአምላክን ስም መጥራት እና የመጽሐፍ ቅዱስ ቃልን መጥቀስ በቂ የክርስትና ምልክት አይሆንም ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስን በማወቅና በመጥቀስ ረገድ ሰይጣንን የሚተካከለው የለምና (ማቴ.4) ሰይጣን የአምላክን ኃይል ያምናል ይንቀጠቀጣል ለእግዚአብሔር ይገዛል ነገር ግን በጐ ምግባር የለውም ይህም የሚታወቅበት ጠባዩና ልዩ ምልክቱ ነው።
በምዕራባውያን ጎዳናዎችና በተላላቅ የመዝናኛ ሥፍራዎች ሴትና ሴት በፍትወት እየተፈላለጉ ወንድ እና ወንድ እየተቧደኑ በፍትወት ሲቃጠሉ ማየት የዕለት ሁኔታ ሆኗል። በዚህም ኃጢአታቸው ንስሓ ከመግባት ይልቅ “ኑሮ ካሉት መቃብር ይሞቃል” እያሉ የሰነፎችን እና ተስፋ የቆረጡ ሰዎችን ብሂል ምሽግ አድርገው ለኅጢአታቸው ምክንያት ሳይኖራቸው ከሕይወት ይልቅ ሞትን መርጠዋል።
ባጠቃላይ በአሜሪካና በአውሮፓ ሀገሮች ሁኔታዎች ከተፈጥሮ ሥርዐትና ሃይማኖት ውጭ አፈንግጠዋል። ይህን የኑሮ ዘዴ በማስተዋሌ ግብረ ሰዶማዊነትና የኅጢአት ደመወዝ ብዬ የሰየምኩትን መጽሐፍ ለመጻፍ መንሥኤ ሆኖኛል። በእርግጥ በሀገራችን ኢትዮጵያ ካለው ባሕልና የሃይማኖት ክብር የተነሣ ግብረ ሰዶማውያን ራሳቸው ግብረ ሰዶማዊነታቸውን እየተነተኑ ምክንያት መስጠት ባይደፍሩም፣ በድብቅ የሚለማመዱት እና የሚፈጽሙት ተከታዮቻቸው መበራከት ወደፊት ለወጣቱ ትውልድ ሃይማኖትና ባሕል የለሽ እንዳይሆን ነው።
________________________________________
Like this:
Like Loading...