Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • May 2023
    M T W T F S S
    1234567
    891011121314
    15161718192021
    22232425262728
    293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተከርስቲያን’

የፀረ-ክርስቶሱ ዓለም፡ “ሥርዓተ ጥምቀቱን” ለመንጠቅ፡ የግሪክ ኦርቶዶክስ አባቶችን በማንቋሸሽ ላይ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 14, 2018

በቆጵሮስ ደሴት፡ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስቲያን ተከታዮች፡ ልጆቻቸውን በጠበቀ መንፈሳዊ ሥነስርዓት ያጠምቃሉ። በዚህ መልክ ለሁለት ሺህ ዓመታት ያህል ያጠመቋቸው ህፃናት ያው ስንቱን መከራና ስቃይ አልፈው የዛሬው ዘመን ላይ ደርሰዋል።

የጥምቀትን ጥቅም ያውቃሉ፤ ጥምቀት የማትደገም፣ የማትከለስ አንዲት ናትና። ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ልጅነትን የምናገኝባት ጥምቀት የማትደገምና የማትከለስ አንዲት ብቻ መሆንዋን ሲያስተምር ‹‹አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት…አለ›› ብሏል (ኤፌ.÷)። ሃይማኖታቸው የቀና 318ቱ ሊቃውንትም ‹‹ኃጢአትን በምታስተሠርይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን፡፡››ብለው አስተምረዋል።

አሁን በሜዲያና በማህበረሰባዊ ድኽረ ገጾች ላይ፡ ሥርዓተ ጥምቀቱን በማጥላላት፡ “ተመለከቱ! ኦርቶዶክሶች ሕፃናትን በሚረብሽ መልክ ያጠምቃሉ” እያሉ የአውሬው ደቀመዛምርት በመለፈፍ ላይ ይገኛሉ። በዚህ ዘመን የምንጠብቀውና፡ ከፀረክርስቶሱ ወታደሮች ጋር የመፋለሚያ መስኮቹ ከሆኑት አንዱ አንዱ ሥርዓተ ጥምቀት ነው። በአንድ በኩል ለሰው ልጅ አሳቢዎችና ተቆርቋሪዎች ሆነው ለመታየት ይሻሉ፤ በሌላ በኩል ግን ለልጆቻቸው ሥርዓተ ጥምቀትን በመንፈግ፣ ብሎም ጥሩውን ከመጥፎ ሳይለዩ ያለ እመንት እንዲያድጉ በማድረግ የሚሠሩት ተወዳዳሪ የሌለው ኃጢአትና ግፍ በጭራሽ አይታያቸውም። እንዲያውም ቀዳዳ እየፈለጉ ክርስትናን ማጥቃት ይመርጣሉ።

በተለይ የእንግሊዙ DailyMail ጋዜጣ በዚህ ጉዳይ ላይ ቅሌታም የሆነ ጽሑፍ ይዞ ወጥቷል፤ እጅግ በጣም ብዙ አንባቢዎችም ዘግበዋል፤ 95 % የሚሆነው ከአውሬው አፍ የወጣ ነው። (https://addisabram.wordpress.com/ )

የሚገርመው፡ የእንግሊዟ ንግሥት ኤልሳቤጥ ባለቤት፡ ልዑል ፊሊፕ በግሪክ ተወልደው አድገዋል፤ በግሪክ ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስቲያን የተጠመቁና አጥባቂ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን እንደሆኑም ይነገርላቸዋል።

DailyMail

______

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: