Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • May 2023
    M T W T F S S
    1234567
    891011121314
    15161718192021
    22232425262728
    293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ያሬድ ዲባባ’

የኢትዮጵያን ስም ለመጥራት የተናነቀው “ኦሮሞ” ጀርመን ጋዜጠኛ | ጀርመንኛ “ኬኛ ነው”፤ ከኦሮሚያ ነው የፈለሰው” ይላል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 15, 2019

ወቸውጉድ! አንድ ቀን ጀርመን የኛ ናት፤ ልዩ ጥቅም ይገባናል ማለታቸው አይቀርም። “ፅጌረዳውም፣ ቡናውም፣ ቋንቋውም፣ የላቲን ፊደሉም” ኬኛ….

በዘረኝነት ጋኔን የተለከፈው ወንድማችን ያሬድ ዲባባ ይባላል፤ በ አስራ ሁለት ዓመት እድሜው ነው ጀርመን የገባው። በሰሜን ጀርመን (ብሬመን + ሃምቡርግ) ለሚገኝ የቴሌቪዥን እና ራዲዮ ጣቢያዎች በጋዜጠኝነት ዝናን ያተረፈ ነው፤ አብዛኛዎቹ ጀርመኖች የማይናገሩትን የሰሜን ጀርመን ቀበሌኛ/ዲያሌክት (ፕላት ጀርመን፤ ለእንግሊዝኛ እና ሆላንድኛ ይቀርባል) አቀላጥፎ ይናገራል። በቋንቋ ችሎታው አደንቀዋለሁ (እኔ እራሴ በሰባት የተለያዩ ሕዝቦች መካከል የኖርኩና ቋንቋዎቻቸውንም በሚገባ የምናገር “ኩሩ ኢትዮጵያዊ” ነኝ፤ የእርሱን ያህል ግን አልሆንም)፤ ያሬድ እንግሊዝኛውንም ሰምቼዋለሁ ጥርት ያለ እንግሊዝኛ ነው የሚናገረው። ነገር ግን፡ እንዲሁ በቀላሉ የተገኘ ስጦታ አይደለም፤ ብዙ ተከፍሎበታል፤ ነፍስ ተሽጧል፤ ስለዚህ ያሬድ ዲባባ ማንነቱን የሸጠና እናት ኢትዮጵያን የካደ ደካማ ዘረኛ ነው።

[የማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ ፰፥፴፮]

ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?

ፕሮቴስታንት ጀርመኖች ኢትዮጵያን ለመበታተን ባላቸው የረጅም ጊዜ ህልም እንደ ያሬድ ያሉትን ሞኞች ይጠቀሙባቸዋል። ከአንድ ከስድስት ዓመት በፊት ያሬድ ዲባባና ደነነሽ ዘውዴ (በጀርመን ቴሌቪዥን ድራማዎችን በመሥራት የምትታወቅ ኢትዮጵያዊት ናት) በተመሳሳይ ፕሮግራም ላይ አቅርበዋቸው በጎሳ ሲያባሏቸው ነበር፤ ሆን ብለው ነበር ያን ፕሮግራም ያዘጋጁት።

የመናፍቁ የማርቲን ሉተር ፕሮቴስታንት ጀርመን በአምስት መቶ አመት ውስጥ ክርስትናን አጥፍታ ወደ ጣዖት አምልኮት በመመለስ ላይ ነች። የክርስቶስ ተከታዮች የሆኑት ምናልባት አስር በመቶ አይሆኑም፤ ግን በግዛቷ የቀሩት ጥሩ ሰዎች እነርሱ ብቻ ናቸው፤ ከአገራችን ጋር ግን ግኑኝነት የላቸው፤ ወደ አገራችን የሚገቡት ግን ልክ “ወንጌላዊ” ነኝ በማለት ወደ ኢትዮጵያ ተጉዞ እደየነበረው ጀርመናዊው ዮኻን ክራፕፍ ዓይነት ሰዎች ናቸው። ይህ ሰው ከመቶ አመታት በፊት ኦሮሚያ የተባለውን ግዛት ለመመሥረት የተነሳሳ፣ የኢትዮጵያን ቀጥተኛ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ለመዋጋት የዘመተ እርኩስ የክርስቶስ ተቃዋሚ ሰው ነበር።

“ኦሮሚያመርዝ ነው!!!

እውነቱን ትተው ውሸቱን፤ ሰፊውን ጠልተው ጠባቡን፣ የሚያኮራውን ንቀው የሚያቀለውን፣ የሚያስከብረውን አውግዘው የሚያዋርደውን፣ ግዕዝን ትተው ላቲኑን፣ የማርያም መቀነትን ትተው የዘንዶ ቀበቶን፣ ክርስቶስን ትተው ዲያብሎስን፣ እግዚአብሔርን ትተው ዋቄዮን፣ ተዋሕዶን ትተው አምልኮ ጣዖትን፣ ኢትዮጵያን ትተው ኦሮሚያን መርጠዋል። በዚህም በቅርቡ ክፉኛ ይቀጣሉ። መዳን የሚፈልጉ ዋቄዮ አላህን ትተውና ንስሃ ገብተው ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር ቶሎ ቢሰለፉ ይሻላቸዋል።

_______:_›_____

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: