Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ’

ጥር ፬ እንኳን ለወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ በአል አደረሰን

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 12, 2018

ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ

በዚህች ቀን ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ሞትን ሳይቀምስ የተሰወረበት ቀን ነው፤ ዮሐ 21 20

ዮሐንስ ወንጌላዊ

ዮሐንስ ማለት ‹‹ የእግዚአንሔር ጸጋ ነዉ››፤ደስታ ማለት ነዉ፡፡አባቱ ዘብዴዮስ ፤ እናቱ ማርያም ባዉፍልያ ትባላለች፡፡ቁጥሩ ከዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት የሆነ ያዕቆብ የተባለ ወንድም ነበረዉ፡፡ ማቴ 421 ፤ ማር 120 ፤ማቴ 2020 ቅዱስ ዮሐንስ አስቀድሞ የዮሐንስ መጥምቅም ደቀ መዝሙር ነበር፡፡ ዮሐ 135 ቅዱስ ዮሐንስ ከአባቱና ከወንድሙ ጋር ዓሣ በሚያጠምድበት በገሊላ ባህር ላይ መረቡን ሲያበጅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያነት ጠራዉ፡፡ እሱም አባቱን ሌሎቹንና ታንኳን ትቶ ከወንድሙ ያዕቆብ ጋር ጌታን ተከተለዉ፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ ብዙ ስሞች አሉት

  1. ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
  2. ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ
  3. ዮሐንስ ቁጽረ ገጽ
  4. ዮሐንስ ታኦሎጎስ
  5. ዮሐንስ አቡቀለምሲስ
  6. ዮሐንስ ወንጌላዊ
  7. ዮሐንስ ዘንስ

ከሐዋርያት መካከል ሞትን ያልቀመሰ በህይወተ ሥጋ እያለ ወደ ሰማይ የተነጠቀ እንደ ሔኖክ ፣እንደ ኤልያስ በብሔረ ሕያዋን የሚኖር ሐዋርያ ነዉ፡፡ጌታችንም ለቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹‹‹ዮሐንስ እኔ እስክመጣ ድረስ በሕይወት ይኖር ዘንድ ብወድስ ምን አግዶህ??›››ዮሐ 2120 ይህም እስከ ምጽአት ድረስ እንደሚኖር መናገሩ ነዉ፡፡በማቴ 1618 ላይ ‹‹እዉነት….……ሞትን የማይቀምሱ አንዳንድ አሉ›››››ያለዉ ቃል ለቅዱስ ዮሐንስና መሰሎቹ የተነገረ ቃል ነዉ፡፡

የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በረከቱ ረድኤቱ ከሁላችን ጋር ይሁን፡ ራዕዩ ይገለጥልን!

______

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: