Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘የግብጽ መቅሰፍቶች’

ህዝቤን ልቀቅ | ታይቶ የማይታወቅ የአንበጣ መንጋ ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ አምርቷል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 14, 2020

ባለፈው ሳምንት ሐምራዊቷን የፋሲካ ጨረቃ አይተናታልአሁን ደግሞ እየመጣ ያለውን እንከታተል…”ምስጋና ለኮሮና ፥ አንበጣ ይምጣ!” የምንልበት ዘመን ላይ ደርሰናል። ከጠላቶቻችን ውድቀት ይልቅ የፍትሕ አምላክ እግዚአብሔር የሚሰጠው መልስ በይበልጥ ያስደስታል።

  • ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን አግተህ ያንተ ልጆች ብቻ ሊማሩ?
  • ኢትዮጵያውያንን አስርበህ ያንተ ልጆች ብቻ ሊመገቡ?

ፋሲካን ለመጀመሪያ ጊዜ የጀመሩት የእስራኤል ልጆች ናቸው ። በዓሉንም ማክበር የጀመሩት ከግብጽ ነው።

ኦሪት ዘጸአት ምዕራፍ ፲፪

እግዚአብሔር በግብጻዊን ምክንያት በእስራኤላዊያን ላይ ሲደርሱ የነበሩ በርካታ ችግሮችን :- ጡብ መስራት ግርፋት መጨረሻ ላይም የእስራኤል ሴቶች የሚወልዷቸው ህጻናት ወንዶች ከሆኑ እንዲገደሉ ልምድ አዋላጆችን አሰልጥኖ ማሰማራትይህ ሁሉ ግፍ ሲደርስባቸው እስራኤል ወደ እግዚአብሔር ጮሁ እግዚአብሔርም ጩኸታቸውን ሰምቶ ሙሴንና አሮንን ያመልከኝ ዘንድ ህዝቤን ልቀቅየሚል መልዕክት አስይዞ ወደ ንጉሥ ፈርኦን ላካቸው። ፈርኦን ግን ልቡ ደንዳና ስለነበረ እግዚአብሔር ማነው? ህዝቡንም አልለቅቅም አለ ይልቁንስ በእስራኤል ላይ የባሰ ጫና መፍጠር ጀመረ :-ትናንት ጡብ እንዲሰሩ ገለባ ይሰጣቸው ነበር አሁን ግን ገለባውን ራሳቸው ከየትም እንዲያመጡ የጡቡ ቁጥር ግን ከትናንቱ እንዳያንስ ተወሰነባቸው ። ከዚህም የተነሳ እስራኤል አሁንም ይጮሃሉ ።

በዚህም ምክኒያት እግዚአብሔር በግብጽ ላይ መቅሰፍት ማውረድ ጀመረ።

መቅሰፍቶችም:-

  • .የሙሴ በትር እባብ መሆን ዘጸአት ፯፥፰፡፲፫
  • .የደም መቅሰፍት (የግብጽ ወሃ ሁሉ ወደ ደም መቀየር) ዘጸአት ፯፥፳፡፳፰
  • .የጓጉንቸር መቅሰፍት ዘጸአት ፰፥፩፡፲፭
  • .የተባይ (የቅማል)መቅሰፍት ዘጸአት ፰፥፲፮፡፲፱
  • .የዝንብ መቅሰፍት ዘጸአት ፰፥፳፡፴፪
  • .የእንስሳት እልቂት ዘጸአት ፱፥፩፡፯
  • .የእባጭ(ቁስል) መቅሰፍት በሰውና በእንስሳት ላይ ዘጸአት ፱፥፰፡፲፪
  • .የበረዶ መቅሰፍት ዘጸአት ፱፥፲፫፡፴፭
  • .የአንበጣ መንጋ መቅሰፍት ዘጸአት ፲፥፩፡፳
  • . የጨለማ መቅሰፍት ዘጸአት ፲፥፳፩፡፳፱

ይህ ሁሉ ሲሆን ፈርኦን እስራኤልን አልለቅቅም አለ። ስለዚህ አሁን የቀረውና የመጨረሻው የፋሲካን በዓል ማክበር ነው።

ላይ እንደተጠቀሰው የእስራኤል ልጆች ፋሲካን የጀመሩት በግብጽ ሳሉ ነው።

በእነሱ የዘመን አቆጣጠር በመጀመሪያ ወር ወሩም በገባ በ10ኛ ቀን ጸሐይ ስትጠልቅ በግ ወይም ፍየል እንዲያርዱ የሚታረደው በግ ወይም ፍየል ምንም አይነት ነውር የሌለበት ሆኖ ከታረደ በኋላ ደሙ ከስጋው የሚበሉትን ሰዎች ቤት ጉበኑንና መቃኑን እንዲቀቡት ከዚያም የበጉ ወይም የፍየሉ ስጋ ተጠብሶ በዚያች ሌሊት ከመራራ ቅጠልና ካልቦካ ቂጣ ጋር እንዲበሉት ሲበሉም በአጭር ታጥቀው ጫማቸውን አድርገው በትራቸውን ይዘው በጥድፊያ እንዲበሉ ምክኒያቱም አሁን በግብጽ ላይ የሚመጣው መቅሰፍት እጅግ ከባድ (የበጉ ወይም የፍየሉ ደም በቤታቸው ጉበንና መቃን ላይ የቀቡ እስራእል ብቻ ስለሆኑ ቢያች ሌሊት እግዚአብሔር በከተማ ውስጥ እያለፈ ደሙን በጉበኑና በመቃኑ ላይ ያልተቀባ ቤት ሲያገኝ በእያንዳንዱ ቤት ከሰው እስከ እንስሳ በኩር የተባለውን በሙሉ ስለሚገድል) ግብጾች በራሳቸው ጊዜ ወጡልን ስለሚሏቸው ነው ።

ከዚህ በኋላ ለእስራኤል ፋሲካን ማክበር የዘላለም ስርዓት እንዲሆን ተደነገገ። በመጀመሪያ እርሾ የተባለ ከቤታቸው ያወጣሉ ለሰባት ቀን ያልቦካ ቂጣ ይበላሉ።

ሰሞኑን በመላው ዓለም እርሾ ከገበያ መጥፋቱን ልብ ብለናል?! ለምን እርሾ?

__________________________

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

“ናግራን” ሳውዲ አረቢያ በአንበጣ መንጋ ተወረረች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 2, 2019

ሰማዕታተ ናግራን

ከኢትዮጵያ (ኤርትራ + ሱዳን) አካባቢ የተነሳው የአንበጣ መንጋ በሳውዲ እና የመን መዋሰኛ የምትገኘውን የናግራን ከተማ ወርሯል። በ፮ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ (የአክሱም) መንግሥት

ቀይ ባሕርን ተሻግሮ እስከ ደቡብ ዓረብ (የመን) ድረስ ግዛቱን አስፍቶ እንደነበር የሚታወቅ ነው። ከ495-525 .. የነገሠው የሀገራችን ንጉሥ አጼ ካሌብ በየመን (ናግራን/Najran) አካባቢ የሚገኙ ክርስቲያኖች፡ ድሁ ንዋስ (ፊንሐስ) በተባለ አይሁዳዊ ከደረሰባቸው ጥቃት ለመከላከል መቶ ሃያ ሺህ ሠራዊት በ፷ መርከቦች አዝምቶ ከጥቃት ታድጓቸዋል።

ለሰማዕታቱም መታሰቢያ ይሆን ዘንድ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የሐዋርያነት ታሪክ በዐረቢያ ምድር የመጀመሪያው ድንቅ ቤተ ክርስቲያን ከ1400 ዓመታት በፊት በዚሁ በናግራን ታንጾ ነበር፤ ይህም የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ነበር። ነገር ግን እርኩሱ መሀመድ (በገሃነም እሳት ይቃጠል) 622 .ም ጀምሮ በዲያብሎሳዊው ጂሃዱ እና “ሁለት ሃይማኖቶች በአረቢያ ጎን ለጎን መኖር የለባቸውም” በሚል መርሆው እዚያ የነበሩትን ተዋሕዶ ክርስቲያኖችን (ደካማ በነበረበት ዘመን መጠለያ ሰጥተውት የነበሩትን) በመጨፍጨፍ ቤተክርስቲያናቸውን አፈራርሶባቸዋል። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ዛሬ ሳውዲ አረቢያ ተብሎ በሚጠራው ሃገር በምትገኘዋ በናግራን ከተማ ክርስቲያኖች አይኖሩም።

የመጀመሪያ ማሰንቀቂያ የሆነው ይህ የአንበጣ መንጋ በሚቀጥሉት ሳምንታት ወደ አረብ ኤሚራቶች፣ ኢራን እና ግብጽ ያመራል። እኛ ዝም ብንል የሰማዕታት ደም ዝም አይልም፤ ይጮኻል፣ ይጣራልፈስሶ አይቀርምሊቢያና የመን ውጥንቅጣቸው እየወጣ እንደሆነ እያየን ነው፣ ግብጽና ሳውዲም አንበጣ ብቻ ሳይሆን ገና እሳት ይወርድባቸዋል።

[ኦሪት ዘጸአት ምዕራፍ ፲፡፬፥፭]

አንበጣዎች

ሕዝቤን ለመልቀቅ እንቢ ብትል ግን፥ እነሆ ነገ በአገርህ አንበጣዎችን አመጣለሁ፤ የምድሩንም ፊት ይሸፍኑታልና ምድሩን ለማየት አይቻልም፤ ከበረዶውም አምልጦ የተረፈላችሁን ትርፍ ይበሉታል፥ ያደገላችሁንም የእርሻውን ዛፍ ሁሉ ይበሉታል

__________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: