Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • March 2023
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    2728293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ጌታ’

ቀዳም ሥዑር | የቅዱስ እሳት ተአምር በኢየሩሳሌም | The Miracle of the Holy Fire in Jerusalem

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 1, 2021

✞✞✞ቅዳሜ፤ ቀዳም ሥዑር (ሹር ቅዳሜ)፤ ለምለሚቱ ቅዳሜ፥ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ፥ ሰንበት ዐባይ፥ ቅዱስ ቅዳሜ።✞✞✞

የማያቃጥለው እና የክርስቲያኖችን ነፍስ የሚያስደስተው ይህ ድንቅ ሥነ-ስርዓት በኢየሩሳሌም በሚገኘው የትንሳኤ ቤተክርስቲያን ውስጥ በቅዱስ ቅዳሜ ይካሄዳል።

ፋሲካ የሚውልበት ቀን በየዓመቱ እንደ አዲስ ይወሰናል፡፡ የቀን እና የሌሊት ርዝመት እኩል በሚሆንበት የፀደይ እኩልነት እና ከአይሁድ ፋሲካ በኋላ የመጀመሪያ እሁድ መሆን አለበት። ስለዚህ ብዙ ጊዜ የተለያዩ መስፈርቶችን በመጠቀም ከሚወስነው የካቶሊክና ፕሮቴስታንት ፋሲካ ቀን ይለያል።፡ የቅዱስ እሳት በዓለም ምስራቅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በጣም የታወቀ ተዓምር ነው፡፡ ለዘመናት በየአመቱ በተመሳሳይ ቦታ፣ በተመሳሳይ ጊዜና በተመሳሳይ ሁኔታ ይካሄዳል። ከጊዜ ወደ ጊዜ እንደዚህ በመደበኛነት እና ያለማቋረጥ የሚከሰት ሌላ ተዓምር አይታወቅም። የሚከናወነው በኢየሩሳሌም በሚገኘው የትንሳኤ/ የቅዱስ ጎለጎታ ቤተ ክርስቲያንን ውስጥ ነው ፣ በምድር በጣም በተቀደሰው ስፍራ ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በታሰረበት፣ በተሰቀለበት እና በመጨረሻም ከሞት በተነሳበት፡፡

The ceremony, which awes the souls of Christians, takes place in the Church of the Resurrection in Jerusalem. The date for Pascha is determined anew for every year. It must be a first Sunday after the spring equinox and Jewish Passover. Therefore, most of the time it differs from the date of Papal Protestant and Protestant Easter, which is determined using different criteria. The Holy Fire is the most renowned miracle in the world of Eastern Orthodoxy. It has taken place at the same time, in the same manner, every single year for centuries. No other miracle is known to occur so regularly and so steadily over time. No other miracle is known to occur so regularly and so steadily over time. It happens in the Church of the Holy Sepulchre in Jerusalem, the holiest place on earth, where Christ was crucified, entombed, and where He finally rose from the dead.

Breaking News from #Jerusalem the Resurrection Church :blood is leaking from the stone Jesus body was laid before his burial . You can hear the Israeli police closed the area.

___________________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የጌታችን ስቅለት በዓል የአዲስ አበባ አድባራት በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው በነበሩበት ዘመን

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 30, 2021

ዛሬስ? ዛሬማ የአርዮስ ኢሬቻ በላይና አጋንንት መንጋው መፈንጫዎች ሆነዋል።

✞✞✞ዓርብ ስቅለት በደብረ ቤቴል አበ ብዙሃን-አብርሃም ገዳም✞✞✞

✞✞✞ዓርብ ስቅለት | ተፈጸመ! | ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ ወጣን✞✞✞

ዓርብ ስቅለት የዕዳ ደብዳቤያችን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ለመጨረሻ ጊዜ የተደመሰሰበት፤ ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ የወጣንበት ዕለት ስለኾነ የድኅነት ቀንይባላል፡

👉 ጌታችን ሲሰቅል የሚከተሉት ሰባት ተአምራት ተፈጽመዋል፤

፩. ፀሐይ ጨለመ፤

. ጨረቃ ደም ኾነ፤

. ከዋክብት ረገፉ፤

. የቤተ መቅደስ መጋረጃ ተቀደደ፤

. አለቶች ተፈረካከሱ፤

. መቃብራት ተከፈቱ፤

. ሙታን ተነሡ (ማቴ. ፳፯፥፶፩፶፬)፡፡

____________________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የጌታችን ስቅለት ከ፸፫/73 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በቅዱስ ኡራኤል ዕለት ዋለ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 30, 2021

✞✞✞ዓርብ ስቅለት ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ የወጣንበት ዕለት ነው✞✞✞

ዓርብ ስቅለት (የድኅነት ቀን) የዕዳ ደብዳቤያችን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ለመጨረሻ ጊዜ የተደመሰሰበት፤ ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ የወጣንበት ዕለት

ዓርብ ስቅለት የዕዳ ደብዳቤያችን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ለመጨረሻ ጊዜ የተደመሰሰበት፤ ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ የወጣንበት ዕለት ስለኾነ ‹የድኅነት ቀን› ይባላል፡፡ ጌታችን ከተያዘባት ሰዓት አንሥቶ አይሁድ ከቀያፋ ወደ ሐና፣ ከሐና ወደ ቀያፋ ሲያመላልሱት አደሩ፡፡ ሲነጋ ከቀያፋ ወደ ጲላጦስ አደባባይ አስረው ወሰዱት (ማቴ. ፳፯፥፩-፶፯)፡፡ አይሁድ ይህን አጥፍቶአል የሚሉት ነጥብ ሳይኖራቸው ነውና ጌታችንን ለፍርድ ያቀረቡት ጲላጦሰ እነርሱ ወደ ተሰባሰቡበት ቦታ ወጥቶ “ይህን ሰው ወደ እኔ ያመጣችሁበት በደል ምንድን ነው?” ሲል በጠየቃቸው ጊዜ በቂ ምላሽ አላቀረቡም፡፡

“ክፉ የሠራ ባይኾንስ ወደ አንተ ባላመጣነውም ነበር በሚል የሸፍጥ ቃል ሲያጕረመርሙ ጲላጦስ መልሶ እኔ ምንም ጥፋት አላገኘሁበትም፤ እናንተ ወስዳችሁ እንደሕጋችሁ ፍረዱበት፤ አላቸው፡፡ አይሁድም ኦሪት ኢትቅትል ብእሴጻድቀወኀ ጥአ ኢታኅዩ፤ ጻድቅን ሰው አትግደል፤ ኀጥኡንም ከፍርድ አታድን፤ ትላለችና እኛስ ማንንም ልንገድል አልተፈቀደልንም፤ብለዋል (ዮሐ. ፲፰፥፳፰-፴፩)፡፡ ይኸውም መንፈስ ቅዱስ በሕጋችን ጻድቀ ባሕርይ ክርስቶስን መግደል አይገባንም ሙሉ በሙሉ ጥፋተኞች ነን፤ሲያሰኛቸው ነው፡፡ በኋላም እርሱ ሞቶ ዓለም ይድን ዘንድዳ ምድር መጥቷልና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያለ ጥፋቱ ሞት ተፈረደበት፡፡ ስለዚህም ገርፈው ሰቀሉት፡፡

ዓርብ ስቅለት | ተፈጸመ! | ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ ወጣን

ዓርብ ስቅለት የዕዳ ደብዳቤያችን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ለመጨረሻ ጊዜ የተደመሰሰበት፤ ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ የወጣንበት ዕለት ስለኾነ የድኅነት ቀንይባላል፡

👉 ጌታችን ሲሰቅል የሚከተሉት ሰባት ተአምራት ተፈጽመዋል፤

፩. ፀሐይ ጨለመ፤

. ጨረቃ ደም ኾነ፤

. ከዋክብት ረገፉ፤

. የቤተ መቅደስ መጋረጃ ተቀደደ፤

. አለቶች ተፈረካከሱ፤

. መቃብራት ተከፈቱ፤

. ሙታን ተነሡ (ማቴ. ፳፯፥፶፩፶፬)፡፡

👉 ጌታችን በመስቀል ላይ ሳለ የሚከተሉትን ሰባት ዐበይት ቃላት አሰምቶ ተናግሯል፤

. “ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ (አምላኪየ አምላኪየ ለምን ተውኸኝ?)”

. “እውነት እውነት እልሃለሁ፤ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትኖራለህ

. “አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁትምና ይቅር በላቸው

፬. እመቤታችንን “ሴትዮ ሆይ፣ እነሆ ልጅሽ”፤ ደቀ መዝሙሩንም “እናትህ እነኋት” በማለት የቃል ኪዳን እናትነትና ልጅነት ማከናወኑ፤

፭. “አባት ሆይ በአንተ እጅ ነፍሴን አደራ እሰጣለሁ”

. ተጠማሁ

፯. “ዅሉ ተፈጸመ (ማቴ. ፳፯፥፵፭-፵፮፤ ሉቃ. ፳፫፥፵፫-፵፮፤ ዮሐ. ፲፱፥፲-፴)፡፡

ከሰድስት ሰዓት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ጨለማ ኾኖ ከቈየ በኋላ ከዘጠኝ እስከ ማታ እንደ ተለመደው ብርሃን ሁኖአል፡፡ “ወፍና ሠርክ ይበርህ ብርሃነፀሐይእንዲል (ዘካ. ፲፬፥፯)፡፡ በዚህ ዕለት ሰባት መስተፃርራን (ጠበኞች) ታረቁ፤ ተስማሙ፡፡ እነዚህም፡- ሰውና እግዚአብሔር፣ ሰውና መላእክት፣ ሕዝብና አሕዛብ፣ ነፍስና ሥጋ ናቸው (ኤፌ. ፪፥፲፤ ቈላ. ፩፥፳)፡፡ ጌታችን ጠዋት በሦስት ሰዓት ተገረፈ፤ በስድስት ሰዓት ተሰቀለ (ማቴ. ፳፯፥፩-፴፯፤ ሉቃ. ፳፫፥፩-፵፬፤ ዮሐ. ፲፱፥፩)፡፡

ጌታችን በውኃው ተጠምቀን፣ ደሙን ተቀብለን የእግዚአብሔር ልጆች እንኾን ዘንድ ከቀኝ ጎድኑ ጥሩ ውኃ፣ ትኩስ ደም አፈሰሰልን (ዮሐ. ፲፱፥፴፬)፡፡ በዐሥራ አንድ ሰዓት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከመስቀል አውርደው ሽቶ እየረበረቡ በድርብ በፍታ ገንዘው ቀበሩት (ሉቃ. ፳፫፥፶-፶፬፤ ዮሐ. ፲፱፥፴፰-፵፪)፡፡ ነፍሱ ወደ ሲኦል ወርዳ ነፍሳትን ነጻ አወጣች (፩ኛ ጴጥ. ፫፥፲፱)፡፡ በዚህ ጊዜ በርሃነ መለኮቱ በሲኦል ተገለጠ፡፡ ስለዚህም “ንሴብሖለእግዚአብሔር እየተባለ ይዘመራል፡፡ ከሆሣዕና አንሥቶ ተከልክሎ የነበረው ኑዛዜ ይናዘዛል፤ ጸሎተ ፍትሐት ይደረጋል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

👉 ገብርኤል 👉 ማርያም 👉 ኡራኤል 👉 ጊዮርጊስ 👉 ተክለ ሐይማኖት 👉 ዮሴፍ 👉 መድኃኔ ዓለም

በዕለተ ሥቅለት በደመ ወልድ ዓለምን ለመቀደስ ከሁሉ ይልቅ የተሰየመው ቅዱስ ኡራኤል ነው።

ቅዱስ ኡራኤል

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

በፍጹም መጠበቅን ጠብቆ ለዚህ ያደረሰን አምላካችን ክብርና ምስጋን አምልኮትና ውዳሴ ይድረሰውና ይህን ታላቅ መልአክ በችሎታችን መጠን እንድናመሰግን እግዚአብሔር ይርዳን፤ አምላክ ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን፤ ምስጢሩን ይግለጥልን አሜን፡፡

ዑራኤል የተባለ መልአክ ሊረዳኝ መጣ፡፡” [/ዕዝ. ሱቱ. ]

በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል።

በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ

በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ። ይጠራኛል እመልስለትማለሁ፥ በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋራ እሆናለሁ፤ አድነዋለሁ አከብረውለሁ። ረጅምን ዕድሜ አጠግበዋለሁ፥ ማዳኔንም አሳየዋለሁ። መዝ. [/፺፩/፥፲፩፡፲፮]

አፈቅሮ ፈድፋደ፡ዑራኤል ሆይ፣ ከመልኮች ሁሉ ይልቅ ያንተን መልክአ ጸሎት እወዳለሁ፡፡ የመልክህ ስነ ጸዳል በደመ ወልድ እግዚአብሔር የታተመ ነውና፡፡

ዑራኤል ሆይ፣ እግዚአብሔር ሀይሉን የሚገልጽብን መልአከ ብርሃናት አንተ ነህ፡፡ በዕለተ ሥቅለት በደመ ወልድ ዓለምን ለመቀደስ ከሁሉ ይልቅ አንተ ተሰይመሃልና፡፡ ስለክብርህ የሰማይ መላእክት አደነቁ፡፡

ለተፈጥሮትከ፡

ዑራኤል ሆይ፡ያለ መናገር በጥንት አርምሞ ከነፋስና ከእሳት ለተፈጠረ ተፈጥሮህ ሰላም እላለሁ፡፡ ዑራኤል ሆይ የተፈጥሮና የይቅርታና የቸርነት ክቡር መልአክ ነህና ስለኛ ስለሰው ልጆች ወደ ልዑል እግዚአብሔር ማልድ አማላጅነትህ ዘወትር ከጥፋት ያድናልና፡፡

ለዝክረ ስምከ፡

ዑራኤል ሆይ፡ከማርና ከወተት ይልቅ ለሚጥመው ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ፡፡

ዑራኤል ሆይ፡ክፍልህ /ክንፍህ/ በደመ ወልድ እግዚአብሔር የተከበረ /የታለለ/ ነውና፡፡ ለዓለሙ ሁሉ መድሃኒት ትሆን ዘንድ ግሩም የሚሆን የእግዚአብሔር ሥልጣን በክብር ከፍ ከፍ አደረገ፡፡ (መልክአ ዑራኤል)

የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።” [መዝ.፴፫/፴፬/፥፯]የሊቀ መልአኩ የክዱስ ዑራኤል ረድኤቱ በረከቱ ፍጹም አማላጅነቱ ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡

ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣኝ፣ ካለማወቅ ወደ መረዳት ያደረሰኝ አነሳስቶ ላስጀመረኝ አስጀምሮ ላስፈጸመኝ ጥንት ላሌለው ቀዳማዊ ፍጻሜ ላሌለው ድህራዊ ያልኖረበት ጊዜ የሌለ የማይኖርበት ጊዜም የማይኖር የዘላለም ንጉስ ሁሉን ቻይ ፈጣሪ እግዚአብሔርን በራስ ፀጉሬ ቁትር በአጥንቶቼም ልክ አመሰግናለሁ፡፡

በሰማይ ያሉ መላእክት በምድርም የሚኖሩ የአዳም ዘር ሁሉ የሚያመሰግኗት በአማላጅነቷ ሁል ጊዜ የማትለየኝ ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበራ የብርሃን እናት የሁሉ እመቤት የአምላክ እናት ከተመረጡ የተመረጠች ከተለዩ የተለየች ከተከበሩ የተከበረች እናቴ እመቤቴ ድንግል ማርያም በቃላት ልገልጸው ከምችለው በላይ አመሰግናለሁ፡፡ ሌሊትና ቀን ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑና ሳይሰለቹ የሚጠብቁን ሊቀነ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ቅዱስ ገብርኤል ቅዱስ ሩፋኤል ቅዱስ ዑራኤል ቅዱስ ራጉኤል ቅዱስ ፋኑኤል እልፍ አእላፋት የሆኑ ጠባቂ መላእክት ሳመሰግን በደስታ ነው፡፡

በጸሎታቸው ያልተለዩኝን ጻድቃን አባቶቼን አቡነ ተክለሃይማኖትን አቡነ ገብረምንፈስ ቅዱስን አቡነ ሀብተማርያምን አቡነ አረጋዊን አቡነ ኪሮስንና ሌሎች ቅዱሳን አባቶቼን እንዲሁም እናቶቼን ቅድስት ክርስቶስ ሰምራን ቅድስት አርሴማን ብዙ ያልጠቀስኳቸው ቅዱሳንን ለማመስገን ቃላት የለኝም፡፡

በሰማኝትነታቸው የጥንካሬ ምሳሌ የሆኑልኝ በጸሎታቸው የረዱኝን ቅዱሳን ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስን ቅዱስ እስጢፋኖን መጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስንና ሌሎችን ቅዱሳን ሰማዕታትን ሁሉ በእጅጉ አመሰግናለሁ ለዘላለሙ አሜን፡፡

የተከዱትንና የተገፉትን የአክሱም ጽዮን ልጆችን፤ በፈተና፣ በመከራ፣ በድካምና በስቃይ ላይ ያሉትን ወገኖቻችንን ሁሉ ያለ ደዌና ያለ ከፋ ሕማም ለክርስቶስ ትንሣኤ ያድርሰልን ፤ ቀናተኞችና አረመኔዎች የሆኑትን እርጉም ጠላቶቻቸውን/ጠላቶቻችንን ሁሉ በቶሎ ያንበርክክልን!!! አሜን።

___________________________________

Posted in Ethiopia | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ዓርብ ስቅለት | ተፈጸመ! | ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ ወጣን

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 17, 2020

ዓርብ ስቅለት የዕዳ ደብዳቤያችን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ለመጨረሻ ጊዜ የተደመሰሰበት፤ ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ የወጣንበት ዕለት ስለኾነ ‹የድኅነት ቀን› ይባላል፡

👉 ጌታችን ሲሰቅል የሚከተሉት ሰባት ተአምራት ተፈጽመዋል

  • . ፀሐይ ጨለመ፤
  • . ጨረቃ ደም ኾነ፤
  • . ከዋክብት ረገፉ፤
  • . የቤተ መቅደስ መጋረጃ ተቀደደ፤
  • . አለቶች ተፈረካከሱ፤
  • . መቃብራት ተከፈቱ፤
  • . ሙታን ተነሡ (ማቴ. ፳፯፥፶፩፶፬)

👉 ጌታችን በመስቀል ላይ ሳለ የሚከተሉትን ሰባት ዐበይት ቃላት አሰምቶ ተናግሯል

  • . “ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ (አምላኪየ አምላኪየ ለምን ተውኸኝ?)”
  • . “እውነት እውነት እልሃለሁ፤ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትኖራለህ
  • . “አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁትምና ይቅር በላቸው
  • . እመቤታችንን ሴትዮ ሆይ፣ እነሆ ልጅሽ ደቀ መዝሙሩንም እናትህ እነኋትበማለት የቃል ኪዳን እናትነትና ልጅነት ማከናወኑ፤
  • . አባት ሆይ በአንተ እጅ ነፍሴን አደራ እሰጣለሁ
  • . ተጠማሁ
  • . ዅሉ ተፈጸመ (ማቴ. ፳፯፥፵፭፵፮፤ ሉቃ. ፳፫፥፵፫፵፮፤ ዮሐ. ፲፱፥፲)፡፡

+_______________________________+

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

ያስለቅሳል! ግን፡ ዓርብ ስቅለት ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ የወጣንበት ዕለት ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 25, 2019

ዓርብ ስቅለት (የድኅነት ቀን) የዕዳ ደብዳቤያችን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ለመጨረሻ ጊዜ የተደመሰሰበት፤ ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ የወጣንበት ዕለት

ጌታችን ሲሰቅልም የሚከተሉት ሰባት ተአምራት ተፈጽመዋል

. ፀሐይ ጨለመ፤

. ጨረቃ ደም ኾነ፤

. ከዋክብት ረገፉ፤

. የቤተ መቅደስ መጋረጃ ተቀደደ፤

. አለቶች ተፈረካከሱ፤

. መቃብራት ተከፈቱ፤

. ሙታን ተነሡ (ማቴ. ፳፯፥፶፩፶፬)፡፡

ጌታችን በመስቀል ላይ ሳለ የሚከተሉትን ሰባት ዐበይት ቃላት አሰምቶ ተናግሯል፤

. ‹‹ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ (አምላኪየ አምላኪየ ለምን ተውኸኝ?)››

. ‹‹እውነት እውነት እልሃለሁ፤ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትኖራለህ››፤

. ‹‹አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁትምና ይቅር በላቸው››፤

. እመቤታችንን ‹‹ሴትዮ ሆይ፣ እነሆ ልጅሽ››፤ ደቀ መዝሙሩንም ‹‹እናትህ እነኋት›› በማለት የቃል ኪዳን እናትነትና ልጅነት ማከናወኑ፤

. ‹‹አባት ሆይ በአንተ እጅ ነፍሴን አደራ እሰጣለሁ››

. ‹‹ተጠማሁ››፤

. ‹‹ዅሉ ተፈጸመ›› (ማቴ. ፳፯፥፵፭፵፮፤ ሉቃ. ፳፫፥፵፫፵፮፤ ዮሐ. ፲፱፥፲)፡፡

__________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሰን | Happy Epiphany

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 16, 2017

ምሥጢረ ጥምቀት

ጥምቀት፡ማለት ‹‹አጥመቀ›› ከሚለው የግእዝ ግሥ የወጣ ሲሆ ትርጉሙም ማጥመቅ ፣ መጠመቅ ማለት ነው፡፡ ይኸውም ከራስ ፀጉር እስደ እግር ጥፍር ድረስ በተጸለየበት ውሃ /ማየ ሕይወት ወይም ማየ ገንቦ/ ውስጥ በሥላሴ ስም መጥለቅ መዘፈቅ ማለት ነው፡፡ ምሥጢረ ጥምቀት ሌሎች ምሥጢራትን ለመፈጸም የመግቢያ በር ነው፡፡ ወደ ሐዲስ ኪዳን ጥምቀት ከመሔዳችን በፊት ጥምቀት በብሉይ ኪዳን ምን እንደሚመስል እንመልከት::

ጥምቀት በብሉይ ኪዳን

በብሉይ ኪዳን ጥምቀት በውሃ በታጠብ ፣ መጥለቅና መንፃት ነበር፡፡ በብሉይ ኪዳን በዓል ሲከበር በዓሉን ለማክበር የሚሰበሰበው ሕዝብ በሙሉ በውሃ በመረጨት ለበዓሉ ዝግጅት የሚፈልጉ ዕቃዎችን ሁሉ በውሃ መታጠብና መንፃት ነበረባቸው፡፡ ዘሌ 627

በብሉይ ኪዳን ሰውን ወይም ዕቃን ያረክሳሱ ተብሎ የሚታመንባቸው ነገሮች ነበሩ ለምሳሌ፡ለመሥዋዕት የታረደችውን ጊደር ደም በጣቱ የነካ የዝግባ እንጨትና ግምጃ ወስዶ የጊደሪቱን ሥጋና አጥንት ለሚቃጠልበት የጣለ ካህን ልብሱንና ገላውን በውሃ ካልታጠበ ወደ ሰፈር መግባት አይፈቀድለትም ነበር፡፡ የሞተ ሰው አስከሬን የነካ በሞተበተ ድንኳን ውስጥ የገባ ሁሉ እንደርኩስ የቆጠር ስለነበር በውሃ መታጠብና መንፃት የተለመደ ሕግ ነበር፡፡ ዘፀ 1918 ፣ መዝ 5051፡፡ ከብሉይ ኪዳን ውጭ የነበረ ሰው የኦሪቱን አምነት ሲቀበል ከማኅበረ አይሁድ ከመግባቱ በፊት መገረዝና መታጠብ ገድ ነበር፡፡ ከተገረዘና ከታጠበ በኋላ እንደ አይሁድ ሥርዓት መባዕ ማቅረብና ከማኅበሩ ጋር አንድ መሆን ይፈቀድለታል፡፡ ከሌላው እምነት ወከ ይሁዳነት ሊገባም ዕለት እንደተወለደ ሕፃን ይቆጠር እንደነበር መጻሕፍት ይነግሩናል፡፡ እራሱን ከኢግዙርነት መለየት ከመቃብር እንደመውጣት ነው ተብሎም ፈይታመን ነበር፡፡

ሌላው የብሉይ ኪዳን ጥምቀት የዮሐንስ ጥምቀት ነው፡፡ የሐንስ የንስሐ ጥምቀትን ያጠምቅ ነበር፡፡ ማር 14 የዮሐንስ ጥምቀት አማኞችን ለክርሰቶስ ጥምቀት የሚያዘጋጅ የክርስቶስን ጥምቀት ለመቀበልና በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ ባለቤት ለመሆ የሚያበቃ ነበር፡፡ ሜቴ 311 የሚያጠምቅበትም ዓለማ ሰዎችን ከኃጢአት ወደ ሥርየት ከአምልከኮተ ጣኦት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መመለስና ሥርየተ ኃጢአት አግኝቶ ከማሕበረ ጻድቃን ጋር አንድ መሆንን ያሳያል፡፡ በብሉይ ኪዳን ይፈጸም የነበረው ጥምቀት ምንም እንኳን ምሳሌነት ቢኖረውም በሐዲስ ኪዳን እንደሚፈጸመው ጥምቀት ምሥጢር አልነበረም፡፡ የብሉይ ኪዳን ጥምቀት ፈየመንጻት ጥምቀት ነበር እንጂ፡፡

ዮሐ 26

የጥምቀት ምሳሌ በብሉይ ኪዳን

ስለ ጥምቀት አስቀድሞ በብሉይ ኪዳን ብዙ ምሳሌ ተመስሏለወ ትንቢትም ተነግሯል፡፡ ከምሳሌዎቹም ጥቂቶቹን ስንመለከት፡

1ኛ የኖህ መርከብ ዘፍ 717 1ኛ ጴጥ 320 መርከቧ የጥምቀት ምሳሌ ስትሆን በመርከቧ ተጠልለው የዳኑት ሰዎች የአማንያን ምሳሌ በንፍር ውሃ የጠፉት የኢአማንያን ምሳሌ ናቸው፡፡ በመርከብ ውስጥ የነበሩት እንደዳኑ በጥምቀት አምነው የተጠመቁ ሁሉ ከሲኦል ባህር ከመስጠም ሲድኑ ከመርከቧ ውጭ የነበሩት ሰጥመው እንደጠፉ በጥምቀት ባለማመን ጸንተው ያልተጠመቁም በሲኦል ባህር ሰጥመው ይቀራሉ፡፡

2ኛ ግዝረት፡ዘፍ 1714 ግዝረት የተገረዙ ሁሉ የአብርሃም ልጆች ይባሉ እንደነበር ያለተገረዙ ሁሉ ደግሞ ከአብርሃም ልጅነት የወጡ ነበር፡፡ አሁንም የተጠመቀ ሁሉ የእግዚአብሔር ልጅ በመባል ሲኖር ያልተጠመቀ ደግሞ ከእግዚአብሔር ልጅነት ይለያሉና ግዝረት ለጥምቀት ምሳሌ ሆነ፡፡

3ኛ እስራኤላውያን ባህረ ኤርትራን መሻገራቸው፡እስራኤላውያኑ የክርስቲያኖች ምሳሌ ግብፃውያን የአጋንንት ምሳሌ ባህረ ኤርትራን መሻገራቸው የጥምቀት ምሳሌ ነው፡፡ እስራኤላውያን በግዞት ከነበሩበት ከግብጽ ባርነት ነፃ የወጡት ባህረ ኤርትራን ከተሻገሩ በኋላ ነው፡፡ ባህረ ኤርትራ ለፈርኦንና ለሠራዊቱ ሞትን ሲያስከትል ለእስራኤላውያን ግን ሕይወት ፣ ደስታንና ነፃነትን አጎናጽፏቸዋል፡፡ ክርስቲያኖችም በጥምቀት በርኩሳን አጋንንት ከመገዛት ከዘለዓለም ሞት ነፃ ወጥተዋል የኤርትራን ባህር ለፈርኦንና ለሠራዊቱ ድል መንሻ እንደሆነ በጥምቀትም አጋንንት ድል ሆነዋል፡፡

4ኛ እስራኤላውያን በኢያሱ መሪነት ፈለገ ዮርዳኖስን መሻገራቸው ኢያሱ 41-9 እስራኤላውያን ዮርዳኖስን ተሸግረው ከነአን እንደገቡ ክርስቲያኖችም ተጠምቀው ወደ እርሳቸው ገነት መንግሥተ ሰማያት ይገባሉና፡፡

5ኛ አብርሃም ፈለገ ዮርዳኖስን ተሸግሮ ከመልከጼዴቅ ኅብስተ አኮቴት ጽዋዓ በረከት መቀበሉ ዘፍ 1417

አብርሃም የምእመናን ምሳሌ

መልከጼዴቅ የክርሰቶስ /የካህናት/ ምሳሌ

ሕብስተ አኮቴት ጽዋዓ በረከት የክርስቶስ ሥጋወደም ምሳሌ

ዮርዳኖስ የጥምቀት ምሳሌ

አብርሃም ዮረዳኖስን ከተሻገረ በኋላ ህብስተ አኮቴት ጽዋዕ በረከት እንደተቀበለ እኛም ከተጠመቅን በኋላ የጌታን ሥጋና ደም እንቀበላለንና፡፡

የጥምቀት ትንቢት በብሉይ ኪዳን

1ኛ ‹‹ጥሩ ውሃ እረጫችኋለሁ እናንተም ትጠራላችሁ›› ሕዝ 3625 ጥሩ ውሃ የተባለው የምንጠመቅበት ውሃ ነው፡፡ በንፁህ ውሃ የታጠበ ነገር ደዕድፈቱ እነደሚጠራ ሰውም አምኖ ሲጠመቅ ኃጢአቱ ይሠረይለታልና፡፡ ሌላው

2ኛ ‹‹ምህረትን ፈየወዳልና… ኃጢአታችንንም በባህር ጥልቅ ይጥለዋል›› ሚክ 719 በጥልቅ ባህር የተመሰለው ጥምቀት ነው፡፡ በባህር ውስጥ የገባ ፍፁም እንደማይታይ በጥምቀትም የተሠረየ ኃጢአት ፈጽሞ አያስቀጣም በፍዳ አያሲይዝምና አንድም ከባህር ውስጥ በክንፋቸው የሚበሩ በእግራቸው የሚሄዱ በደረታቸው የሚሳቡ ተገኝገዋል፡፡

በጥምቀትም አንድ ልጅነት አግኝተው በመንፈስቅዱስ የጸጋ ስጦታዎች አማካኝነት ለተለያ ደረጃዎች በቅተዋልና፡በክንፍ የሚበሩ የሰማዕታት ምሳሌ ፣ በእግራቸው የሚራመዱ በገዳም ተወስነው የሚኖሩ መነኮሳት ምሳሌ ፣ በደረታቸው የሚሳቡ ደግሞ በዓለም በሕግ የሚኖሩ የክርስቲያኖች ምሳሌ ናቸው፡፡

ጥምቀት ለምን ምሥጢር ተባለ?

ጥምቀት ምስጢር የተባለበት ምክንያት ከላይ እንደጠቀስነው በሚታይና በሚሰማ አገልግሎት የማይታይ ረቂቅ ጸጋ ስለሚሰጥበትና ላመኑት ብቻ የሚፈጸም በመሆኑ ውሃው ተለውጦ ከጌታ ጎን የወጣውን ውሃ /ማየ ገቦ/ ሲሆን የምንጠመቅበት ገንዳ ከግሞ ማኅጸነ ዮርዳኖስ ሲሆን አለመታየቱ ከመምህር ተምሮ በልቡና በማመን የሚታወቅ በመሆኑ አንድም እግዚአብሔር የገለጠልንን ያህል ካሆነ በስተቀር ስለማነውቀው ምሥጢር ተባለ፡፡

የጥምቀት አስፈላጊነት /ጥቅም/

ድህነት እናገኛለን፡ማር1616 ‹‹ያመነ የተጠመቀ ይድናል ያላመነ ግን ይፈረድበታል›› ይላል፡፡ ይህን ይይዙና ‹‹ያላመነ›› እንጂ ‹‹ያልተጠመቀ›› ይፈረድበታል አይልም ስለዚህ አለማመን አንጂ አለመጠመቅ አያስፈርድም ይላሉ፡፡ ይህ ግን አይደለም ባይጻፍም በውስጡ ‹‹ያልተጠመቀ›› የሚለው ቃል እንዳለ እናስተውል፡፡ ምክንያቱም ከፊት ያድናል ያለው ያመነ ብቻ ሳይሆን የተጠመቀም ነው የሚለው፡፡ ታዲያ ያመነና የተጠመቀ ከዳነ የማይድነው ወይም የሚፈረድበት ደግሞ ፈያላመነና ያለተጠመቀው ጭምር መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ዮሐ 101 ፣ ዮሐ 139 ስለዚህ ግድ ለመዳን ማመን ብቻ አይጠቅምም መጠመቅም ያሻል፡፡

ከውሃና ከመንፈስ ዳግመኛ እንወለዳለንጌታችን ምስጢረ ጥምቀትን በትምህርት ለኒቆዲሞስ በሥጋ ከወላጆቻችን እንደተወለድን ሁሉ ‹‹ከውሃና ከመንፈስ ዳግም ልትወለዱ ግድ አላችሁ›› ብሎ አስረድቶታል፡፡ ዮሐ 33 የሐነስ መጥምቅም ፈሪሳውያንን እና ሰዱቃውያንን ደገሰጻቸው በኋላ ‹‹እኔ የንስሐ ጥምቀት አጠምቃችኋለሁ የጫማውን ጠፈር ልፈታ የማይገባኝ ከኔ በኋላ የሚመጣው ግን እርሱ በመንፈስ ቀዱስ አሳትነት ያጠምቃችኋል፡፡›› ብሎ ግልጽ ቃል ተናግሯል፡፡ ሜቴ 311 ለዚህ ነው በመንፈስ ቅዱስ ዳግም ከእግዚአብሔር እንወለዳለን ያልነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ለመንፈስ ልጁ ለቲቶ ‹‹የመድኃቲታችን የእግዚእብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ እንደምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆን መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን›› ቲቶ35 ብሎ ድንቅ ቃል ተናግሯል፡፡ ከዚህ በኋላ የእግዚአብሔር ልጆች እንባላለን፡፡ እናንተን ግን ልጆቼ ብያችኋለሁ ባሮች አይደላችሁም እንዳለ ለነቢያት ያልታደለ የልጅነት ክብር በጥምቀት እናገኛለን፡፡

ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ሞቱን በሚመስል ሞት ሞተን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ እንነሳለን፡ይህ ከጌታችን ጋር በጥምቀት ከሞቱና ከትንሣኤው ጋር እንሳተፋለን ማለት ነው፡፡ ሞቱን በሚመስል ሞት እሞታለን ሲል ጌታችን አንድ ጊዜ ሞቶ ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው እንደለየ እኛም በጥምቀት ከኃጢአት እንለያለን ማለት ነው፡፡

የኃጢአት ሥርየት እናገኝበታለን፡ከጥምቀት በፊት ያለ ኃጢአት በጥምቀት ከጥምቀት በኋላ ያለ ኃጢአት ደግሞ በሥጋወደሙ እንደሚሠሬ ተጽፏል፡፡ በዚህም ሰው ከኃጢአት በመለየቱ በጸጋም ከእግዚአብሔር በመወለዱ የመንግሥተ ሰማይ ወራሽ ይሆናል፡፡ ሕዝ 3625 ሐዋርያትም ‹‹ኃጢአታችሁ ይሠረይ ዘንድ ንሥሐ ግቡ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ስም ተጠመቁ›› ሐዋ 238 በማለት አስተምረዋል፡፡ ከእነርሱ በኋላ የተነሱት ሠለስቱ ምዕትም ኃጢአት በሚሠረይባት በአንዲት ጥምቀት እናምናለን ብለው በጸሎት ሃይማኖት ጽፈውልናል፡፡

በጥምቀት የቤተክርስቲያን አባል እንሆናለን፡በዘመነ ኦሪት የእግዚአብሔር ሕዝብ የአብርሃም ልጆች ለመባል ግዝረት ሃይማኖታዊ ግዴታ ነበር፡፡ ጥምቀትም በክርስቶስ ለሚያምኑ ሁሉ ከቅድስት ቤተክርስቲያ የሚገኝ ጸጋ ተካፋይ ከማድረጉም በላይ ራሱን ተጠማቂውን የእግዚአብሔር ልጅ ያሰኘዋል፡፡ ቆላ 211 በዚህ የክርስቶስ ቤተሰቦች የቤተክርስቲያን አባል እንሆናለን፡፡

የጥምቀት አመሰራረት በሐዲስ ኪዳን

ጥምቀት በሐዲስ ኪዳን የመሠረተው የሁሉ መሠረትና መሥራች የሆነው ጌታችንና አምላካችን መክኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ሲመሠርተውም በ3 መልኩ ነው፡፡

. በትምህርት፡ለኒቆዲሞስ በማስተማር ዮሐ 35

. በትእዛዝ፡ሐዋርያትን መርጦ ካጸናቸው በኋላ እርሱ ወደ ሰማይ እንዳረገ ዓለምን ዞረው ወንጌልን እንዲሰብኩ አሕዛብንና ያላመኑትን ሁሉ ‹‹በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ደቀ መዛሙርቴ አድርጉ›› ብሎ በማቴ 2819 በማዘዝ መሥርቶታል፡፡

. በተግባር፡እኛ ክርስቲያኖች ራሱ አምላክ ከኃጢአት በቀር ሳያደርገው ለኛ ለልጆቹ አድርጉ ያለን አንዳች ነገር የለም፡፡ ተጠምቆ ተጠመቁ ፣ ጹሞ ጹሙ ፣ መከራ ተቀብሎ መከራ ተቀበሉ፡፡ ስለዚህ ጥምቀቱንም በ30 ዘመኑ በእደ ዮሐንስ በባሕረ ዮርዳኖስ ተጠምቆ በተግባር መሥርቶአልና፡፡

በምሥጢረ ጥምቀት ሙሉ ጸጋ የተሰጠው ግን በበዓለ ሃምሳ ለሐዋርያት በጽርሐ ጽዮን የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ መውረድ በኋላ ነው፡፡

የጌታ ጥምቀት

ጌታ መቼ ተጠመቀ?

ከእመቤታችን በተወለደ በ30 ዘመኑ በዘመነ ሉቃስ ጥር 11ቀን ማክሰኞ ሌሊት 10 ሰዓት፡፡

ጌታችን ለምን ተጠመቀ?

እንደምናውቀው ጌታችን በዘመነ ሥጋዌው ከሠራቸው ብዙ ሥራዎች አንዱ መጠመቅ ነው፡፡ በወንጌል ትርጓሜም ‹‹ወሖሮን እግዚእ ለኃምስ ግብራት›› ማለት ጌታችን አምስቱን ሥራዎች ሄዶባቸው ወይም ሠራቸው ይላል፡፡ እነዚህ ጥምቀት ፣ ተአምኖ ኃትውእ /ኃጢአትን ማመን/ ይህ ከኃጢአተኞች ጋር መቆጠሩ እንጂ እርሱ ኃጢአት የለበትም ፣ ከዊነ ሰማዕት ሰማዕት /ምስክር/ መሆን ብሎ ስለእውነት ሲመሰክር እንደመጣ እራሱ ተናግሯል ፣ ተባሕትዎ መጾሙ ፣ ምንኩስና በድንግልና መኖሩን፡፡ እነዚህን ሁሉ ፈጽሟል፡፡ ታዲያ ጌታ ለምን ተጠመቀ? ስንል 3 ዐበይት ነጥቦችን እናያለን፡፡

1. ለትሕትና፡– ‹‹ከእኔ ተማሩ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና›› እንዳለ በማቴ 1129 ለአርአያ /ለትምህርት/ እንዲሆነን ብሎ ተጠመቀ፡፡ ዮሐ 131-7

ምንጭ

__

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: