Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘የኢትዮጵያ ቀጥተኛ ተዋሕዶ እምነት’

አቡነ ሳሙኤል | የኢትዮጵያውያን ጥንታዊ ሥልጣኔ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 8, 2018

እኛ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት ዓለም ጨለማ ውስጥ በነበረበት ጊዜ ቀድመን ያወቅንና የሰለጠን፤ ጥሩን ከመጥፎው፤ ጽድቁን ከኃጢአት ለይተን የተረዳን፤ ከአምስት ሺህ ዓመታት በላይ ታሪክ ያለን ሰብአዊ ክብራችን የጠበቅን ሕዝቦች፤ ለፈጣሪያችን ተገዥ፤ ሰውን አክባሪ፤ ሃይማኖተኞች መሆናችንን ለመረዳት ጥንታዊ ታሪካችንን ማየት ይገባል፡፡ ለምሳሌ፡ዓባይ (ናይል) ግዮን ወንዝን በተመለከተ፤ ከቀይ ባህር በተያያዘ መልኩ ከውጩ ዓለም ጋር የነበረን ግንኙነት፤ ሀገራችን የመን ድረስ የነበራትን የይዞታ ስፋትና የሕንድ ውቅያኖስን በመጠቀም ከህንድና ከሌሎች ዓለማት ጋር የነበረንን የጠበቀ ትስስር መመልከቱ በቂ ማስረጃ ሊሆነን ይችላል፡፡

ኢትዮጵያ በታሪክ ጸሐፍትና በፈላስፎች ዘንድ ብቻ ሳይሆን በመጽሐፍ ቅዱስም የታወቀች አገር ናት። የሕዝቧም ማንነት በቅዱስ መጽሐፍ (በብሉይ ኪዳን) እና በሐዲስ ኪዳን ተገልጧል። ሙሴ የሥነ ፍጥረትን ታሪክ በተናገረበት በመጀመሪያው መጽሐፍ ኢትዮጵያ በዐባይ ወንዝ የተከበበች አገር መሆኑዋን ተናግሯል። “የሁለተኛው ወንዝ ስም ግዮን ነው፤ እርሱም ኢትዮጵያን ምድር ይከበዋል” የሚል ማስረጃ ተጽፎ እናገኛለን፡፡ ዘፍ 2÷13

እስራኤልን ከግብፅ ነጻ ያወጣው ታላቁ ነቢይ ሙሴ የዮተር ኢትዮጵያዊ ልጅን ያገባ መሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። ዘኁ. 12÷1

መጽሐፍ ቅዱስ የኢትዮጵያን ሕዝብና ምድር ሁልጊዜ ከግብፅ ጋር በማያያዝ ይናገራል፡፡ ኢሳ. 20÷3-6፣ ሕዝ. 20÷4-51፣ ዳን. 11÷43፤ ናሆ. 3÷9

በጂኦግራፊ አቀማመጥም ኢትዮጵያ ከግብፅ ደቡብ የምትገኝ አገር መሆኑዋ በቅዱስ መጽሐፍ ተነግሯል ሕዝ. 2910፣ ዮዲ .1÷10

ሱዳንንና ግብፅን ሲያጠጡ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ወንዞች ዐባይና ተከዜ በመጽሐፍ ቅዱስ የታወቁ ታላላቅ ታሪካዊ ወንዞች ናቸው ኢሳ. 18÷1

ኢትዮጵያ በማዕድን የከበረች አገር እንደመሆንዋ አልማዟና ወርቋም በዓለም ተደናቂ ነበር፡፡ኢዮ. 28÷19

ሕዝቧም በንግድ ሥራ በዓለም የታወቁ ነበር። በንግዳቸውም በልጽገውና ተደስተው ይኖሩ ነበር። ኢሳ. 43÷3

የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደ ድንክ አጭር፣ እንደ አዛሔል ረዥም ሳይሆኑ ልከኛና መጠነኛ ናቸው። ኤር. 13÷23

የኢትዮጵያ ግዛትም እጅግ በጣም ሰፊ እንደ ነበር ቅዱስ መጽሐፍ ይመሰክራል። በዜና መዋዕል ካልዕ እንደተገለጸው ኢትዮጵያውያን በጦር ስልትና በጀግንነት ከጥንት ጅምሮ የታወቁ ናቸው ዜራህ (ዝሪ) በሚባለው ንጉሣቸው እየተመሩ ዘምተው ምድረ ይሁዳን ያዙ 2ኛ ዜና መዋ. 14÷9-1516÷8

ኢትዮጵያውያንን ያለ ፈቃደ እግዚአብሔር በኀይላቸው ተመክተው በሚሠሩት ሥራ ነቢያት ይገሥፁአቸው ነበር። ሶፎ. 2÷12

በእግዚአበሔርና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የማያቋርጥ ፍቅርና ግንኙነት ሲገልጡ ደግሞ “ኢትዮጵያ እጆቹዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች” እያሉ በግልፅ ተናግረዋል። መዝ. 68÷31

ከዚህ ሌላ እንደ ባጅ ያሉ ታዋቂ ታሪክ ጸሐፊዎች ኢትዮጵያ ያለ ሃይማኖት የኖረችበት የታሪክ ዘመን እንደሌለ ጽፈዋል። ይህም ያገር ውስጥ ታሪክ ጸሐፊዎች ከሚሰጡት የምስክርነት ቃል ተጨማሪ ነው።

ኢትዮጵያ ከክርስትና በፊት ስለነበራት ሃይማኖት ስንናገር የአቅኒዎቹዋን የሕይወት ታሪክ በመመርመር ነው። ኢትዮጵያን ያቀኑ ሰዎች የመምለኬ እግዚአብሔር የኖኅ የልጅ ልጆች የአያታቸውን አምላክ አንድ እግዚአብሔርን ያመልኩ ነበር።

በተጨማሪም በሐዲስ ኪዳን ክርስትናን በ34 .ም እንደተቀበለች እነዚሁ ብሔራውያን ሊቃውንት፦ ኢትዮጵያውያን የቅዱስ ፊልጶስን ትምህርትና ስብከት ከጃንደረባው ሰምተው ክርስቶስን መቀበላቸውንና ማመናቸውን ሲገልጡ እንዲህ ብለዋል።

“…. መጥምቁና የወንጌል ሰባኪው ሐዋርያ ፊልጶስ ሆይ! ኢትዮጵያውያን ትምህርትህን ከብልሁ ጃንደረባ ሰምተው ለድንግል ማርያም ልጅ ይሰግዳሉ…..”

ወይም መባቸውን ይዘው ለተወለደው ሕፃን ሊሰግዱለት ቤተልሔም ከተገኙ ሰብአ ሰገል አንዱ ኢትዮጵያዊ ከባዜን ንጉሥ የተላከ መሆኑ ግልጽ ነው።

ይህ አገላለጥ ጃንደረባው በመንፈስ ቅዱስ ከተላከለት አስተማሪው ከቅዱስ ፊልጶስ የተማረውን ትምህርት ለኢትዮጵያውያን በማስተማሩ ዳዊት በመዝሙሩ 72÷9 “በፊቱም ኢትዮጵያውያን ይሰግዳሉ” ሲል የተናገረው ትንቢት እንደተፈጸመ ያሳያል።

ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ “ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ አምናለሁ” ብሎ እምነቱን በመግለጡና በማረጋገጡ “ኢየሱስ የእግዚብሔር ልጅ እንደሆነ በሚያምን ሁሉ እግዚአብሔር በእርሱ ይኖራል፤ እርሱም በእግዚአብሔር ይኖራል” (1ኛ ዮሐ. 4÷15) የሚለው አምላካዊ ተስፋ የተፈጸመለት እውነተኛ አማኝ ነበር።

ጃንደረባው የጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ምእመናንን በምታጠምቅበት ጊዜ ትጠቀምበት ለነበረው ሥርዐተ ተአምኖ ጀማሪ መሆኑ ይነገርለታል። ሥርዐቱም የሚከተለው ነው።

አጥማቂው ካህን፦ “ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ታምናልህን? ተጠማቂ ምእመን፡አዎ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ አምናለሁ።

ይህ ሥርዐት ከወንጌላዊው ፊልጶስና ከጃንደረባው ንግግር ጋር ስለሚተባበር ከዚሁ እንደተወሰደ ይታመናል። የሐዋ. ሥራ 8÷37

ወንጌላዊው ፊልጶስና ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ በምን ቋንቋ እንደተነጋገሩ የግብረ ሐዋርያት አንባቢዎች ሁሉ ለማወቅ እንደሚፈልጉ ግልጥ ነው። ድርጊቱ የተፈጸመው በ34 .ም በተከበረው በበዓለ ሐምሳ ሰሞን እንደሆነ በሐዲስ ኪዳን ተገልጧል። ስለሆነም ወንጌላዊው ፊልጶስ በበዐለ ሐምሳ ዕለት ከቅዱሳን ሐዋርያት ጋር ስለዚህ በመንፈስ ቅዱስ በሀገሩ ሁሉ ቋንቋ የመናገር ስጦታን መቀበሉ የታመነ ንው። ስለሆነም ጃንደረባው በራሱ ቋንቋ በግእዝ መጽሐፈ ኢሳይያስን በሚያነብበት ጊዜ ፊልጶስ ሊሰማውና ሊያነጋግረው ችሏል። በመሆኑም ፊልጶስና ጃንደረባው የተነጋገሩበት ኢትዮጵያዊ ቋንቋ ግእዝ ነበር።

በመሆኑም እኛ ኢትዮጵያውያን እንደ ክርስትናችን ሁሉ በተለይ ሰብአዊ ክብራችንና ጤናማ ሕይወታችን በጠበቀ መልኩ ለመምራት የነበረን አሁንም ያለን ጥሩ ትውፊት በቀላሉ የሚለካና የሚታይ አይደለም፡፡ ሊቃውንቱ ሰዎች ሰላማዊና ጤናማ ሕይወት እንዲኖራቸው ለማድረግ ለምርምር የጻፏቸው መጻሕፍት፤ ለመድኃኒትነት የዕፀው ቅመማ፤ የግብረገብ (መልካም ሥነ ምግባራት ትምህርት) ጽሑፎቻችንን በዘረፋ እና በስርቆት ወደ ውጭ ሀገር ቢሄዱብንም አሻራቸው ግን አሁንም አለ፡፡ በጥንት ጌዜ ሰዎች ከልዩ ልዩ ዕፀው መድኃኒት እየቀመሙ በሽተኞችን ይፈውሱ ነበር ኢሳ. 38÷21 ኤር. 8÷22 ሕዝ. 47÷12 ኩፋሌ. 10÷7 እግዚአብሔር አምላክ ለኖኀ መድኃኒትነት ያላቸውን ዕፀው አሳይቶታል።

ጥበብ፣ ማስተዋል፣ ዘዴ ማንኛውንም ነገር ለማግኘት የመመርመር ችሎታ፣ የሥራ ችሎታ የሕክምና ችሎታ የአስተዳደር ችሎታ ያላቸው ሁሉ ጥበበኞች ይባላሉ፡፡ ዘፍ. 31÷2-5 ሕዝ. 27÷8-9

ሰው እግዚአብሔርን በመፍራት ጥበብን ያገኛልና በእግዚአብሔር መንገድም ይራመዳልና መዝ.111÷10፣ ያዕ. 1÷5 ሆኖም ተማርን የሚሉ ሰዎች ጥበብ ከእግዚአብሔር ጥበብ ጋር ሲመዛዘን እንደ ምንም ወይም እንደ ኢምንት ነው።

ሰው ጥበበኛ ነኝ ቢልም በእግዚአብሔር ዘንድ እንደ ባዶ እንደ (አላዋቂ) ነው። ምክንያቱም አወቅሁ ተፈላሰፍኩ መጠቅኹ የሚል ሰው በእግዚአብሔር ከሃሊነት የተፈጠረ እና ሙሉ ሕይወቱም በእግዚአብሔር ሥልጣን የተወሰነ ስለሆነ እያንዳዱ ሰው እንደ ወቅቶች ታይቶ የሚሔድና የሚያልፍ መሆኑን ማወቅና መመራመር በራሱ ጥበብ ከመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች አንዱ መሆኑን ኢትዮጵያውያን ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ 1ቆሮ. 12÷8፣ ሮሜ 1÷221ቆሮ. 1÷19፣ ያዕ 3÷13

ይህን እውቀታችንና ጥንታዊነታችንን መነሻና መሠረት በማድረግ አሁን ዓለም በግሎቫላይዜዥን ከደረሰበት ስልጣኔ ጋር እንዴት አድርገን በማጣጣም የሚበጀንን ብቻ መጠቀም እንዳለብን ቆም ብሎ በማሰብና በማስተዋል ሊሆን ይገባል፡፡ ሁሉም ነገር ከውጭ የመጣውና ጊዜ የወለደው ፍልስፍና ሁሉ ጥሩ ነው ብለን የምናምንና የምንቀበል ከሆን ወይም ዘመናዊነትን ብቻ የምንከተል ከሆነ አደጋው በትውልድና በሀገር እንዲሁም በነፍስም ሆነ በሥጋ የከፋ ይሆናል፡፡

አሁን በቀላሉ የምናያቸውና የምንሰማቸው ከጊዜ በኋላ ዋጋ ሊያ ስከፍሉን ይቸላሉና ነው።

ጥሩ ማስተዋል የተሞላበት ዕውቀት ምን ጊዜም ቢሆን ሰውን ወደ እግዚአብሔር ይመራዋል እንጂ ከእግዚአብሔር አያርቀውም። ከእግዚአብሔር የሚያርቅ ሃይማኖታዊ ያልሆነ ሥጋዊ ዕውቅት ብቻ ነው።

. ሳይንስና ሐኪሞቹ

ብዙዎችን ሰዎች በተለይ በሕክምና ሙያ ባሉ ክፍሎች ከሃይማኖት እንዲርቁ የሚያደርጉዋቸው ዋና ዋና ምክንያቶች ሙያቸው ሳይሆን የአምላክን ሥራ ተመራምረው መድረስ ባለመቻላቸው ነው። ይህ ደግሞ ክህደቱ የብስጭት ይመስላል፡፡ ዛሬ የምናየው የሳይንስ ዕድገት በሚያደርገው ምርምርና (መፈላሰፍ) ለብዙዎች ሰዎች የዕውቀት ዳርቻ ሆኖ ታይቷቸው ሊሆን ይችላል። ከዚህ በፊት ያልታዩና የማይታወቁ የነበሩት ነገሮች ሁሉ ዛሬ በልዩ ልዩ መሣሪያዎች ርዳታ በመገለጻቸው ምክንያት ብዙ ሰዎች የፍጥረት ምስጢር እንደተገኘ አድርገው ቈጥረውታል። ስለዚህ ዛሬ ከመታየትና ከዕውቀትም ውጭ የሆነ ነገር ሁሉ በብዙዎች ዘንድ እንደሌለ ያህል እስከ መቈጠር ደርሷል። ነገር ግን በእውነቱ ከሆነ እነዚህ ሰዎች ምንኛ ተሳስተዋል? ዛሬ የሰው ልጅ የደረሰበት የዕውቀት ደረጃ ምንም እንኳ ካለፈው ዘመን ጋራ ሲነጻጸር ከፍ ያለ ሁኖ ቢታይም ቅሉ እውነቱ ሲታይ የምናውቀው ነገር ከማናውቀው ነገር ጋር ሲነጻጸር ከዕውቀት ጫፍ መድረሳችን ቀርቶ ገና ከመጀመሪያው (ከመነሻው) ትንሽ ፈቀቅ እንኳ እንዳላልን ለምን አንረዳም። አንዳንድ ሰዎች በሃይማኖት እግዚአብሔርን ከማመን የሚርቁት ስለ ሰው የዕውቀት ደረጃ እንዲህ ዐይነት አስተያየት ስለሌላቸው ነው። ይኸውም የሰው ልጅ ሊኖር የሚቻለውን ነገር ሁሉ እንዳገኘና እንደ ተረዳው አድርገው ያስባሉ። በመሆኑም ከዕውቀት ውጭ የሆነውንና ሊታይ ወይም ሊዳሰስ የማይቻለውን ሁሉ ሊቀበሉት ያዳግታቸዋል። ግን ይህ ሁሉ መሳሳት ነው። ለዚህ ጉዳይ ታላላቅ ሳይንቲስቶችንም ሆነ ሊቃውንትን መጠየቅ ያስፈልጋል። መጻሕፍቶቻቸውንም ወስደን ብንመለከት እንዲህ ያለው አመለካከት ስሕተት መሆኑን ያረጋግጡልናል። ለመሆኑ ሳይንስ ገና ከዚህ መቼ ደረሰና! ገና ልናውቀው የሚገባን የዚህ ዓለም ምስጢር የትና የት! ሳይንስ ስለ ዓለም የመጨረሻውን ጥበብ ሰጥቷል ብለን ስንደመድም በማግስቱ እንደገና አዳዲስ ነገሮችና በሽታዎች ሲፈጠሩ እናያለን። በዚሁ ጉዳይ ተመራማሪዎች በየበኩላቸው የሚያቀርቡትን ሐሳብ ብንሰማ በእውነቱ ከዚህ በላይ ስለ ሳይንስ ከፍተኛ ግምት ባልደረስን ነበር።

ዛሬ ስለምንመካበትና ሁሉንም ነገር እንዳወቅን አድርገን ስለምን መለከተው፣ ስለምናስበው ስለዚሁ ሳይንስ ስለ ተባለው ነገር BOUTROUX የተባለ ሊቅ ከዚህ ቀጥሎ ያለውን ቃል ለማስረጃነት ይሰጠናል።

ሳይንስ ተብሎ ስለሚነገረው ነገር ዛሬ ባለንበት ዘመን የተፈጠረውን ሐሳብ መመልከት ዋጋ ያለው ነገር ነው። ከጥቂት ዓመታት በፊት ሳይንስ ሲባል የፍጥረትን ልዩ ልዩ ነገሮች በትክክል አድርጎ የሚፈታና የሚያስረዳ ፍጹምነት ያለው የዕውቀት ዐይነት ሁኖ ይታሰብ ነበር። ይህም የሆነበት ምከንያት ይህ ትምህርት ብዙ ርምጃዎችን በማድረጉ የሱ ኀይል የማይደርስበት ምንም ስፍራ እንደማይገኝ ታስቦ ከፍ ያለ ግምት ተጥሎበት ስለ ነበር ነው። ግን ይህ ሁሉ ዛሬ ሳይንስ ያስገኘው ጥቅም አለ፤ ነገር ግን ያልተደረሰበትም ሌላ ጥበብና እውቀት አለ።

LE COMTE DE NOUY የተባለ ምሁር ሲናገር እንዲህ ብሏል።

ተረድቸዋለሁ ደኀና አድርጌ ዐውቀዋለሁ ብለን ዛሬ ስለ ምንም ነገር ለመናገር አንችልም። ይህ እንዲህ ዓይነቱ አፍን መልቶ መናገር ከብዙ ዓመታት በፊት ነበር እንጂ ዛሬ እንዲህ ለማለት የማይቻል መሆኑ በሊቃውንት ሁሉ ፊት የጸደቀ ሐሳብ ሁኗል። ምክንያቱም ቀድሞ ማንኛቸውንም ነገር በርግጥ ባሕርዩን ለይተን ምስጢሩን የምንረዳው አድርገን እናስብ ነበር።ነገር ግን ዛሬ እንዲህ ያለው ዘመን አልፎ ያለነው የኀይላችንን ትንሽነት መገንዘብ ማስተዋል ግዴታ ከሆነብን ዘመን ላይ ነን ያለነው። ከዚህ በፊት በሰው ዕውቀት ላይ የነበረው እምነትና ከፍተኛ ግምት ዛሬ የለም። ይህ በፊት የነበረው እምነትም ተመልሶ ሊመጣ የሚችልበት ዘመንም ያለ አይመስልም።

የዚህን ሰው ሐሳብ የመሰለ ዛሬ እንዲሁ ሌላም PRINCIPLE OF INDETERMINTION በሚል ዐይነት አነጋገር የታወቀ በሳይንቲስቶች በኩል አንድ ዐይንት ሐሳብ ተፈጥሯል። በዚህም ሐሳብ መሠረት ስለ ምንም ነገር ከዚህ በፊት ይደረግ እንደ ነበረው ሁሉ አንድም ርግጠኛና ስሕተት የሌለበት ሆኖ የሚታሰብ ዕውቀት ለማግኘትና ወስኖ ለመናገርም የማይቻል መሆኑ የተረጋጋጠ ሁኗል። ይህም በብዙዎች ታላላቅ ምሁራን ዘንድ የጸደቀ ሐሳብ ነው።

እንደዚህም አንድሬይንክ የተባለ ሊቅም ሲናገር የምናውቀው ነገር መጠኑ ካንድ ከማይታወቅ ትልቅ የውቅያኖስ ባሕር ውስጥ እንደ ሁለት ያኸል ጠብታዎች ነው። የበለጠ ባወቅንም ቁጥር ሌሎች ብዙዎች የማይታወቁ ልዩ ልዩ ከባድ ጥያቄዎች ይፈጠሩብናል ሲል አመልክቷል። ስለሆነም ብዙ ምሁራን እንዳላችሁ አውቀናል ሰዎች ከየት እስከ የት ነው እውቀታችሁ?

አንድሬ ብሎንዴል የተባለ ምሁርም እንዲህ ብሏል። የዛሬዎቹ ሊቃውንት ከፍጥረት ምስጢር ፊት ስለ ራሳቸው ከፍ ያለ ትሕትና ይሰማቸዋል። ዛሬ ሁላቸውም ደካማነታቸው ታውቋቸዋል።

ባንድ ከፍተኛ አእምሮ ይኸውም የዓለሙ ፈጣሪና አቀናባሪ በሚኾን ኀይል ማመንም ከማናቸውም ከማቲሪያሊስቲክ ሐሳብ ሁሉ የበለጠ አጥጋቢነት ያለው ነው ብለዋል።

እንዲሁም ኬ.ሙሬ የተባለ ሊቅም ከዚህ የሚከተሉትን ቃላት ተናግሯል።

ዓለሙ ከአእምሮ ኀይል በላይ ነው። በዓለሙ ፊት አእምሮ ተሸንፎ የሚወድቅ ነው። ከዓለሙ ትልቅነትና ግርማም ፊት አእምሮ የራሱን ትንሽነት ስለሚገነዘብ ትሕትና ይሰማዋል።

ዶክተር ሮምበር ሚልካነ የተባለ አንድ ሌላም ሊቅ እንዲህ ሲል ተናግሯል።

በ፲፱ነኛው መቶ ዓመት ይደረግ እንደነበረው አንድ ፊዚስት የዓለሙን መሠረታዊ ነገር እንዳወቀ ዐይነት አድርጎ ያስብ የነበረበት ዘመን አልፚል። ዛሬ ሊቃውንት የሰው አእምሮ እንኳንስ እንዲህ ያለ ዕውቀት ሊያገኝ ይቅርና ጥቂት እንኳ እንዳልተራመደና እንደ እውነቱም ያለው መንገድ በመጀመር ላይ መሆኑን ተገንዝበዋል።

ሰር ጄስም ጂንስ የተባለ አንድ የከዋክብት ተመራማሪ ሊቅም የሰውን አእምሮ ደካማነት ሲጠቅስ የዓለሙን እውነተኛና ቀጥተኛ ባሕርይ እናገኛለን ብለን ምንጊዜም የዚህ ተስፋ ሊኖረን አይችልም ሲል ተናገሯል።

አሁን ይህን ሁሉ የጠቀስንበት ምክንያት ብዙ ሰዎች የአምላክንም መኖር ሆነ የሃይማኖትን እውነተኛነት በአእምሮ ወይም በስሜት አውታሮች በኩል እንደ ሌላው ሁሉ ነገር በግልጽ ለመረዳት ያስቡና ይህ ሳይሆንላቸው ሲቀር ወደ ክህደት የሚያደርጉትን ርምጃ ለመውቀስ ነው።

ዶክተሮች በምትሠሩት የሕክምና ሙያ ሥራና በምታክሙት ታማሚ እውነተኛው ሐኪም አምላክ መሆኑን በእናንት ምክንያት፣ በእናንተ ጥበብ እግዚአብሔር ገብቶበት ሰውን ያህል ትልቅ ፍጡር ታድኑበት ዘንድ በእምነትና በጸሎት ሥራችሁን ጀምሩት።

እንዲሁም መልካም ስነ ምግባርን በመጠበቅና በማስተላለፍ በኩል በሀገራችን ቅዱስ ባህል መሠረት ኢትዮጵያዊና ኢትዮጵያዊት መደሰት ባለባቸው ጊዜያት ሰብአዊ ክብራቸውን፤ ባህላቸውን፤ ሃይማኖታቸውን፤ ታማኝነታቸውን በጠበቀ መልኩ ይበላሉ ይጠጣሉ ይደሰታሉ እንጂ ከእንስሳት በአነሰ መልኩ የረከሰ ተግባር አይፈጽሙም፡፡ ስለዚህ የሀገር መሪዎችና የሃይማኖት አባቶችም ጥሩና ቅዱስ ባህላችን የማስከበርና ከመጥፎና ጐጂ ልማዶች ሕዝቡን የመጠበቅ ከእግዚአብሔርም ሆነ ከሰው ታላቅ አደራና ኃላፊነት አለብን፡፡ በቃልም የምናስተምረውንና የምንናገረውን በተግባር የማንገልፀው ከሆነ መልእክታችን ሙሉ በሙሉ ተቀባይነትን አያገኝም።

ለምሳሌ ያለፈው አንድ አራተኛ ክፍለ ዘመን ሳይንስ ብዙ ዕውቀትን አምርቷል፡፡ ከዚህ ክፍለ ዘመን በፊት ካለፉት በሙሉ ዐራቱ ክፍለ ዘመናት ይልቅ በጣም ጨለምተኛ የሆነው የቅርብ ጊዜ የታሪክ ንባብ ሁሉም አዳዲስ እውቀቶችን ለክፉ ነገር ዓላማ የተጠቀምንባቸው መሆኑ የግድ መታወቅ አለበት፡፡ ይህም ሲባል የእኛ የሆነው የተረበሸ ወይም በጫጫታ የተሞላ እና የተደባለቀ ስሜት እንዲሁም እዚህም እዚያም በጣም የተጨናነቀ ነው፡፡ ነገር ግን ምዕራባዊው ዓለም በሰላማዊ ሰልፍ ብቻ የተሻለ ዓለም ነው፡፡ በአጠቃላይ እኛ በታዋቂ አዳዲስ ንቃት ዕውቀት ወደ ከበሩ ሀብቶችና ውስጣዊ ምጣኔዎች እየተወስድን ነው፡፡ በእያንዳንዱ የሰው ልጅ ኅሊና የማይገመቱና ሊጠኑ የሚገባቸው፤ሊያድጉ የሚገባቸውና በምርምር ሊጣሩ የሚገባቸው አመራጮች አሉ፡፡

ማን ነው ይህን ሊል የሚችል? ሰንበር ያለበትን ሕፃን፤ ፊቱ በለቅሶ ቀይ ሆኖ ባየ ጊዜ ይህ ልጅ አንድ ቀን የታላቅ ሕንፃ ዲዛይን የሚያደርግ መሆኑን እንዲሁም የትልቁ ካቴድራልን ዲዛይን የሚያደርግ መሆኑን፣ በማርስ የመልክዓ ምድር ገጽታ ላይ እግሩን የማያሳርፍ መሆኑን ደፍሮ የሚናገር ማን ነው? ገዳይ ለሆነ በሽታስ መድኃኒት የማያገኝ መሆኑን፤ በብቸኛ ሁኔታ በጥበብ የተሞላ መጽሐፍ ትውልድን አስተማሪ የሆነ የማይጽፍ መሆኑንስ? ታላቅ ኃይል ያላትን ሀገር የማይመራ መሆኑን ወይም ብቸኛ የሆነች ነፍስን የማያድን መሆኑን ደፍሮ የሚይናገር ማን ነው?

ይህ ሁኔታ እኛ የእኛን ሰብእና ብቻችንን ሁነን እንድናሳድገው የተሰጠ አስተያየት አይደለም፡፡ የዚህ ተቃራኒው ግን ይሠራል፡፡ ከእኛ ውጭ በሆኑት ከሰዎች ጋርና ከክስተቶችም ጭምር ይህ የእኛ ሰብእና ጥልቅ የሚሆነውና የሚሰፋው በዚህ ትርጉም ባለው ግንኙነት ብቻ ነው፡፡ ማንም ሰው ብቸኛ ደሴት አይደለም፡፡ ይህ ተቀባይነት ያለው በዓለም ላይ ያለ እውነት ነው፡፡ የእኛ የራሳችን ተሞክሮዎች በመመሪያ የሚከናወኑ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን እኛ በሌሎች ሰዎች ልምዶች በጉጉት በተቃራኒ ጊዜ የእኛ ስስ ስሜት ወይም መነቃቃትና አረዳድ በታላቅ ሁኔታ ከፍተኛ ነው፡፡ ይህም ሲባል ከሚሰቃዩት ጋር ለመሰቃየት ፤ከሚደሰቱት ጋር ለመደሰት፤ በሌሎች ሰዎች ሕመምና ጭንቀት ለመግባት በጎዳና የሚኖሩት ሁሉ የድረሱልን ጥሪ የሚጣሩትን ታላቅ ቦታ ግምት መስጠት ይገባል፡፡

እኛ የወጣቶችን አስደሳች የሆነ ሕይወት፤የታላላቆችን ቅን የሆነ ጥበብ ፤የወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን በጉጉት መነሳሳት ለመጋራት በምንችለው መጠን፤ እንተባበር፡፡ የተለያዩ ወጣቶች የሱስ ሰለባዎች እንዳይሆኑ ለሕይወታቸው መበላሻት ምክንያት የሚሆኑትን የተስፋ ቢስነት ወይም ሙሉ በሙሉ ተስፋ በመቁረጥ በአልባሌ ቦታ የሚውሉና በሱሰኝነትና በሌብነት ሥራ የተጠመዱ ወገኖች እንዳይኖሩብን መጠንቀቅ ይገባናል፡፡

. ስለ ሕክምና አገልግሎት የቤተ ክርስቲያን መልእክት

ሐኪምና ሕክምና (ሐከመ፡አከመ ፈወሰ አዳነ) ከሚለው የግዕዝ ቋንቋ የወጣ ስያሜ ነው፡፡ በሌላም አገላለጽ ጠቢብ አቃቤ ሥራይ ተብሎ በብዙ መጻሕፍት ላይ ተመዝግቦ እናገኛለን፡፡ ጠቢብ አቃቤ ሥራይ ማለትም ጥበበኛ ፈዋሽ አዳኝ ባለ መድኃኒት የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡ ሕክምናን ጥንታዊ ወይም ባሕላዊ ሕክምና ዘመናዊ ወይም ሳይንሳዊ ሕክምና ብለን በ2 ምዕራፍ ልንከፍለው እንችላለን፡፡

ሕክምና ማለት በእግዚአብሔር ልግሥና በሰዎች ፍልስፍና የተገኘ እና የሚገኝ በሽተኛ ሰውን ወይም የታመመ እንስሳን የመፈወስ ጥበብና የማዳኛ ዘዴ ማለት ነው፡፡ የሕክምናውና የጥበቡ ባለቤትም ፈዋሴ ድውያን መንሥኤ ሞውታን የተባለው ሕሙማነ ሥጋን በተአምራት ሕሙማነ ነፍስን በትምህርት የሚፈውሰው ዶክተሩ ጠቢበ ጠቢባን እግዚአብሔር ነው፡፡

በመጽሐፈ ሰሎሞን መጽሐፈ ምሳሌ 9 ላይ የተጠቀሰውን ኃይለ ቃል (ጥበብሰ መድኃኒነ ውእቱ) ጥበብ ወይም ጠቢብ የተባለው በቅዱስ ሥጋው በክቡር ደሙ ያዳነን መድኅኒታችን እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ነው በማለት ሊቁ እንደተረጐመው፡፡ (ቅዳሴ ኤጴፋንዮስ) የመጀመሪያውም ሐኪም ራሱ ባለቤቱ እግዚአብሔር ሲሆን በሽተኛውና ታካሚውም አባታችን አዳም ነው፡፡ ለሰው ልጅ ጤንነት መድኃኒት ምክንያት ሕይወት የሚሆኑትም ለምሳሌ ያህል የተጠቀሱትን ከቅዱስ መጽሐፍ እንዲህ እናነባለን፡፡ (እምኩሉ እፅ ዘውስተ ገነት ብላዕ ወእምእፅሰ ዘሀሎ በማዕከለ ገነት ዘያሌቡ ሠናየ ወእኩየ ኢትብላዕ እሞኔሁ) (መልአከ ሕይወት) ጌታ የሕይወት ባለቤት ጌታ በገነት መካከል ካለው አትክልት አዝርዕት ሁሉ ለጤንነትህ ይጠቅምሃልና ብላ ነገር ግን ለጤንነትህ የማይጠቅም ጐጂና መርዛማ የሆነውን ፍሬ ዕፅ ግን አትብላ ስንኳን መብላት ቅጠሉን ወይም ግንዱን በእጅህም አትንካው፡፡ ምክንያቱ ከዚያ መርዛማ ዕፅ ከበላህ ድውየ ሥጋ ድውየ ነፍስ ያደርግሃልና ሲል መርዛማውን ዕፅ ከነምክንያቱ በመግለጽ እንዳይበላው አስጠንቅቆታል፡፡ ከዚህም ኃይለ ቃል መርዛማና አደንዛዥ የሆኑ እፀዋት መጠቀም እንደሌለብን እንገነዘባለን፡፡ ይህን የመሰለውንም መርዛማ እና አደንዛዥ ለሰዎች ሕይወት ጠንቅ የሆነውን ዕፅ ይዞ የተገኘም ሰው በሕግ ፊት ተጠያቂ እንደሚሆን በዓለም አቀፉ ሕገ መንግሥት ተደንግጓል፡፡ ዘፍ.2 ÷17

ዳግመኛም በትርጓሜ መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ 39÷ከቁ.26 ጀምሮ ለሕይወታችን ገንቢ ለጤንነታችን ጠቃሚ የሆኑትን እንደምሳሌ ሁነው ተጠቅሰው የምናገኛቸው እህልና ውኃ ወይንና ስንዴ ማርና ቅቤ እንዲሁም ጨው እና ነጭ ሽንኩርት የመሳሰሉት በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ (ጥበበ ሲራክ ንባብና ትርጓሜው) ደዌ ሥጋው በጸናበት ቸነፈሩና ወረርሽኙ በተስፋፋበት ወቅትም ለቀደሙት ቅዱሳን አበው ለሄኖስ ለሄኖክና ለኖኀ ከላይ የተጠቀሱትንና ሌሎችንም በርካታ ፈዋሽ መድኃኒቶችን ነግሯቸዋል (አሳይቷቸዋል)፡፡ ከቀደሙት አበው ሲያያዝ በመጣውም አምላካዊ መመሪያ መሠረት በሊቀ ነቢያት ሙሴ አማካይነት ታላቁ ቅዱስ መጽሐፍ ከተጻፈበትም ጊዜ ጀምሮ አበው ነቢያት በቈጽለ ወይን፤ በፍሬወይን፤ በሐረገ ወይን፤ በቈጽለ በለስ፤ በፍሬ በለስ፤ በማየ ዮርዳኖስ ሕዝብንና አሕዛብን ሳይለዩ በእኩልነት በሽተኞች የሆኑትን የሰው ልጆች ሁሉ በእግዚአብሔር ስም ይፈውሷቸው እንደነበርና መርዛማውንና መራራውንም ውኃ በጨው ያጣፈጡት እንደነበር ከታላቁ ቅዱስ መጽሐፍ አንብበን መረዳት እንችላለን፡፡ መጽሐፈ ነገሥት ለምሳሌ፡የእስራኤል ንጉሥ ሕዝቅያስ በታመመ ጊዜ የተላኩት አሽከሮች ለጌታቸው ደዌ መፍትሔ ሲጠይቁት ቅዱሱ ነቢይ ኢሳይያስ ቈጸለ ወይኑን ሐረገ ወይኑንና ፍሬ ወይኑን ቈርጦ በመስጠት (ሑሩ ቅብዕዎ ኀበ ሕበጡ ለእግዚእክሙ በስሙ ለእግዚአብሔር ጸባኦት አምላከ እስራኤል ወየሐዩ) ሂዳችሁ በአሸናፊው በእስራኤል አምላክ በእግዚአብሔር ስም የጌታችሁ የሕዝቅያስ አካሉን በዚህ ፍሬወይን ቈጽለ ወይን ቀቡት እርሱም ይድናል በማለት አሽከሮቹን እንደመከራቸውና ንጉሥ ሕዝቅያስም በዚሁ የፈውስ አገልግሎት እንደተፈወሰ እንረዳለን ( 2ነገሥ. . 20 . 1-7) በተመሳሳይ ሁኔታ ታላቁ ነቢይ ኤርምያስም በቈጽለ በለስ በፍሬ በለስ ምክንያት በሽተኞችን በመፈወስ ይረዳቸው እንደነበረ አንብበን መረዳት እንችላለን፡፡

በተለይ ጥበብ ሥጋዊ ጥበብ መንፈሳዊ የተገለጸለት ነቢዩ ንጉሠ እስራኤል ሰሎሞን የእያንዳንዳቸውን የዕፀዋት አገልግሎት ያውቅ ስለነበር በእፀዋቱ ምክንያት በእግዚአብሔር ስም ለሕሙማኑ የፈውስ አገልግሎት ይሰጥ ነበር፡፡ ከፈውሱ ተጠቃሚዎችም መካከል አንዷ የኢትዮጵያ ንግሥት ሳባ እንደሆነች በትርጓሜ መጻሕፍት ተገልጿል፡፡ (ትርጓሜ ወንጌል)

ጥበበኛው ሰሎሞንም ከእርሱ በፊት የነበሩት አባቶቹ እስራኤላውያን በግብጻውያን ላይ ከተከሰተው ቸነፈር በሲና በረሃም ሳሉ ከወረደባቸው ደዌ ሥጋና መቅሰፍተ ሥጋ የጸኑት በእርሱም በሰሎሞን ዘመን የነበሩዋት ወገኖቹ ድውያን እብራውያን የተፈወሱት ሕያው ማሕየዊ በሆነው በእግዚአብሔር ቅዱስ ስም እንደሆነ እና እፀዋቱና አፍላጋቱ ግን ምክንያተ ሕይወት መሆናቸውን እንዲህ በማለት አስረድቷል፡፡

አኮ ዘድኀነ በዘርዕየ አላ በእንቲከ ድኀነ ኦ መድኃኔ ኩሉ ትርጉም የሁሉ መድኃኒት ጌታ ሆይ ድውያነ ሥጋ እስራኤል አርዌ ብርቱን በማየት የጸኑ አይደሉም አንተን በማመን ጸኑ እንጂ ወዝንቱ ትእምርት ኮኖሙ መድኃኒተ ያዘክሮሙ ትዕዛዘ ቃልከ ይህ አርዌ ብርት አዘህ ያሠራኸውን ሕገ ሕይወት መጽሐፍ ያሳስባቸው ዘንድ ምክንያተ ሕይወት ሆናቸው እንጂ፡፡

ግዕዝ አኮ እፅ ዘይሰትይዎ ወኢሥራይ ዘይቀብእዎ ዘፈወሶሙ አላ ቃለ ዚአከ እግዚኦ ዘኩሎ ይፌውስ ፈውሶሙ እስመ ለሞት ወለሕይወት ሥልጣን ብከ፡፡

ትርጉም ሕሙማኑን ድውያኑን የሚጠጡት እንጨት የሚቀቡት አስማት ያዳናቸው አይደለም አቤቱ ሁሉን የሚያድን ቅዱስ ቃልህ አጸናቸው እንጂ ለሕይወትና ለሞት ሥልጣን አለህና በማለት ለፈውስ አገልግሎት የሚውሉት እፀዋቱ አዝርዕቱ፣ አትክልቱና ማያተ አብሕርቱ ምክንያተ ሕይወት ናቸው እንጂ ፈዋሹ እግዚአብሔር ስለሆነ በእግዚአብሔር ፈዋሽነት አምነን ቅዱስ ስሙን ጠርተን እፀዋቱን ወይም ክኒኑንና መርፌውን ብንጠቀም የፈውስ አገልግሎት ማግኘት የምንችል መሆኑን በጥንቃቄ አስረድቶናል፡፡ ትርጓሜ መጽሐፈ ጥበብ ም10 ከቁ. 29-36፡፡

በመቀጠል ጥበበኛው ሰሎሞን ፈዋሽ ከሆኑ ዕፀዋትም መካከል አንደኛውን እፀ ሕይወት ጠቆም አድርጐ አልፏል፡፡ ግዕዝ ሐረገወይን ዘእምሐሢሦን ይትገዘም ወበጐልጐታ ይተከል ኮነ መድኃኒትየ ትርጉም፡ከገነት የተቈረጠው በጐልጐታ የተተከለው ሐረገወይን ጉንደ ወይን (ቅዱስ መስቀል) መድኃኒቴ ሆነኝ በማለት እርሱ ሰሎሞን ንግሥት ሳባና ሌሎችም ድውያን በጉንደ ወይን (በጉንደ መስቀል) ከደዌ ሥጋ ከደዌ ነፍስ የተፈወሱበት መሆኑን መስክሯል መሐልየ ሰሎሞን

በመጨረሻም ጥበበኛው ነቢይ ሰሎሞን ከደዌ ሥጋ ከደዌ ነፍስ የሚያድኑ መምህራን እንዲሁም የፈውሰ ሥጋ አገልግሎት የሚሰጡ ጠበብት ሐኪሞች በየኅብረተሰቡ መካከል በብዛት እየተገኙ ለዓለሙ ኅብረተሰብ አገልግሎት ቢሰጡ ጠቃሚ መሆናቸውን ሲገልጽ እስመ ብዝኃ ጥበብት መድኃኒተ ዓለም ውእቱ ትርጉም የጥበበኞች (የመምህራን የሐኪሞች) መብዛት የዓለም መድኃኒት ነው በማለት የባለሙያዎች እጥረት መኖር እንደሌለበት መልእክቱን አስተላልፏል፡፡ መጽ. ጥበብ 4÷25

ከደዌ ሥጋ የሚፈውስ ሐኪም (ወጌሻ) ከደዌ ሥጋና ከደዌ ነፍስ የሚያድን ካህን ለሰው ልጆች ሁሉ አስፈላጊ መሆኑንና አምላካችን እግዚአብሔርም በዚህ ዓለም ፈዋሽ መድኃኒትን (አንድም) ሥርየተ ኃጢአትን እንደፈጠረና እንደአዘጋጀ ተገልጋዩ ኅብረተሰብም ሐኪሙን ካህኑን አክብሮ መገልገል እንደአለበት እንዲህ በማለት ነቢየ እግዚአብሔር ሲራክ አባታዊ ምክሩን ይለግሰናል፡፡ ግዕዝ አክብሮ ለአቃቤ ሥራይ እስመ በከመ እዴሁ ከማሁ ክብሩ እስከ ሎቱኒ እግዚአብሔር ፈጠሮ

ትርጉም ባለመድኃኒቱን ሐኪሙን አክብረው በአገልግሎቱ መጠን መከበር ይገባዋልና እርሱንም እግዚአብሔር ለዚህ አገልግሎት ፈጥሮታልና አንድም ካህኑን አክብረው በመስቀሉ (በእጁ) ባርኮ በጸበሉ ረጭቶ (አጥምቆ) በቃሉ ናዝዞ ከደዌ ሥጋ ከደዌ ነፍስ በማዳኑ ሊከበር ይገባዋልና እርሱንም እግዚአብሔር ለዚህ ለክህነት አገልግሎት ሹሞታልና፡፡ ግዕዝ፡እስመ እግዚአብሔር ፈጠረ ሥራየ እምነ ምድር ወብእሲ ጠቢብ ኢይሜንኖ ትርጉም እግዚአብሔር መድኃኒትን ከምድር ፈጥሯልና ብልህ ሰውም አይንቀውም (እግዚአብሔር ካህኑን ከሰው መርጦ ሹሞታልና) ብልህ ሰውም አይንቀውም ግዕዝ፡አኮኑ በእፅ ጥዕመ ማይ ከመ ያዕምሩ ኃይሎ ትርጉም መድኃኒት መናቅ እንደሌለበት ይታወቅ ዘንድ መራራው ውኃ በእንጨት የጣፈጠ አይደለምን? ነቢዩ ሙሴ ዞጲ በሚባል እንጨት መራራውን ውኃ እንደ አጣፈጠው ዘፀዓት. 15÷25

ነቢዩ ኤልሳዕም መራራውንና መርዛማውን ውኃ በጨው አጣፍጦታል፡፡ እፀዋቱ በእግዚአብሔር ስም ከተጠቀሙባቸው ፈዋሽነት እንደአላቸው ለማጠየቅ ጌታ ለኖኅ ሺህ መድኃኒት ነግሮታል (አሳይቶታል)፡፡ ከሺሁ ሦስቱን መቶ ይህ ለዚህ ይበጃል ብሎ ቃል በቃል ነግሮታል፡፡ ሰባቱን መቶ (፯፻ን) ግን ከዕፀዋት ውጤቶች ከሆኑት ከማር እና ከቅቤ ታገኘዋለህ ብሎታል (ኩፋሌ 42÷8-10)

በመቀጠልም ነቢዩ ሲራክ ሐኪሙና እፀዋቱ ካህኑና ጥምቀቱ ለፈውሰ ሥጋና ለፈውሰ ነፍስ ምክንያቶች ናቸው እንጂ ሕይወተ ሥጋንና ሕይወተ ነፍስን የሚያድለው የሕይወት ባለቤት እግዚአብሔር ነውና ደዌህን ያርቅልህ ችግርህንም ያስወግድልህ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸልይ በማለት መልክቱን በማስተላለፍ መልእክቱን ይቋጫል፡፡

ግዕዝ፡ወልድየ ኢትጸመም ሕማመከ ጸሊ ኀበ እግዚአብሔር ወውእቱ ይፌውሰከ

ትርጉም ልጄ ሕማምህን ቸል አትበል አድነኝ ብለህ ወደ እግዚአብሔር ጸልይ እርሱም ይፈውስሃል (ትርጓሜ መጽሐፈ ሲራክ ም. 38 ከቁጥር 1-15) ይመልከቱ፡፡

ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በዚህ ዓለም ስለሚገኙት ፈዋሽ እፀዋት እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡ ወተከለ እግዚአብሔር ሠለስተ ዕፀወ ሕይወት በዲበ ምድር

ትርጉም እግዚአብሔር በምድር ላይ ሦስት የሕይወት እንጨቶችን ተከለ (አበቀለ) በማለት ከመጽሐፍ ቅዱስ ከተነገረው ጋር አያይዞ ተናግሯል፡፡ ይህንንም ቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ ሲል ተርጉሞታል፡፡ ግዕዝ፡ከፈለነ ንብላዕ እምእፀ ሕይወት ዘውእቱ ሥጋሁ ቅዱስ ወደሙ ክቡር

ትርጉም ከእፀ ሕይወት እንበላ ዘንድ አደለን ይኸውም ቅዱስ ሥጋው ክቡር ደሙ ነው በማለት በከፊል ተርጉሞታል፡፡ ሠለስቱ እፀወ ሕይወት የተባሉት ሁለቱ ቅዱስ ኤፍሬም እንደተረጐመው እፀ ሥርናይና እፀ ወይን ሲሆኑ ሦስተኛው ለልጅነት ለሥርየተ ኃጢአት ምክንያት የሚሆነው እፀ ዘይት ወይም እፀ በለሳን ነው፡፡ በለሳነ ኮነ ሐፈ ሥጋሁ በቁሎ ሜሮን ቅብዕ ዘይቄድስ ኩሎ እንዳለው ደራሲ በመቀጠልም ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ስለ እፀ ሕይወት ሲያብራራ ወላዲተ አምላክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያምን ባመሰገነበት አንቀጽ እንዲህ በማለት ዘምሯል፡፡ ግዕዝ፡አንቲ ውእቱ እፅ ቡሩክ ዘኮንኪ እፀ ሕይወት በዲበ ምድር ህየንተ ዕፀ ሕይወት ዘውስተ ገነት

ትርጉም በገነት መካከል ስላለው እፀ ሕወት ፈንታ በምድር ላይ እፀ ሕይወት የሆንሽ የተባረክሽ እፅ አንቺ ድንግል ማርያም ነሽ በማለት እመቤታችንን በቃል ኪዳኗ ለሚማጸንባት በአማላጅነቷ ለሚተማመንባት ሁሉ ምክንያተ ሕይወት መሆኗን አስረድቷል፡፡ (ድጓ አንቀጸ ብርሃን) ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሥጋችን ለብሶ ባሕርያችን ባሕርይ አድርጎ ሰዎችን በሚያስተምርበት ጊዜ አንድ አንዶችን ፈቀድኩ ንጻሕ በቃሉ ብቻ ያለምንም ምክንያት እኔ ፈቅጃለሁና ንጻ እያለ ድውያንን የፈወሰ ሲሆን በሌላ ጊዜ ደግሞ ለፈውሱ ምክንያት በመፈለግ የዓይነ ሥውሩን ዓይን በምራቁ ጭቃ ለውሶ በመቀባትና ሂደህ በሰሊሆም በፈሳሹ ወንዝ ውኃ ተጠመቅ በማለት ይፈውሳቸው እንደነበር በቅዱስ ወንጌል ተጠቅሷል፡፡ ዮሐ. 9÷1

ዳግመኛም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሕክምና አገልግሎት መጠቀም ተገቢ መሆኑን ጥንቁልና ወይም እንደ በደል የሚቆጠር አለመሆኑን እንዲህ ሲል በቅዱስ ወንጌል አስረድቷል፡፡ግዕዝ፡ሕሙማን ይፈቅድዎ ለዐቃቤ ሥራይ

ትርጉም በሽተኞች ሐኪሙን ወይም ባለመድኃኒቱን ይሹታል በማለት ያስተማረ ሲሆን በሉቃስ ወንጌል እንደተመዘገበው ወንበዴዎች ደብድበው የጣሉትን ቁስለኛ ሰው ደጉ ሣምራዊ መጥቶ ለጊዜው ቁስሉን የሚያለዝብ ዘይትና የሚያደርቅለት ወይን ቀብቶ በአህያውም ላይ ጭኖ ወደተሻለ ሐኪም እንደወሰደውና እንደአሳከመው በምሳሌነት ጠቅሶ እንደአስተማረበትና ደጉ ሳምራዊም የነፍስ አድን ሥራ በመሥራቱ በሽተኛውን በወቅቱ ባለው ባሕላዊ ሕክምና በመርዳቱ እንደ አመሰገነው እንረዳለን፡፡ ሉቃስ 10÷30

ምንጭ፡ አቡነ ሳሙኤል

______

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

ገነትን ፍለጋ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 7, 2018

(በዶ/ር ሐዲስ ትኩነህ)

መግብያ

የቀደሙ አባቶች ገዳማውያን ገነትን ፍለጋ የፍየል ሌጦ ለብሰው፣ ጤዛ ልሰው፣ድንጊያ ተንተርሰው በረሀ ለበረሀ ተንከራተዋል፡፡ ሰማዕታትም ገነትን ፍለጋ ተሰደዋል ፣ እንደእንጨት ተፈልጠው፣ እንደአትክልት ተከትፈው ደማቸውን አፍሰዋል፡፡ ከቀደሙ አባቶች መካከል እግዚአቤሔርን አገልግለው በሕይወተ ሥጋ ሳሉ ወደ ገነት ተነጥቀው በገነት የሚኖሩ አሉ (ኄኖክ ፣ ኤልያስና ዕዝራ) (መጽሐፈ ምሥጢር ገጽ 212 ፣ ዕብ 115 ፣ ኄኖክ 41161)፡፡ አንዳዶቹ አባቶች ወደገነት ከተነጠቁ በኋላ የሀገሪቱን መልካምነት አይተው የተመለሱ ይገኙባቸዋል (2 ቆሮ 124)፡፡ ከገነትም ከተመለሱ በኋላ በፊት ይሠሩት ከነበረው መልካም ሥራ ይበልጥ ለመሥራት ይነሣሳሉ፡፡ በመሆኑም ይራባሉ፣ ይጠማሉ፣ ዓለም ሊሸከመው የማይችለውን ከባድ ሸክም ሁሉ ይሽከማሉ፡፡ ከሞትም በኋላ በሕይወተ ሥጋ ሳሉ ወደአዩት ሀገር በክብር ይሄዳሉ፡፡ አንዳዶቹም አባቶች በሃማኖት ጸንተው የብዙ ገድል ባለቤቶች ይሆኑና በዕረፍታቸው ጊዜ ወደዚሁ ሀገር ይገባሉ፡፡

ገነት ማለት ምን ማለት ነው? ገነት ማለት የተክል ቦታ ፣ ብዙ ዛፍና ዕንጨት ያለበት ፣ ሽቱና ቅመማ ቅመም የሚበቅለበት ፣ ውሀ የሚገባበት የተከለለ ቦታ ማለት ነው (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ገጽ 313)፡፡ ከዚህም ሌላ መጻሕፍት ስለገነት ብዙ ስያሜ ሰጥተዋት እናጋኛለን፡፡ ይህም ገነት ዕፁት (መሐ 412) ፣ ገነተ አቅማሕ (መጽሐፈ ምሥጢር ገጽ 219) ፣ ገነት ርውይት (በውሀ የረካች) (ሲራ 2430)፣ ገነተ ጽጌ (አባ ገብረ ማርያም) ፣ ገነተ ተድላ (አክሲማሮስ ገጽ 156)፣ ገነተ ትፍሥሕት (አክሲማሮስ ገጽ 157)፣ ገነተ እግዚእ ((አሪ ዘፍ 1310) ፣ ገነተ ኅሩያን ደቂቅ (ደራሲ) ፣ ምድረ ገነት (ድጓ ገጽ 407 ፣ ዕዝ ሱቱ 42) ፣ ኤዶም ገነት (ድርሳነ ማሕየዊ ገጽ 110) ፣ ሰማይ ሣልሲት (2 ቆሮ 12:2)፡፡ ገነት ኤዶም (መጽሐፈ ምሥጢር ገጽ 212)፡፡ የስሟ ትርጓሜ ይህ ይሁን እንጅ ገነት መልካም የሠሩ የሚኖሩባት ፣ ክፉ የሠሩ የሚከለከሉባት መንፈሳዊ ሀገር ናት፡፡

ገነት ዬትትገኛለች?

ገነት እንደመጽሐፈ ቀሌምንጦስ አገላለጽ ከቀራንዮ በላይ በአየር ላይ ትገኛለች፡፡ ገነት ከቀራንዮ በላይ ትገኛለች ስንል ከቀራንዮ ጋር የተያያዘች ሳትሆን በህዋ ላይ በመንሳፈፍ ያለችና መሬትነት ያላት ሀገር ናት (አክሲማሮስ ገጽ 73፣መጽሐፈ ቀሌምንጦስ)፡፡ ይህችም ገነት የመጀመሪያው ሰው አዳም በቀራንዮ በማእከለ ምድር ከተፈጠረና ለእንስሳት ሁሉ ስም ካወጣ በኋላ ሊኖርባት የተሰጠችው ቦታ ናት (ኩፋ 49 ፣ ዕዝ ሱቱ 16 መቃ ቀዳ 2714 ፣ አቡሻክር ፣ ጊዮርጊስ ወልደ ሐሚድ)፡፡ አዳም በምድር መካከል ተፈጠረ የሚለው ቃል የሚያስረዳው በዚህ በቀራንዮ ላይ አራቱ የዓለም ክፍሎች የሚገናኙ መሆኑን ነው፡፡ በዚህ ቦታ ላይ ብዙ ነገር ተከናውኖበታል፡፡ ይህም አዳም ወደገነት በሚገባበት ዕለት እንስሳትና መላእክት ተሰባስውበታል፡፡ የኖኅ ልጅ ሤም የአዳም አባታችንን ዐፅም ቀብሮበታል፡፡ መልከጼዴቅ የልዑል እግዚበሔር ካህን ሆኖ ተቀምጦበታል፡፡ አብርሃም አባታችን ይስሐቅ ልጁን ለአግዚአብሔር መሥዋዕት አድርጎ አቅርቦበታል፡፡ ጌታችንም ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዐርብ የሰው ዘርእ ለማዳን ተሰቅሎበታል (መዝ 7312)፡፡ ገነት አራት አቅጫዎችና ሦስት መንገዶች ያሏት ሀገር ናት፡፡ አንደኛው መንገድ በጎልጎታ፣ ሁለተኛው በደብረ ዘይት ፣ ሦሰተኛው በደብረ ሲና ላይ ነው፡፡ በገነት ክረምትና በጋ አይፈራረቁባትም፡፡ በውስጧም የሚገኙ እንጨቶች ያበራሉ (ኄኖክ 821)፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በዚህ ዓለም ያሉ ረኀብ ፣ ጥም ፣ ሕማም ፣ ሞት ፣ ማጣት ማግኘት የለባትም፡፡ ገነት የምስጋና ፣ የደስታ ፣ የእውነትና የቅድስና ቦታ ብቻ ናት (መጽሐፈ ቀሌምንጦስ)፡፡

ገነት በመጽሕፍ ቅዱስ

በመጽሐፍ ቅዱስ ኤድን የሚለው ቃል ከ17 ጊዜ በላይ ተጠቅሶ ይገኛል፡፡ ከጥቅሶቹም ውስጥ አንዳዶቹ ኤድን ስለሚባል ሀገር የሚገልጹ ሲሆን አንዳዶቹ በኤድን ስለአለች የተክል ቦታ ይገልጻሉ፡፡ ኤድን የቃሉ ትርጉም ደስታ ፣ ለም ቦታ ፣ መልካም መዓዛ ያለበት አካባቢና ሰፊ ሜዳ ማለት ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ገነት ያለችና የምትኖር ሀገር ናት፡፡ በመሆኑም መጽሐፍ ቅዱስ ስለገነት ስም ፣በውስጧ ስለሚገኙ ዕፀዋትና ወንዞች ፣ አዳምና ሔዋን ፣ ገነትን ስለሚጠብቅ መልአክ (ኪሩብ/ሱራፊ) ይገልጻል፡፡ ይህም እንደሚከተለው ይገለጻል፣ አንቺ የገነት የሕይወት ውሃ ጉድጓድ ከሊባኖስ የሚፈስ ወንዝ ነሽ (መኃል 415)፡፡ እግዚአብሔር አምላክም በምሥራቅ በኤድን ገነትን ተከለ፤ የፈጠረውንም ሰው ከዚያው አኖረው (ኦሪ ዘፍ 28)፡፡ ወንዝም ገነትን ያጠጣ ዘንድ በኤድን ይወጣ ነበር፤ ከዚያም ከአራት ይከፈል ነበረ (ኦሪ ዘፍ 210)፡፡ በእግዚአብሔር ገነት በኤድን ነበርህ የከበረ ዕንቍስ ሁሉ፥ ሰርድዮን፥ ቶጳዝዮን፥ አልማዝ፥ ቢረሌ፥ መረግድ፥ ኢያስጲድ፥ ሰንፔር፥ በሉር፥ የሚያብረቀርቅ ዕንቍ፥ ወርቅ፥ ልብስህ ነበረ፤ የከበሮህና የእንቢልታህ ሥራ በአንተ ዘንድ ነበረ፤ በተፈጠርህበት ቀን ተዘጋጅተው ነበር (ሕዝ 2813)። በክብርና በታላቅነት በኤድን ዛፎች መካከል ማንን መስለሃል? ነገር ግን ከኤድን ዛፎች ጋር ወደ ታችኛው ምድር ያወርዱሃል (ሕዝ 3118)፡፡ አዳምንም አስወጣው፤ ወደ ሕይወት ዛፍ የሚወስደውንም መንገድ ለመጠበቅ ኪሩቤልንና የምትገለባበጥ የነበልባል ሰይፍን በኤድን ገነት ምሥራቅ አስቀመጠ (ኦሪ ዘፍ 324)። ኢየሱስም፦ “እውነት እልሃለሁ፥ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትሆናለህ” (ሉቃ 2343)፡፡

እነዚህ ሁሉ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች የገነትን መኖርና የአዳምን ከገነት መሰደድ ይገልጻሉ፡፡ ሆኖም መጽሐፍ ቅዱስ ገነት የምትገኝበትን ኤድን ዬት አካባቢ እንደሆነች በግልጽ አያመለክትም፡፡ ነገር ግን መጽሐፈ ኩፋሌ ለእግዚአብሔር ሦስት የተቀደሱ ቦታዎች እንዳሉት ይገልጻል (ኩፋ 532)፡፡ እነዚህም ቦታዎች፣ አንደኛዋ ደብረ ሲና ፣ ሁለተኛዋ ደብረ ጽዮን ፣ ሦስተኛዋ ገነት እንደሆኑና ሦስቱንም አንጻራዊ አድርጎ ፈጥሯቸዋል ይላል (ኩፋ 98)፡፡ አንጻራዊ አድርጎ ፈጥሯቸዋል የሚለውን ቃል ስንመለከት ደብረ ሲና በምዕራብ ፣ ደብረ ጽዮን በመካከል ፣ ገነት በምሥራቅ እንደሆኑ እንረዳለን፡፡ ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ምልከታ እንደሚያሳየው ገነት ከደብረ ጽዮን በምሥራቅ በኩል ባለው አካባቢ ትገኛለች ማለት ነው፡፡ ገነት ከከነዓን ምድር በስተምሥራቅ ሁና ከደብር ቅዱስ ጋር ጎረቤት መሆኗ ነው፡፡

ደብር ቅዱስ

ደብር ቅዱስ (በአተ መዛግብት) (መጥርዮን) አዳምና ሔዋን ከገነት ከተሰደዱ በኋላ ይኖሩበት የነበረ ቦታ ነው (አቡሻክር)፡፡ ይህ ተራራ የገነት አጎራባች ሲሆን በዚህ ቦታ ይኖሩ የነበሩ አባቶች ሁሉ ገነትን አሻግረው ይመለከቷት ነበር፡፡ ይህም ማለት ገነት ለደብር ቅዱስ የቀረበች ቦታ ናት ማለት ነው፡፡ ደብር ቅዱስ በአሁኑ ጊዜ ኤርሞን (ሄርሞን) የሚባለው ተራራ ነው፡፡ ይህም ተራራ በ3ቱ ሀገሮች በእስራኤል ፣ በሶርያና በሊባኖስ መካከል የሚገኝ በበረዶ የተሸፈነ ተራራ ነው፡፡ ኤርሞን ወይም ሄርሞን ዋሻ የበዛበት ተራራ ሲሆን ትርጓሜው ደብረ መሐላ (የመሐላ ተራራ) ማለት ነው፡፡ የዚህም ተራራ ጫፍ ሰርዲን ይባላል፡፡ በዚህ በሰርዲን ጫፍ ላይ የሴት ልጆች እስከ ኖኅ ዘመን ድረስ ይኖሩበት ነበር (የመጽሐፈ ኅኖክ አንድምታ)፡፡ እነዚህም የሴት ልጆች ወደደብር ቅዱስ ተራራ ግርጌ ወደሚገኝ ምድረ ፋይድ ወደተባለ ቦታ ተጠቃለው ወርዋል (አቡሳክር ፣ ጊዮርጊስ ወልደ ሐሚድ)፡፡ ምድረ ፋይድ ማለት ምድረ ኀሣር ወመርገም ፣ ምድረ ድንፄ ወረዓድ ማለት ነው (የወንጌል አንድምታ ገጽ 19)፡፡ ይህም መከራ የሚፈራረቅበት ፣ ቀይና ጥቁር የሚወለድበት ፣ ሀብታምና ድሀ የሚኖርበት ቦታ ማለት ነው፡፡

የገነት ወንዞች

አራቱ የገነት ወንዞችን በተመለከተ የዘመናዊ ጸሐፊዎች የተለያየ ሐሳብ ሰጥተዋል፡፡ ከዚህም የሐሳብ መለያየት ያደረሳቸው የወንዞቹ ተራርቆ መገኘትና የፍሰት አቅጣጫቸው ነው፡፡ አንደኛው ኤፍራጥስ የተባለው ወንዝ ከቱርክ ተራራማ ሥፍራ ፈልቆ ከላይ የቱርክንና የሦርያን ደምበር ፣ ከታች የሦርያንና የኢራቅን ደምበር በማካለል ከጤግሮስ ወንዝ ጋር ተቀላቅሎ ወደፋርስ ባሕረሰላጤ ይገባል፡፡ የጤግሮስም ወንዝ ከቱርክ ተራራማ ቦታ ፈልቆ በባቢሎን (ኢራቅ) አድርጎ በመጨረሻ ከኤፍራጥስ ወንዝ ጋር በመደባለቅ ወደባሕረሰላጤው ይገባል፡፡ ኤፌሶን የታባለው ወንዝ በአሁኑ ጊዜ ውሀ ይዞ የሚፈስ ወንዝ ሆኖ አልተገኝም፡፡ ሆኖም በወንዙ ላይ ጥናት ያደረጉ ሰዎች እንደሚሉት ይህ ወንዝ ከመዲና አጠግብ ከሚገኝ ሂጃዝ ከሚባል ተራራ ተነሥቶ የዐረብያን ምድር አቋርጦ በኵየት ሰሜን ምሥራቅ አድርጎ ወደባሕረሰላጤው ይገባ እንደነበር ያስረዳሉ፡፡ በአሁኑ ጊዜ ድሮ ይሄድበት የነበረውን ደረቅ ወንዝ በማጥናት መጽሐፍ ቅዱስ ኤፌሶን የኤውላጥን ምድር ይከባል ከሚለው ሐሳብ ጋር ለማጣጣም ጥረት አድርገዋል፡፡ ግዮን የተባለው ወንዝ የሀገራችን ትልቁ ወንዝ ነው፡፡ ይህም ወንዝ በመጽሐፍ ቅዱስ የኢዮትዮጵን ምድር ይከባል (ኦሪ ዘፍ 213) እንደተባለው በርካታ የሀገራችንን አካባቢዎች በማዳረስ የሱዳንና የግብፅ ሀገሮች አቋርጦ ሚዲትራንያን ባሕር የሚገባ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ሊቃውንት አራቱ ወንዞች በህልውናቸው እንዳሉና እያንዳደቸው ልዩ አገልግሎት እንደሚሰጡ ይጽፋሉ፡፡ ይህም መልካም ሥራ የሠሩ ምእመናን ወንዞችን በርስትነት እንደሚወርሷቸው ነው፡፡ አናደኛው ወንዝ ኤፌሶን ፈለገ ሐሊብ ነው፤ ርስትነቱም ለሕፃናት ነው፡፡ ሁለተኛው ወንዝ ግዮን ፈለገ ወይን ነው፤ ርስትነቱም መልካም ሥራ በመሥራት ሕይወታቸውን የሚያሳልፉ ሰዎች ርስት ነው (በጾም ፣ በምጽዋትና በጸሎት የሚኖሩ ምእመናን ይውርሱታል)፡፡ ሦስተኛው ወንዝ ጤግሮስ ፈለገ መዓር ነው፤ ርስትነቱም ነገርን የሚታገሡ ሰዎች ነው (የወንድማቸውን ጥላቻ ታግሠው ፣ ክፉውን ነገር በመልካም ነገር ለውጠው የሚኖሩ ሰዎች ይወርሱታል)፡፡ አራተኛው ወንዝ ኤፍራጥስ ፈለገ ዘይት ነው፤ ርሰትነቱም ደማቸውን ያፈሰሱ ሰማዕታተ ክርስቶስ ርስት ነው (ስለቤተ ክርስቲያን ደማቸውን ያፈሰሱ ሰማዕታት ይወርሱታል) (የወንጌል አንድምታ ትርጓሜ ገጽ 52)፡፡

ገነት በዘመናዊ ጸሐፊዎች

የዘመናዊ ጸሐፊዎች ገነትን በምድር የነበረችና በማየ አይኅ ጊዜ የጠፋች ሀገር ያደርጓታል (የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 241)፡፡ በአሁኑ ጊዜ ኤድን የሚባለው ሀገር የመሶፓታሚያና የአካባቢው አገሮችን (አሦር ፣ አካድ ፣ ባቢሎን (ኢራቅ)ና ፋርስ (ኢራን) ያጠቃልላል ይላሉ፡፡ አንዳዶቹ ኤድን ገነት በደቡብ መሶፓታሚያ ማለትም በደቡብ ኢራቅና ኢራን ደንበር የጤግሮስና የኤፍራጥስ ወንዞች ወደባሕረሰላጤው ከሚገቡት ላይ ነበረች ይላሉ፡፡ አንዳንዶቹ ተመራማሪዎች ኤድንን በመካከል ያደርጉና በሰሜን አርመንን ፣ በሰሜን ምሥራቅ አዘርባይጃንን ፣ በሰሜን ምዕራብ ቱርክን ፣ በምሥራቅ የካስፒያን ባሕርን ፣ በምዕራብ ሦርያን፣ በደቡብ ምዕራብ ኢራቅን፣ በደቡብ ምሥራቅ ኢራንን አድርገው የኤድንን የድሮ ካርታ ያስቀምጣሉ፡፡ አንዳዶቹ ጸሐፊዎች ትክከለኛ የገነት ቦታ ሊባኖስ የሚባለው ሀገር ነው ይላሉ፡፡ ምክንያታቸውም ነቢዩ ሕዝቅኤል ስለጢሮስና ስለኤድን ገነት የተናገረው የትንቢት ቃል ነው (ሕዝ 28:11-19)፡፡ ከቤተ ክርስቲያን ጸሐፊዎችም ሁለት አይነት ገነቶች እንዳሉ ይገልጻሉ (አንዷ ምድራዊት ፣ ሁለተኛዋ ሰማይዊት)፡፡ ምድራዊቷ ገነት አዳምና ሔዋን የነበሩባት የዛሬዋ መሶፓታሚያ እንደሆነች ያምናሉ፡፡ ሰማያዊቷ ገነት የነፍሳት ማደሪያና ክርስቶስ እስኪመጣ ድረስ የነፍሳት መቆያ ሀገር እንደሆነች ጽፈዋል (ሐና ማርቆስ (1996 ገጽ 41-42)፡፡

የቤተ ክርስቲያን ምንጮችንና የዘመናዊ ምንጮችን ስንመለከት የተራራቀ ሐሳብ አላቸው፡፡ የቤተ ክርስቲያን ምንጮች እንደሚያስሩዱት ገነት ልዕልት ናት (ከፍ ያለች)፤ ምድርም ዝቅ ያለች ናት (ሕዝ 3118) ፣ ሥውርና የንጹሓን መኖሪያ ፣ የነፍሳት ማደሪያ ናት ይላሉ፡፡ በተጨማሪም በዚህ ዓለም ሰዎች ዐይን መታየት አትችልም የሚል ጠንካራ እምነት አላቸው፡፡ በውስጧ ስለሚገኙት ወንዞች ሲናገሩ ወንዞቹ የገነትን ዕፀዋት ካጠጡ በኋላ ወደዚህ ዓለም መጥጠው የዓለምን አካቢቢዎች ያጠጣሉ ይላሉ፡፡

ገነት በቅዱስ ያሬድ አስተምህሮት

በቅዱስ ያሬድ አስተምህሮ ገነት ያለችና የምትኖር ፣ የንጹሓን ማደሪያ ናት፡፡ ቅዱሳን ሰዎች በሩቅ ሁነው እንደሚመለከቷትና አገራቸው እንደሆነች እንደሚገነዘቡ ይገልጻል፡፡ ይህም፣እምርኁቅስ ርእይዋ ወተአምኅዋ ወአእመሩ ከመ ሀገሮሙ ይእቲ ገነት ይእቲ ነቅዐ ገነት አዘቅተ ማየ ሕይወት ማኅደር ለንጹሓን (ከሩቅ ሁነው አዩአት አይተውም ሰላም አሏት አገራቸውም እንደሆች አወቁ ገነት ናት የሕይወት ምንጭ ናት የንጹሓን ማደሪያ ናት) (ጾመ ድጓ ገጽ 110)፡፡ የገነት ምድር አፈጣጠርንም ሲያስረዳ ፣ እምሰማይ አውርደ ምድረ ገነት ዘሰይሰቅያ ለምድር በቃለ ሰላም (በፍቅር ምድርን የሚያጠጣት አምላክ የገነትን ምድር ከሰማይ አውረደ (ድጓ ገጽ 407)፡፡ አዳም በገነት ከኖረ በኀላ ከፈጣሪው ጋር በመጣላቱ ከገነት በተሰደደ ገዜ እንዳዘነ ፣ እንደተከዘና ንስሓ እንደገባና በኋላም ወደገነት እንደተመለሰ ሲገልጽ፣ ተማኅለለ አዳም ቀዳሜ ኵሉ ፍጥረት ወተነሢሖ ገብዐ ውስተ ገነት (የፍጥረት ሁሉ መጀመሪያ አዳም ምህላ ይዞ ንስሓም ገብቶ ወደ ገነት ተመለሰ) ብሏል (ድጓ ገጽ 420)፡፡

እግዚአብሔር ለወዳጆቹ በገነት መልካም ነገር እንደሚያደርጋለችው ሲጽፍ፣ ዘዐይን ኢርእየ ወእዝን ኢሰምዐ ዘአስተዳለወ ለእለ ያፈቅርዎ ኀበ አልቦ ደዌ ወአልቦ ሐማም ኀበ ኢመውቱ እምዝ ዳግመ ገነት ተርኅወ አክሊል ተደለወ ፍኖት ረትዐ ወፃማ ኀለፈ (እግዚአብሔር ለሚውዳቸው ያዘጋጀው ዐይን ያላየው ጀሮ ያልሰማው ነው ፣ ደዌ የሌለበት ሕማምም የሌለበት ነው ፣ ዳግመኛ የማይሞቱበት ነው ፣ ገነት ተከፈተ ፣ አክሊል ተዘጋጀ ፣ መንገድ ተጠረገ ፣ ድካምም አለፈ (ድጓ ገጽ 101) ብሏል፡፡ ገነት በዚህ ዓለም ከሚገኙ ተራሮች ከፍ አንደምትልና በርቀት የምትታይ መሆኗን ሲገልጽ፣እንተ ታስተርኢ እምአርስተ አድባር ርኁቅ ጻድቃን ኪያሃ አብደሩ እምወርቅ ሀገረ ክርስቶስ ሐዳስ ንድቅ ወበውስቴታ የኀድር ጽድቅ (ከታራሮች በላይ ከርቀት የምትታይ ጻድቃን ከወርቅ ይልቅ እሷን ወደዱ ፣ አዲስ ሕንፃ የክርስቶስ ሀገር ናት፤ በውስጧም እውነት ያድራል) ብሏል፡፡ ገነት በናግራን (ዐረብያ) አካባቢ እንደምትገኝ ሲገልጽ፣በሐኪ ኦ ዐባይ ሀገር ሀገረ ናግራን ሀገረ ነጐድጓድ ሀገረ እግዚአብሔር እንተ ተሰመይኪ ገነተ (አንች ትልቅ ሀገር የነጐድጓድ ሀገር ፣ የእግዚአሔር ሀገር ፣ ገነት ተብለሽ የተጠራሽ ናግራን (ናጅራን) ሆይ ሰላምታ ይገባሻል) ብሏል፡፡ ከዚህ ላይ እንተ ተሰመይኪ ገነተ የሚለው ሐረግ ገነት በናግራን አካባቢ መሆኗን ያመለክታል፡፡

ቅዱስ ያሬድ በገነት ስለሚገኙ አራቱ ወንዞች ሲጽፍ፣ሀገር ቅድስት ሀገሩ ለንጉሥ ዐቢይ አፍላገ ሕይወት በየማና ወአፍላገ ሕይወት በፀጋማ ይውኅዝ ሐሊብ ወመዓር ውሉደ ሰላም የዋሃን ይበውኡ ውስቴታ (የገናና ንጉሥ ሀገር ልዩ ናት ፣ የሕይወት ወንዞች በቀኟና በግራዋ ናቸው ፣ በውስጧም ወተትና መዓር ይፍሳል ፣ የሰላም ልጆች የዋሃን ከውስጧ ይገባሉ (ድጓ ገጽ 140) ብሏል፡፡ ገነት የዕረፍት ቦታና የቅዱሳን ነፍሳት ማረፊያ እንደሆነችም ሲገልጽ ፣እስመ ለክሙ ተርኅወ ገነት ወተተክለ ዕፀ ሕይወት ኀበ ማየ ዕረፍት ውስተ ገነተ ትፍሥሕት ህየ ይበውኡ ነፍሳቲሆሙ ለጻድቃን (ገነት ተከፈተላችሁ፣ የደስታ ቦታ ከምትሆን ከገነትም የሕይወት ዛፍ ተተከለላችሁ እኮ) (ድጓ ገጽ 109) ባሏል፡፡

የገነት መዘጋትና መከፈት

አዳም የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ባለመጠበቁ ገነት ተዘግታ ስትኖር በጌታችን ሞትና ትንሣኤ መከፈቷ የሁሉም ክርስቲያን እምነት ነው፡፡ በመሆኑም የገነትን መዘጋትና መከፈት ፣ የአዳምን ወደቀደመ ቦታው መመለስ የሚገልጹ ብዙ ድርሳናት ተጽፈዋል፡፡ ከእነዚህም ጥቂቶቹ እንደሚከተለው ቀርበዋል ፣ ፈቀደ እግዚእ ያግዕዞ ለአዳም ኅዙነ ወትኩዘ ልብ ወያግብኦ ኀበ ዘትካት መንበሩ (ጌታ ልቡ ያዘነና የተከዘ አዳምን ነጻ ያወጣው ዘንድና ወደቀድሞው ቦታው ይመልሰው ዘንድ ወደደ)፡፡ ተፈሥሒ ኦ ቤተ ልሔም ሀገሮሙ ለነቢያት እስመ በኀቤኪ ተወልደ ክርስቶስ ዳግማይ አዳም ከመ ያግብኦ ለአዳም ቀዳሚ ብእሲ እምድር ውስተ ገነት (የነቢያት አገራቸው ቤተ ልሔም ሆይ ደስ ይበልሽ ሁለተኛው አዳም ክርስቶስ ከአንች ዘንድ ተወልዷልና የመጀመሪያው ሰው አዳምን ከምድር ወደገነት ይምልሰው ዘንድ)፡፡ በእንተ ሔዋን ተዐፅወ ኆኅተ ገነት ወበእንተ ማርያም ድንግል ተርኅወ ለነ (በሔዋን ምክንያት የገነት ደጅ ተዘጋ ዳግመኛ በድንግል ማርያም ተከፈተልን)፡፡ ወገብረ ሰላመ ማእከሌነ በመስቀሉ ወበትንሣኤሁ ቅድስት አግብኦ ለብእሰ ዳግመ ውስተ ገነት (ለእኛም እርግማን አጠፋልን፤ በመካከላችንም ሁኖ በመስቀሉ አስታረቀን፤ በልዩ ትንሣኤውም ሰውን ዳግመኛ ወደ ገነት መለሰው) (ቅዱስ ኤፍሬም)፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ አመ ተለዐልከ እምድኅረ ፄዋ ለገነተ ጽድቅ ዘእደ ሱራፊ ዐፀዋ ቤዛ ኀጥኣን ኲሎሙ ደምከ አርኀዋ (ኢየሱስ ክርስቶስ ከምርኮ በኋላ ወደላይ ከፍ ከፍ ባልህ ጊዜ የኀጥኣን ሁሉ መድኃኒት ደምህ የሱራፊ እጅ የዘጋትን ገነት ከፈታት) (አባ ዘሐዋርያት)፡፡ወበውእቱ ደመ ርግዘቱ አርኀወ አናቅጸ ገነት ፫ተ ዘተዐፅዉ በእደ ኪሩቤል ወሱራፌል ዘቦሙ ሰይፈ እሳት ወኲይናተ እሳት ወበትረ እሳት (በዚህም በመወጋቱ በፈሰሰው ደም የእሳት ጦርና የእሳት ሰይፍ በያዙ በኪሩቤልና በሱራፌል እጅ የተዘጉ ሦስቱን የገነት በሮች ከፈተልን (ድርሳነ ማኅየዊ ገጽ 110 ፣ ሃይ አበ ሳዊሮስ ገጽ 339)፡፡ በመስቀሉ አርኀወ ገነተ (በመስቀሉ ገነትን ከፈተ) (ጾመ ድጓ ገጽ 73)፡፡

ሁሉም የቀረቡት ማስረጃዎች የሚያሳዩት ገነት በአዳም ጥፋት ምክንያት ተዘግታ ከኖረች በኋላ በክርስቶስ መስቀል ዳግመኛ መከፈቷን ነው፡፡

ማጠቃለያ

ገነት ዬት ትገኛለች የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ የዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ በዙ ምንጮችን ለማየት ሞክሯል፡፡ ከምንጮችም ስለገነት አራት አይነት ሐሳቦች እንዳሉ ተመልክቷል፡፡ አንደኛው አይነት ሐሳብ ገነት ከመሬት በላይ በአየር ላይ ያለች ሀገር ሁና ከመሬት በጣም የራቀች እንደሆነች ይገልጻል፡፡ ሁለተኛው ሐሳብ ገነት በመሬት ላይ ነበረች ነገር ግን በማየ አይ ጊዜ እግዚአብሔር ወደ ሰማይ አሳርጓታል የሚል ነው፡፡ ሦስተኛው ሐሳብ ገነት በማየ አይኅ ጊዜ እንደጠፋችና የነበረችበትም አካባቢ በመሶፓታሚያ አንደነበረና በአሁን ጊዜ ሀገሩ በሌላ ስም እንደሚጠራ የሚስረዳ ነው፡፡ አራተኛው ገነት ከመሬት ሁና ነገር ግን ከፍ ካለ አካባቢ ትገኛለች፡፡ ከፍ ባለ ቦታም በመገኘቷ ሰማይ ትባላለች የሚል ሆኖ ይገኛል፡፡ ገነት በሰማይ ናት ለሚለው ጥያቄ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሲመልስ ገነት በሰማይ ያለች ብትሆን ኖሮ መልአኩ ለጥበቃ ባልተሾመ ነበር ብሏል፡፡ ምክያቱም ሰው ወደሰማይ መውጣት ባለመቻሉ ነው(መጽሐፈ ምሥጢር)፡፡ የቅዱስ ያሬድም ድርሰት ገነት ከተራሮች በላይ በርቀት እንደምትታይና ጻድቃን እርሷን ለማግኘት ጥረት እንደሚያደርጉ ይገልጻል፡፡ ኄኖክም የገነትን አቅጣጫ ሲያመለክት፣ ወደኤርትራ ባሕር ሄድሁ፤ ከዚያም የራቅሁ ሆንሁ፤ ዙጡኤል በሚባል መልአክ በላይ አልፌ ሄድሁ፤ በቸርነቱም ወደምትወረስ ገነት መጣሁ ብሏል(ኄኖ 819-22)፡፡

የገነት መገኛ ግልጽ ባይሆንም በርካታ ማስረጃዎች እንደሚያመለክቱት ገነት ከሰማይ ሳትሆን ክምድር ላይ ናት የሚለውን ሐሳብ ያጠናክራል፡፡ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሣኤም አላማ የተዘጋች ገነትን ለመከፈትና አዳምን ወደቀደመ ቦታው ለመመለስ በመሆኑ ገነት በማየ አይኅ ጠፍታለች የሚለው ሐሳብ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ሰለዚህ ስለገነት መመራመር የሚፈልግ ሁሉ ገነት እግዚአብሔር በሥዉር ያስቀመጣትና ከመታየት የሠወራት ሀገር መሆኗን ተቀብሎ እንደቅዱሳን ሰዎች መልካም ሥራ በመሥራትና ከክፉ ነገር በመራቅ ገነትን መውረስ እንደሚቻል ማመኑ የተሻለ ይሆናል፡፡

ምንጭ

______

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , | 1 Comment »

የኢትዮጵያ ሕያው ዓብያተ ክርስቲያናት | ድንቅ ፎቶዎች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 14, 2017

ፎቶ አነሳሱ እጹብ ድንቅ ነው። ምናለ እንደዚህ ማንሳት ብችል?!

ፎቶዎቹ በጋርዲያን የጉዞ ክፍል በታተሙበት ዕለት በተወዳጅነታቸው የመጀመሪያውን ቦታ ይዘዋል።

አንባቢዎች ከሰጧቸው አስተያየቶች መካከል፦

+ „ተራራ አንቀሳቃሽ እምነት”።

+ „በላሊበላ ምክኒያት ኢትዮጵያን እወዳታለሁ”።

+ ዋውው! እንደዚህ የመሳሰሉ ቤተክርስቲያናት እንዳላቸው አላውቅም ነበር፤ አንድ ቀን እሄዳለሁ።

+ የሚያምር እና የሚስብ።

+ እነዚህን ድንቅ ቦታዎች ተነስቼ እንደመጎብኘት እዚህ ቁጭ ብዬ ፎቶዎቹን አደንቃለሁ፡ በዚህም አፍራለሁ።

Ethiopia’s Living Churches – In Pictures

As one of the first countries to adopt Christianity, Ethiopia has a legacy of churches and monasteries, built on hilltops or hewn out of cliff faces, as well as vibrant traditions of worship. These are celebrated in a lavish book, Ethiopia: The Living Churches of an Ancient Kingdom

ምንጭ

______

Posted in Ethiopia, Faith, Photos & Videos | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

ቅዱስ ምካኤል ወዳጅ ነህ ለሁሉ፤ ዛሬም ቆመሃል በኪዳንህ ላሉ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 21, 2017

እርጉም የዲያብሎስ ልጆች በሴቶቻችን፣ በህፃናቶቻችንና በመላው ሕዝባችን ላይ ዘምተዋል፤ ማን ያየናል፣ ማን ያውቅብናል በማለት ሌት ተቀን ይፈታተኗቸዋል፤ ዲያብሎስን ድል የነሣህ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ! የምስጋናን መሥዋዕት የምታዘጋጅ አንተ ነህና ጠላት ዲያብሎስ ተረማምዶ በእደ ፃዕረ ሞት ወገኖቻችንን እንዳያፍን በአፋቸው ላይ ጥበቃህን አጠንክር።

የቅዱስ ሚካኤል አምላክ ሆይ! በአርአያህ በአምሣልህ የፈጠርከን ሕዝቦችህን ሁሉ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ሠውረን ለዘላለሙ አሜን።

ኅዳር ፲፪ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ታላቅ በዓል

ሚካኤል ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ ሚመኑከመኤልአምላክ ማለት ሲሆን በአንድነት ሲነበብ መኑ ከመ አምላክ (እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው) ማለት ነው፡፡ ይህ ታላቅ መልአክ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራዕዩ ‹‹በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ›› ብሎ ከተናገረላቸው መላእክት ውስጥ የሚመደብ ሲሆን የሰባቱም ሊቃነ መላእክት አለቃ እንዲሆን እግዚአብሔር መርጦ ሹሞታል፡፡ ይህ ታላቅ መልአክ ያደረጋቸው የሠራቸው እጅግ ብዙ የሆኑ ተአምራት አሉት፡፡

ስለዚህ ስለ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ክብር፤ ጠባቂነትና አማላጅነት ከአባቶቻቸው የተማሩትን በኑሮአቸው ያዩትን አባቶቻችን ጽፈዋል፡፡ ስለ ቅዱስ ሚካኤል ከጻፉት አባቶች መካከል የተወሰኑትን ለመጥቀስ ያክል፡

  • + ዮሐንስ አፈወርቅ
  • + ኤዎስጣቴዎስ ዘአንፆኪያ
  • + ቅዱስ መቃርዮስ
  • + ቅዱስ ያሬድ
  • + አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
  • + የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ አባዲማቴዎስ ናቸው፡፡

እኛም የአባቶቻችንን አንደበት አንደበታችን አድርገን በኅዳር 12 ክቡር ገናና የሆነ ቅዱስ ሚካኤል ካደረጋቸውና ከሠራቸው ብዙ ተአምራት ውስጥ የተወሰኑትን በመልአኩ ተረዳኢነት እንዲህ ብለን እንናገራለን አንጽፋለን፡፡

ንግስት ክሌዎፓትራ ‹‹ሳተርን›› ለሚባለው ጣዖት የሠራችው ቤተ ጣዖት በእስክንድርያ ነበር፡፡ ይህ ቤተ ጣዖት እስከ እስክንድርያው ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ /312 – 326/ ዘመን ድረስ ነበር፡፡ እለ እስክንድሮስ ሊያጠፋው ሲነሣ ሕዝቡ ከልቡ ገና የአምልኮ ጣዖት ስላልጣፋ 18 ፓትርያርኮች ያልነኩትን አንተ ለምን ታፈርስብናለህ ብለው ተቃወሙት፡፡ እለ እስክንድሮስም ሕዝቡን መክሮና አስተምሮ የሳተርን በዓል ይውልበት በነበረው ዕለት የቅዱስ ሚካኤልን በዓል እንዲያከብሩ አውጆ ቤተ ጣዖቱንም በቅዱስ ሚካኤል ስም ሰይሞ ቤተክርስቲያን አደረገው፡፡ ከዚህ በኋላ በቅዱስ ሚካኤልም ስም አብያተ ክርስቲያናት መታነጽ ጀመሩ በዓሉ በዚህ ቀን እንዲከበር ተወስኗል፡፡

እንዲህም ሆነ የእግዚአብሔር ወዳጅ የሆነ ስሙ ዱራታዎስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፡፡ የሚስቱም ስም ቴዋብለት ነው፡፡ እነርሱም ሁልጊዜ ያለ ማቋረጥ የዚህን የከበረ መልአክ የሚካኤልን የበዓሉን መታሰቢያ ያረጉ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ በሀገር ውስጥ ችግር በሆነ ጊዜ ገንዘባቸው አለቀ፡፡ በዚህም የተነሳ ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ሚካኤል ለበዓሉ መታሰቢያ የሚያደርጉትን አጡ፡፡ ዱራታዎስም ሽጦ ለበዓሉ መታሰቢያ ያደርገው ዘንድ የእርሱን ልብስና የሚስቱን ልብስ ይዞ ወጥቶ ሄደ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በታላቅ መኮንን አምሳል ለዱራታዎስ ተገለጠለት፤ ቅዱስ ሚካኤልም ዱራታዎስን ወደ በጎች እንዲሔድና በእርሱ ዋስትና በአንድ ዲናር አንድ በግ እንዲወስድ አዘዘው፤ ሁለተኛም ወደ ዓሣ አጥማጅ ሔዶ አንድ ዓሣ እንዲወስድ አዘዘው፡፡ መልአኩም ወደ ቤት ሳይደርስ የዓሣውን ሆድ እንዳይቀድ አስጠነቀቀው፡፡ ወደ ባለ ስንዴም እንዲሔድና የሚሻውን እንዲሁ በእርሱ ዋስትና እንዲወስድ አዘዘው ዱራታዎስም ቅዱስ ሚካኤል እንዳዘዘው አደረገ፡፡

ወደ ቤቱም በተመለሰ ጊዜ በረከትን ሁሉ ቤቱ ተመልቶ አገኘው፤ እጅግም አደነቀ፤ የዚህንም የከበረ መልአክ የበዓሉን መታሰቢያ እንዳስለመደው አደረገ፡፡ የተራቡ ድሆችን ሁሉንም ጠርቶ መገባቸውና ወደ ቤታቸው አሰናበታቸው፡፡

ከዚህም በኋላ ለዱራታዎስና ለሚስቱ ቅዱስ ሚካኤል ለሁለተኛ ጊዜ ተገለጠላቸው ዱራታዎስንም የዓሳውን ሆድ እንዲሰነጥቅ አዘዘው፤ በሰነጠቀውም ጊዜ ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር በዓሳው ሆድ ተገኘ፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ዱራታዎስንና ቴዋብስታን እንዲህ አላቸው፡፡ ‹‹ከዚህ ዲናር ወስዳችሁ ለባለ በጉ ለባለ ዓሳውና ለባለ ስንዴው ዕዳችሁን ክፈሉ የቀረውም ለፍላጎታችሁ ይሁናችሁ፤ እግዚአብሔር አስባችኋልና በጎ ሥራችሁን መስዋዕታችሁን ምጽዋዕታችሁን በዚህ ዓለም አሳመረላችሁ፡፡ በኋላኛውም መንግስት ሰማያትን አዘጋጅቶላችኋል፡፡››

በአንድ ዘመን ብዙ ሰዎች ከግብፅ አውራጃ መጥተው ወደ ባሕር ማዶ ሄዱ፡፡ ከባሕሩም በደረሱ ጊዜ በመርከብ ላይ ተሳፍረው ከየብሱ ጥቂት በራቁና ወደ ባሕሩ መካከል በደረሱ ጊዜ ጽኑ ነፋስ ተነሳባቸው ለመስጠም እስኪ ደርሱ ድረስ፡፡

የማዕበሉ ሞገድ እየጨመረ እየጸና ከፍ አለ፡፡ ታላቅም ማዕበል መጥቶ ሊገለብጣቸው ደረሰ፡፡ ፍጹም ጥፋትና ክፉ ሞት እንደ መጣባቸው ባዩ ጊዜ ጽኑ ሐዘን ያዛቸው፡፡ የሚያድናቸው የሚያጽናናቸው አጥተው ተስፋ ቆረጡ፡፡ ያን ጊዜ እንዲህ ብለው ጮኹ፡፡

‹‹የመላእክት አለቃቸው ግሩም ገናና የምትሆን ሚካኤል ሆይ የተአምራትና የይቅርታ መልአክ ነህና፡፡ ልዑል ቸርነቱን የሚገልጥብህ መልአክ ሆይ! እግዚአብሔር ፍቅሩን የሚያስታውቅብህ መልአክ ሆይ ወደኛ ተመልከት እርዳን፡፡ የተጨነቅን እኛን አድነን፡፡ ከመጣብን ሞትና ጥፋት እንድን ዘንድ ስለኛ ወደ ፈጣሪህ ወደ ፈጣሪያችን ወደ እግዚአብሔር ለምንልን፡፡ አሁን የሞት መጋረጃ ዓይናችንን ሸፍኖታልና፡፡ ፍጹም የጥፋት ጥላንም አይተናታልና›› ብለው በፍጹም ልቦናቸው ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፡፡ በመርከብ ውስጥ ያሉት ሁሉ ጽኑ ለቅሶ እያለቀሱ መራራ እንባ እያፈሰሱ ጮኹ፡፡

ከባሕር ጽኑ ማዕበል ከሞት ያድናቸው ዘንድ ያን ጊዜ በዚያች ሰዓት እግዚአብሔር የልቦናቸውን ሐዘንና ልመናቸውን ሰማቸው፡፡ ያን ጊዜም ይገዳቸው ዘንድ ቸር መልአኩን ሚካኤልን ላከላቸው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ከሰማይ ወረደ መርከቡን በእጁ ይዞ ሳበው፡፡ በመርከቡ ውስጥ ያሉትንም ወደ የብስ አወጣቸው፡፡ በደኅናቸው ተሻገሩ፤ ክፉ ነገር ጥቂትስ ስንኳ ፈጽሞ አላገኛቸውም፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ገናና የሆነ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ልመናውና አማላጅነቱ ፈጽሞ ይጠብቀን፡፡ ከጽኑ ጠላት እጅ በክንፎቹ ጋርዶ ይሰውረን፡፡ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

ምንጮች

-ድርሳነ ሚካኤል ዘኅዳር

-መጽሐፈ ስንክሳር ዘኅዳር

-የሐመር መጽሔት 1993 ዓም መጋቢትና ሚያዚያ

ቅዱስ ምካኤል ወዳጅ ነህ ለሁሉ፤ ዛሬም ቆመሃል በኪዳንህ ላሉ። አሜን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ካኤል ሆይ ስለእኛ ስለሰው ልጆች በጌታ ፊት ቁምልን ምልጃና ጸሎትህ ተራዳእነትህ ጥበቃህ ለዘወትር አይለየን!! አሜን።

አስደናቂ አይደለም!? ላይ ያቀረብኩትን መልዕክት ከላኩ በኋላ፡ ቅዱስ ሚካኤልን ስጠራና ይህን ድህረገጽ ስከፍት፤ ያው የአምላኬ መልአክ በላዬ በራ፦

One Of The Biggest Alternative Media Networks In Italy Is Spreading Anti-Immigrant News And Misinformation On Facebook

______

Antivenom vs Venom | ሊቀ መላእክት ሚካኤል (Michael)በእነዚህ ገዳዮች ላይ ስይፉን ዘርግቶባቸዋል፤ ይገርማል ሁሉም ስማቸው በ “Mይጀምራል

  • ሜርከል (Merkel) ወደ ሞት እየሄደች ነው
  • ሙጋቤ (Mugabe) ወደ ሞት እየሄደ ነው
  • መንግስቱ (Mengistu) ወደ ሞት እየሄደ ነው
  • ሜይ (May) ወደ ሞት እየሄደች ነው
  • ማክሮን (Macron) ወደ ሞት እየሄደ ነው
  • ማንሰን (Manson) ሞተ
  • መሀመድ (Mohammad) ሞቷል
  • ሙስሊም (Muslim) እየሞቱ ነው

______

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

አቡነ ቴዎፍሎስ | ኮማንዶዎች በገመድ አንገታቸውን ሸምቀቅ አድርገው በማነቅ ከገደሏቸው በኋላ አስከሬናቸውን በርካታ ሬሳ በተጣለበት ጉድጓድ ውስጥ ወርውረው ጣሉት

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 29, 2017

ጎፋ ገብርኤል አቅራቢያ የሚገኘውን አደባባይ በብጹዕነታቸው ስም ለመጥራትና ኃውልታቸውንም እዚያ ለማቆም ነበር ታቅዶ የነበረው። ለነገሩማ፤ ኃውልቱ እንዲያውም ከናፍጣ ጭስ ተገላግሎ በዚህች ንጹህና ውብ ቤ/ክርስቲያን ግቢ ውስጥ መተከሉ ሳይሻል አይቀርም።

የአገራችን፣ የወገናችንየአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጠላቶች እነማን እንደሆኑ ያው አሁን በግልጽ እየታየን ነው።

ለእነ “ቦብ ማርሊያ”፣ ለ “ካርል ሃይንስ ቡም” እና ለሌሎቹ ባዕዳውያን የአደባባዮች እና የመንገድ ስሞች ይሰጣሉ፣ ኃውልቶች ይቆማሉ፤ ለወገናችን ለአገራችን መስዋዕት ለከፈሉት ኢትዮጵያውያን ግን ቦታም አይሰጣቸውም።

አወይ ጊዜ አወይ ጊዜ
ጊዜ ነቃሽ ፤ጊዜ ወቃሽ
መንገደኛ ሁሉን ታጋሽ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ

ኢትዮጵያ ብዙ መከራዎችን አሳልፋለች ፤ ብዙዎቹ መከራዎች ከውጭ ወራሪዎች ቢደረሱም ከውስጥ ሀይሎችም ከደረሰው ጥቃት ያልተናነሰ መከራ በቤተክርስትያንና በሀገር ላይ ብዙ መከራ ደርሷል ፤ ይህች ቤተክርስቲያን ከዘመነ አክሱም ጀምሮ አሁን እስካለንበት ዘመን ድረስ ብዙ መንግስታትን አሳልፋለች ፤ ፈሪሀ እግዚአብሔር ያላቸው ነገስታት ለቤተክርስትያን እና ለህዝበ ክርስትያን በርካታ መልካም ተግባሮችን አከናውነው ወደማይቀረው አለም አልፈዋል ፤ ስማቸውም በየዘመኑ በመልካም እየተጠራ ትውልድም የሚዘክራቸው እስከ አሁን ድረስ አሉ ፤ ሌሎች ደግሞ የምትጠፋ መስሏቸው ጦር መዘውባታል ፤ በዘመናቸው ቤተክርስትያኒቷን ለማፍረስ ድንጋይ አንስተውባታል ፤ አሳት ለኩሰውባታል ፤ እርሷ ግን የመጣውን መከራ ተቋቁማ እጃቸውን ያነሱባትን ወደ ኋላ ትታ አሁን እኛ ትውልድ ላይ ደርሳለች፡፡

በሁለተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ላይ የደረሰውን ነገር ማስትታወስ ይኖርብናል፡፡ ብጹዕነታቸው ስለ ቤተክርስቲያን በነበራቸው አቋም ምክንያት በግፈኞች ሕይወታቸውን በግፍ እንዲያልፍ ነበር የተደረገው፡፡

አቡነ ቴዎፍሎስ በእስር ቤት ደረሰባቸውን ፀዋትወ መከራ በዓይን ያዩ በታላቁ ቤተመንግስት አብረዋቸው ታስረው የቆዩ ፤ በአፄ ኃ/ስላሴ ዘመን በስልጣን ላይ የነበሩ ታላላቅ ሰዎች ነበሩ፡፡ ከእነዚህ የአይን ምስክሮች በተገኝው የቃል መረጃ መሰረት ቅዱስነታቸው መጀመሪያ የታሰሩት ለብቻቸው በኢዮቤልዩ ቤተመንግሥት ነበር፡፡ በዚህ ቦታ ጥቂት ቀናት ከቆዩ በኋላ በአንዲት ጠባብ ክፍል ውስጥ አስገብተው እጃቸውንና እግራቸውን ከአልጋ ጋር ጠፍረው አሰሯቸው ፡፡ ቀንም ሆነ ማታ ለሽንት ሲወጡ ካልሆነ በስተቀር ሰንሰለቱ አይፈታላቸውም ነበር በዚህ አይነት ለአራት ቀናት እንዲሰቃዩ ከተደረገ በኋላ ባለስልጣኖች ታስረውበት ወደነበረው ቁጠር አንድ እስር ቤት ወሰዷቸው።

ወቅቱ አብይ ፆም ነበር ከጎፋ ገብርኤል ተይዘው ከመጡበት ቀን ጀምሮ ለአርባ ቀናት ያህል እህል የሚባል ነገር አልቀመሱም ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ጣታቸውን በውሀ ውስጥ በመንከር ከንፈራቸውን ከማርጠብ በስተቀር ጥም የሚቆርጥ ውሀ እንኳን አልጠጡም፡፡ ምግብ እንዲበሉ አንዳንድ ደርግ ባለስልጣናት እና አብረዋቸው ታስረው የነበሩ አዛውንቶች ለምነዋቸው ነበር ነገር ግን ለመብላት ፍቃደኛ አልነበሩም እስከ ፋሲካ ማግስት ድረስ ምንም ሳይቀምሱ ቆይተዋል ፡፡ ለፋሲካ ማግስት ግን እስረኞች መካከል አረጋውያኑ አጥብቀውና አስጨንቀው ስለለመኗቸው እህል ሊበሉ ችለዋል፡፡

በወቅቱ ከነበሩ ሰዎች መረጃ መሰረት ደርግ አቡነ ቴዎፍሎስን በእስር ቤት ስቃይ ካሳዩአቸው ሰዎች መካከል አንድ ሻለቃ የፈፀመባቸው ግፍ ሳይጠቀስ አይታለፍም ፡፡ ይህ ሰው እርሳቸውን የማበሳጨት ተልዕኮ ስለነበረው በንቀት ‹አባ መልአክቱ›› እያለ ይጠራቸው ነበር፡፡ ሞራልም የሚነካ አነጋገርም ይናገራቸው ነበር፡፡ ከወርቅ የተሰራ የእጅ መስቀላቸውን ቀምቶ እስከ መውሰድ ደርሶም ነበር፡፡ ከሚተኙበት ትንሽ ክፍል ውስጥ ሰቅለውት የነበረውን የጌታችን እና የመድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስዕልም በስልጣኑ አውርዶ ወስዶባቸዋል፡፡ የዚህ ሰው ድርጊት ከበስተኋላው የሚገፋፋው ጠላት እንዳለ ያመላክት ነበር፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስ የነበራቸው አነስተኛ ግላዊ ነፃነት እንኳን እስከዚህ ድረስ ተገፍፎ እንደነበር የሻለቃው ድርጊት ያሳያል፡፡

‹‹ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ። ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ፥ ሐሴትም አድርጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና።›› የማቴዎስ ወንጌል 5(11-12)

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ በብዙ ስቃይ እያዩ በእስር ቤት የቆዩት እስከ ሐምሌ 7 1971 .ም ነበር፡፡ በዚህ ቀን እስረኛው እንዲሰበሰብ ታዞ ሲሰበሰብ አንድ ዘበኛ መጣና የሁለት እስረኞችንና የብፁዕነታቸውን ስም ጠርቶ ብርድ ልብሳቸውን እና የሽንት ቤት ወረቀታቸውን ይዘው እንዲወጡ አዘዘ፡፡ በዚህ ወቅት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ወደ ክፍላቸው ገብተው አጭር ፀሎት ካደረጉ በኋላ ጥቁር ቀሚሳቸውን ለብሰው ነጠላ ጫማ አድርገው ቆባቸውን ደፍተውና ከእንጨት የተሰራ የእጅ መስቀላቸውን ይዘው እስረኞችን ካፅናኑ እና መስቀል ካሳለሙ በኋላ ‹‹ እግዚአብሔር ያስፈታችሁ›› በማለት ተሰናብተዋቸው ወጡ፡፡..

‹‹ጊዜው ክረምት ነበር አባታችን አቡነ ቴዎፍሎስ ተይዘው ወደ ራስ አስራት ካሳ ግቢ አዲስ አበባ ከፍተኛ 12 ቀበሌ 22 ተይዘው ሄዱ በወቅቱ የለበሱት ጥቁር የሐር ቀሚስ ጥቁር ነጠላ ጫማ ጥቁር የመነኩሴ ቆብ ነበር፡፡ እንደ ወትሮ በአንገታቸው ያጠለቁት ወይም በእጃቸው የያዙት መስቀል ግን አልነበረም ፡፡ በተጠቀሰው ግቢ ውስጥ ወዳለው ቤት እንዲገቡ ሲደረግ ከውስጥ የተደበቁ ኮማንዶዎች ባዘጋጁት ገመድ በድንገገት አንገታቸውን ሸምቀቅ አድርገው በማነቅ ገደሏቸው፡፡ወዲያውም አስከሬን የሚያነሱ ሌሎች ሰራተኞች አስከሬናቸውን አንስተው ከቤቱ ውጪ ባለው ግንብ ስር በስተ ምዕራብ በኩል በተቆፈረው እና በርካታ ሬሳ በተጣለበት ጉድጓድ ውስጥ ወርውረው ጣሉት›› (በጊዜው ከነበረ ወታደር የዓይን እማኝ የሰጠው ቃል)

ከዚህ በኋላ ቅዱስነታቸው የት እንደደረሱ ምን አይነት ግድያ እንደተፈጸመባቸው ሳይታወቅ ለ13 ዓመት ተዳፍኖ ቆየ፡፡ ነገር ግን ‹‹ የማይገለጥ የተከደነ ፤ የማይታወቅ የተሰወረ ምንም የለም›› ማቴ 1626 እንደተባለው ጊዜ ሲደርስ በምን አኳኋን እንደሞቱና አስከሬናቸው የት ቦታ እንደተጣለ ሊታወቅ በመቻሉ በእንጦጦ አውራጃ ከፍተኛ 12 ቀበሌ 22 ከሚገኝው ከራስ አስራት ካሳ ግቢ አስከሬናቸው ተቆፍሮ ወጥቶ በጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን በክብር አረፈ፡፡

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ከአሜሪካ ቦስተን ዩኒቨርሲቲ በቴዎሎጂ የክብር ዶክትሬት ድግሪ አግኝተዋል ፤ 24 ሺህ ሰው በማሳመንና በማጥመቅ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች አድርገዋል ፤ መንፈሳዊ ኮሌጅ በማቋቋም እንደ አንድ መምህር ከክፍል እየገቡ በማስተማር ምሳሌነታቸውን አሳይተዋል ፤ የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ማስፋፊያ ድርጅት መስርተዋል ፤ ቤተ ክርስቲያን ከዘመኑ ስልጣኔ ጋር ጎን ለጎን መራመድ ትችል ዘንድ ሰባኪያን ቀሳውስትና ዲያቆናት የሚሰለጥኑባቸው የካህናት ማሰልጠኛ ተቋማትን በየሀገረ ስብከቱ እንዲቋቋሙ አድርገዋል ፤ አሜሪካ ከሚገኝው ብሔራዊ የሰብአዊ ጥናቶች መርጃ ድርጅት የገንዘብና የመሳሪያ እርዳታ በመጠየቅ የብራና መጻህፍት የማይክሮ ፊልም ድርጅት አቋቁመዋል(አሁን በመንግስት የተወረሰ) ፤ የዘመን ጥርስ የበላቸው በርካታ በሺህ የሚቆጠሩ የብራና መጻህፍት ጨርሰው ሳይጠፉ ከየገዳማቱና ከየአድባራቱ በማሰባሰብ በማይክሮ ፊልም እንዲቀረጹ አድርገዋል ፤ ቤተክርስቲያን በራሷ ገቢ የምትተዳደርበት የሰበካ ጉባኤ ሃሳብ በማቅረብ አደራጅተው በቃለ አዋዲ እንዲመራ አድርገዋል ፤ የሕጻናት ማሳደጊያ ድርጅት እንዲቋቋም አድርገዋል ፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስ በጠቅላላ ቤተክርስቲያን ያፈራቻቸው አለም አቀፋዊ ብቁ ዲፕሎማት መሆናቸውን ታሪካቸው ይመሰክራል፡፡

______

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , , | Leave a Comment »

በተዋሕዶ አምላክ ጆሮዋ የተከፈታላት እናት እስልምናን በመተዋ ሙስሊሞች ወደ ክርስቲያኖች ዮቱብ ገጽ መጥተው ጋኔናቸውን ያራግፋሉ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 29, 2017

እያንዳንዱ ሙስሊም ውስጥ መንፈሳዊ እባብ አለ!

ክርስቲያኖች ቪዲዮውን አይተው ክርስቲያናዊ ፍቅራቸውንና ደስታቸውን ሲገልጹ፤ መሀመዳውያኑ ግን በድንቁርና እባባዊ መርዛቸውን፣ ጥላቻውን፣ ስድቡንና እርግማኑን ያስታውኩታል

ክርስቲያኖች ይህን ይላሉ፦

  • ዛሬ ላንቺ የደረሠልሽ ቅዱስ ገብርኤል ለኛም ይድረስልን ያሳደገኝ አምላክ አባ እረጅም እድሜ ይስጥልን አሜን
  • የኔ መድሀኒት አለም ላንተ ምን ይሣንሀል ሥራህ ድንቅ ነው ሥምህ የተመሠገነ ይሁን አባ ረጅም እድሜ ይሥጦት
  • ስለ ማይነገረው ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን እልልልልልልልልልልልልልል ለአባታችን እረጅም እድሜና ጤና አብዝቶ ይስጥዎት ለእናታችን የደረሰ አምላክ ለኛም ይርዳን ይፈውሰን አሜን አሜን አሜን
  • የቁልቢው ገብርኤል የራህማው ጌታ አንቺን የሰማሽ ጌታ እኛንም ይስማን የኔ አባት እረጅም እድሜ ይስጦት ያመነ የተጠመቀ ይድናል እኛም በተስፋ እንጠብቃለን
  • ኡፍፍፍ አልቅሼ ልሞት ነዉ እንኳን ደስ አለሽ የኔ እናት ድንቅ ነዉ የእግዚአብሄር ስራ እድሜዎን ያርዝምልዎት አባቴ
  • ተዋህዶ እቺ ነች ዝር ሃይማኖት አትምርጥም አባታችን ፈጣሪ እርጅም እድሜ ይስጥውት
  • ሙስሊሞች እባካችሁ አትሳደብ ሁሉም ስው የሚወደውና የሚፈቅደውን ሀይማኖት የመያዝ መብት አለው እግዚአብሔር ለሁላችንም ምህረትንና ድህነቱን ያድለን ለአባታችን እድሜና ጤና ይስጥልን አሜን
  • መልስ ያጣሁለት ጥያቄ ቢኖር የአላህን ስም ጠርታችሁ ለምን ትገላላችሁ ለምንስ ትሰግዳላችሁ የመለሰልኝ የለም ?????
  • አመነች ዳነች
  • አባታችን እድሜና ጤና ይስጥልን ለበረከት ያብቃን ከስደት መልስ
  • እግዚአብሔር ይመስገን በእውነት እግዚአብሔር ምን የሚሳነው ነገር አለ አህዛቦች ንቁ ለዘሀራ የደረሰ አምላክ ለእናንተም ይድረስላችሁ ተዋህዶ ለዘላለም ትኑር ለእባታችን እረጅም እድሜና ጤናን ያድልልን አሜን
  • ያነበብኩትማ እኔ እንደ ገባኝ ስለ ዳነች ተናደሽ ነው እና ወደ ብርሀን ስለመጣች ለምን ደንቁራ አልቀረችም ነው “”ስለ አመነች ዳነች ፦እንዲህ ናት ኦርቶዶክስ
  • ሙስሊም እማ ናት ሳትሆን ነኝ አትልም ደግሞ ምን ብላ አንቋሸሸች አልተሳደበች እስልምናን ስለ ዳንኩ ኦርቶዶክስ እሆናለሁ አለች እንጅ
  • ክብሩ ይስፋ ለመድሐኒ አለም አባ እድሜና ጤና ይስጥልን አሜን!!
  • እህቴ እንባዬን አስመጣሽው በእውነት ከስጋሽ የበለጠ ነብስሽ ንም አዳንሻት ፈተናውንም እንድትቋቋሚው ያርግሽ ክርስትና ሃይማኖት አልጋ በአልጋ አይደለችምና ምክንያቱም መስቀሉን ተሸክመናልና
  • ምን አለበት ሙስሊም እህቶቸ ዝም ብትሉ አስገድዶ እዩ ያላችሁ ሰው የለ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ እህቶቻችንን እዩዋቸው የሰዉን እምነት አያቆሽሹም
  • እኔ ምለው ሙስሊሞች ለምን ትሳደባላቹ ሰው የፈለገውን ማምለክ ይችላል ጥያቄው ለራሱ ነው ለማንኛውም ፈጣሬ እንኮን ማረሽ እናተን ይቅር ይበላቹ
  • ሙስሊሞች አትንጫጩ ክብር ምስጋና ለመድሀኒአለም እንኳን የክርስቲያን ልጅ ሆንኩ መዳን በእየሱስ ክርስቶስ በድንግል ማሪያም ልጅ ብቻ ነው
  • መናፍቅና ሙስሊም የሚሳደቡት በውስጣቸው ያለው አጋንት ነው ማስተዋል ያድላቸው ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር አባ እድሜወትን ያርዝምልን አሜንንንነ አሜንንን አሜንን
  • እግዚአብሔር ይመስገን እንኳን ተፈወሽ እህት ከጣዎት አምልኮት እንኳን ወጣሽ አላህ የሚባል አምላክ የለም ።
  • የነሱ ሀይማኖት ምን ይላል የአላን ቃል ያልተቀበለ ይገደላል ይላል የኛ ግን ያድናል ድንግን ክብረሽ ይሰፋ
  • ለሙስሊሞች ትምህርት ይሁን

ሙስሊሞች ይህን ያላሉ፦

  • አኡዙቢላሂሚነሸይጧን ረጅም ከኩፍር ጠብቀኝ
  • ዛራ አላህ እውነት አላህ ወደ ሀይማኖት እውነተኛ ወደ ሆነ ኢስሊምና ይመልስሽ ጆሮሽ ተደፍኖ ብቀር ይሻላል
  • ካወቅሽ አሁን ነው የተደፍነብሽ ጆሮሽ ሁሉ ነገርሽ አላህ የማይወልደው የማይወለደው የእየሱስ ጌታ የሆነው አምላካችን ህድያ ይስጥሽ
  • ትክክክል እኔማ ገና ስሰማት አኡዙቢላሂ ሚነሸይጣን ሮዥም እፍፍፍ ገና መስሚያዋ ጆሮተዘጋ አይ
  • ሲጀመር ካፊር ናት ድራማ ልተዉን አሰልጥነዋት ነዉ በሙስሊም ስም
  • ሙስሊም አመስለኝም ቀጣፊ ናት ሙስሊም እዛ አይሄድም አላህ ይድፈንሽ
  • ወሬኛ በያት እይው ኡስታዝ አቡ በከር ነገሩን ጨርሶታበኢስልምና ቆይቶ ክርስቲያን የሚሆኑት ስሙን ብቻ የያዙናቸው ምክንያቱም ቁርአን ምንእንደሚል የማያውቁናቸውብሏል ትክክልነው ይችም አላህ ህድያውን ይስጣት
  • ማንኛውም የየሰውዘር አላህአንድአሎለደምአልተወለደም ማንምያውቃልይሄን እዚህ በመዳምዋይፋይን አፋችሁንአትክፈቱብን አፋችሁን ቆጥቡ ምግብ ብሉበት
  • ይች አላህን የት ታውቂውአለሽ የኛ መድሀኒታችን ቁርአን ነው አንች ሲጀመር ሙስሊም አይደለሽም ውሸታሞች
  • ሠይጣን የተላበሠሽ ድሮም ካፊር ነሽ ሠይጣን ቀዉሥ
  • ቅማላም ድሮም ለሠዉ አይደለም ለቄሡ ሥገጅለት ሁለታቹም ሠይጣኖች አመዳሟች
  • ኤጭ ሲጀመር የሆንሽ ባለዛር ነው እምትመስይው ሀሀሀሀ ምን ትመስላለች ስይጣናም
  • ወይ እህት ጆሮሺ ባይስማ ይሻልሺ ነበራ ከብራሀን ወደ ጨለማ ጋባሺ አላህ ስብብ ባያደራግልሺ አትዲኒም ነበራ አሁንም ወደ ፈጠረሺ አማላክሺ አንድ አላህ ሱብሀኑ ተአላ ተመለሺ አላህ አንድ ነው አይወልዲም አይወለድም
  • አይ ጉድ አላህ ሆይ አሳሳቾችን ያዝልን እድካሁን ጆሮሽ ነበር አሁን ግን ሁለመናሺ ተዘግቶል ሱብሀን አላህ
  • ኢሥላም አሰዳቢ ሙተሽ ብሆን ይሻአልሽ ነበር እምነት ሽን ከመቀየር
  • ሸይጧኖች ምላስሽን ይዝጉት አቦ ምን አይነቷናት በአላህ እንዴት ታሻርካለች እየሱስ የአላግ ባሪያ መሆኑን እያውቀች እነዚህ አባ ተብየውች የሸይጧኖችና የአጋንት አሽከሮችን ናቸው እንፈውሳለን እያሉ እሳት የሚቅጨምሩ ያ አላህ አኽላቃችንን አሳምረህ እንደፈጠርክ ግደለን !!
  • ለዘላለም ይዝጋልሽ ሸይጣን አምላኪ ሲጀመር ሙስሊም አደለሺም ብትሆኒ ንሮ እዚህ እቀጣፊ ቄስ ጋ አትሄጅም ነበር ጅል

______

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

እንኳን ለደብረ ታቦር (ቡሔ) በዓል በሰላም አደረሰን

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on August 19, 2017

______

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , | Leave a Comment »

እህታችን ወይንሸት ተዋሕዶ ስለ ክርስቲያናዊ ስርአተ አለባበስ ሀያት እስላሟንና ሳያት ደምሴን ታስተምራለች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on July 21, 2017

የ ቅ/ ክርስቶስ ሰምራ እና የ ቅ/አርሴማ ልጆች በጭውውት መልክ ያቀረቡት ይህ ቪዲዮ/አውዲዮ ታላቅ መልዕክት ያዘለ ነው።

የክርስቶስ ልጆች እንደ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አለባበሳቸውን ሲያሳምሩ፣ የመሀመድ ልጆች ደግሞ የቅድስት ማርያምን ገጽታ ለማጉደፍ እንደ እርሷ የለበሱ በማስመሰል ቅጥፈትን፣ ማመንዘረን፣ ጥላቻን እና ግድያን ይፈጽማሉ።

ዲያብሎስ መኮረጅ ይወዳልና፤ የኢትዮጵያውያንን ክርስቲያናዊ አለባበስ ያላየ ፡ የሙስሊሞችን አለባበስ ሲያይ በቀጥታ የእመቤታችን ምስል ነው የሚታየው። በውጩው ዓለም በኢትዮጵያኛ ስርዓት ለብሰው መንገድ ላይ የሚወጡትን እህቶቻችን፤ “እንዴ፤ እስላም ነሺ እንዴ?” ተብለው የሚጠየቁበት፤ “ጾም ገብቷል: ይህን ይህን አንበላም” ስንል፡ “እንዴ ረመዳን ደረሰ እንዴ?” በስግደት ጸሎት ስናደርስም፡ እንደዚሁ፡ “እንደ ሙስሊሞች መሬት ላይ ትደፋላችሁን?!“ እየተባልን የምንተቸውና የምንጠየቀው ከዚህ የተነሳ ነው። ያው፡ ዲያብሎስ ዓለምን ለማታለለና ለማሳሳት ምን ያህል እንደተሳካለት!

እነርሱ ባገኙት አጋጣሚ ሁላ እራሳቸውን በማስተዋወቅ ላይ ናቸው፤ በዚህም ዲያብሎሳዊ ግዴታቸውን እየተወጡ ነው፤ እንዴት እንደሚኮራባቸው!

ጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስና ቅዱሳናት፣ እንዲሁም የእኛ ቀሳውስት ጢማቸውን ማሳደጋቸው የተለመደ ነው፤ ታዲያ ሙስሊሞችም ጢሞቻቸውን እያሳደጉ የአምላካቸውን ስም እየጠሩ ክቡሩን የሆነውን የሰውን ልጅ ያርዳሉ። የቅዱሳኑን መልክ፣ ገጽታና ማንንነት ለማጉደፍ።

አያችሁ የኮራጁና የአታላዩ ዲያብሎስ ተንኮል ምን እንደሚመስል!?

[የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፲ ፡ ፲]

ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ

[፪ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ም. ፲፩ ቊ ፲፪ ፣ ፲፭]

ነገር ግን በዚያ በሚመኩበት እንደ እኛ ሆነው ሊገኙ፥ ምክንያትን ከሚፈልጉቱ ምክንያትን እቆርጥ ዘንድ አሁን የማደርገውን ከዚህ ወዲህ ደግሞ አደርጋለሁ።

እንደ እነዚህ ያሉ ሰዎች የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ፥ ውሸተኞች ሐዋርያትና ተንኮለኞች ሠራተኞች ናቸውና።

ይህም ድንቅ አይደለም፤ ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና።

እንግዲህ አገልጋዮቹ ደግሞ የጽድቅን አገልጋዮች እንዲመስሉ ራሳቸውን ቢለውጡ ታላቅ ነገር አይደለም፤ ፍጻሜአቸውም እንደ ሥራቸው ይሆናል

ሳያት ሀያትና ወይንሸትን ሰምታ ሁለተኛ የአረብ ልብስ እንደማትለብስና ቁንጅናዋን ከዚህ በኋላ ለዲያብሎስ እንደማትሰጥ ተስፋ አደርጋለሁ፦

______

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , | Leave a Comment »

ከኢትዮጵያ ጠባቂ እረኞች አንዱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 1, 2017

እንኳን አደረሰን!!!

የቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕትነት በመጽሐፈ ስንክሳር

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አምላክ አመ ዕሥራ ወሠሉሱ ለሚያዝያ በዛቲ ዕለተ ኮነ ፍጻሜ ስምዑ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕት ዐቢይ ወክቡር ዘተሰምየ ፀሐየ ወኮከበ ጽባሕ፡፡

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሚያዝያ ሃያ ሦስት በዚች ቀን ፀሐይና የአጥቢያ ኮከብ የተባለ ታላቅና ክቡር የሆነ የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ የምስክርነት ፍጻሜ ሆነ፡፡

የዚህም ቅዱስ አባቱ መስፍን ነው፡፡ ስሙም አንስጣስዮስ ይባላል፡፡ ከቀጰዶቅያ አገር ነው፡፡ የእናቱም ስም ቴዎብስታ ይባላል ከፍልስጥዔም አገር ናት ታናሽ ሆኖ ሳለ አባቱ ዐረፈ፡፡

ሃያ ዓመትም በሆነው ጊዜ የአባቱን ሹመት ሊቀበል ወደ ንጉሥ ዱድያኖስ ዘንድ ሔደ፡፡ ንጉሡም ጣዖትን እንዲአመልኩ ሰዎችን ሁሉ ሲያስገድዳቸው አገኘው፡፡

ይህንንም አይቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ እጅግ አዘነ በእርሱ ዘንድ ያለውን ገንዘቡን ሁሉ ለድኆች፣ ለምስኪኖች ሰጠ ባሮቹንም ነፃ አወጣቸው፡፡

ከዚህ በኋላ በንጉሥ ፊት ቁሞ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ፡፡ ንጉሡም አባበለው ብዙ ቃል ኪዳንም ገባለት እርሱ ግን አልተቀበለውም፡፡

ለመስማት እንኳ የሚያስጨንቅ ሥቃይን አሠቃየው ጌታችን ግን ያጸናዋል ቍስሉንም ያድነዋል ሦስት ጊዜም እንደሚሞት እርሱም እንደሚአስነሣው በአራተኛውም የምስክርን አክሊልን እንደሚቀበል ነገረው፡፡ ቃል ኪዳንም ሰጠው ስሙ በዓለሙ ሁሉ የተገለጠ ይሆን ዘንድ በተጋድሎና መከራ በመቀበልም ጽኑዕ በሆነ ሥቃይም ሰባት ዓመት እንደሚኖር መላእክትም እንደሚአገለግሉት ነገረው፡፡

ንጉሡም ቅዱስ ጊዮርጊስ ባለመታዘዙና ባለመመለሱ እጅግ አዘነ፡፡ ስለዚህም አትናስዮስ የሚባል ታላቅ ሥራየኛ አመጣ፡፡ እርሱም መርዝን ቀምሞ በጽዋ መልቶ አስማት ደግሞ እንዲጠጣ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰጠው፡፡ ወዲያውኑ የሚሞት መስሎት ነበር፡፡ ቅዱሱም ያንን ጽዋ ጠጣው ምንም ጉዳት አልደረሰበትም፡፡

ያ መሠርይም በክብር ባለቤት በጌታ በኢየሱስ አምኖ በሰማዕትነት ሞተ፡፡ ከእርሱም ጋር ሌሎች ብዙዎች ሰዎች በሰማዕትነት ሙተው የሕይወት አክሊል ተቀበሉ ቁጥራቸውም ሠላሳ ሺህ ሰባት መቶ ነፍስ ነው፡፡

ቅዱስ ጊዮርጊስም በዱድያኖስና በሰባ ነገሥታት ፊት በቆመ ጊዜ በዚያም የተቀመጡባቸው የዕንጨት ወንበሮች ነበሩ፡፡ ቅዱሱንም እሊህን የተቀመጥንባቸውን ወንበሮች እንዲበቅሉ እንዲአብቡና እንዲአፈሩ ታደርጋቸው ዘንድ ከአንተ እንሻለን አሉት፡፡ በዚያን ጊዜ ጸለየ እንዳሉትም አደረጋቸው ይህንንም ድንቅ ሥራ አይተው ቍጥር የሌላቸው ብዙ አሕዛብ በጌታችን አመኑ፡፡

ከዚህም በኋላ ቅዱሱን ወስደው በጐድጓዳ ብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት፡፡ አቃጥለው አሳርረውም ሥጋውንና ዐጥንቱን ፈጭተው አመድ አድርገው ከረጅም ተራራ ላይ በተኑት፡፡ ጌታችንም ነፍሱን ወደ ሥጋው መልሷት ደግሞ አስነሣው፡፡ ወደ ነገሥታቱም ተመልሶ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ስም ሰበከ፡፡ ቍጥር የሌላቸው አሕዛብ አይተው አደነቁ በጌታችንም አምነው በሰማዕትነት ሞቱ፡፡

ነገሥታቱም ደግመው ሙታኖችን ብታሥነሣ አምላክህ ዕውነተኛ አምላክ እንደሆነ እናውቃለን፡፡ በእርሱም እናምናለን አሉት፡፡ ቅዱሱም ጸለየ ከጒድጓድም ውስጥ ወንዶችና ሴቶችን ጐልማሶችንም አስነሣላቸው እነዚያም በክብር ባለቤት በጌታችን ስም አስተማሩ የገሀነምንም ወሬ ተናገሩ ጥምቀትንም ተቀብለው ተመልሰው ዐረፉ፡፡

ከሀድያን ነገሥታት ግን ሙታንን ያስነሣህ አይደለም የረቀቁ ሰይጣናትን አሳየህ እንጂ ብለው ተከራከሩ፡፡ ከዚያም ከጭንቀታቸው ብዛት የተነሣ ከአንዲት ድኃ ሴት ዘንድ አስጠበቁት እርሷም እንጀራ ልትለምንለት ወጣች የእግዚአብሔርም መልአክ በላዩ ከበጎ ነገር ሁሉ የተመላ ማዕድን አቀረበለት፡፡ የዚያች መበለትም የቤቷ ምሰሶ ቅርንጫፍን አበቀለ ታላቅ ዛፍም ሆነ፡፡

ያቺም መበለት በተመለሰች ጊዜ የቤቷ ምሰሶ ቅርንጫፍ አብቅሎ ታላቅ ዛፍ እንደሆነ ስለ ማዕዱም ይህን ታላቅ ምልክት አይታ የክርስቲያኖች አምላክ ሰው ተመስሎ ወደ እኔ መጣ አለች፡፡ ቅዱስም እኔ አምላክ አይደለሁም፡፡ የአምላክ ባሪያ ነኝ እንጂ አላት፡፡ እርሷም እንዲህ ብላ ለመነችው የአምላክ አገልጋይ ከሆንክ ቸርነትህ እንድትደርሰኝ እለምንሃለሁ፡፡ ዕውር ደንቆሮ ዲዳ ጐባጣ የሆነ ልጅ አለኝና ታድንልኝ ዘንድ እለምንሃለሁ፡፡ ስለ ጌታችን እምነትም አስተማራትና በመስቀል ምልክት አማተበው ያን ጊዜም አየ፡፡ ቅዱሱም በሌላ ጊዜ እንዲሰማ እንዲናገርና እንዲሔድ እንዲአገለግለኝም እኔ እሻለሁ አላት፡፡

በዚያን ጊዜ ንጉሡ በአገሩ ሜዳ ውስጥ ሲዘዋወር ያቺን ዛፍ አይቶ አደነቀ ስለ እርሷም ጠየቀ ቅዱስ ጊዮርጊስ በእርሷ ዘንድ የተቀመጠባት የዚያች መበለት የቤቷ ምሰሶ እንደሆነ ነገሩት፡፡ ንጉሡም ተቆጣ ቅዱሱንም ከዚያ ወስዶ አስገረፈው በመንኰራኵርም አበራዩት ሙቶም ከከተማ ውጭ ጣሉት ጌታም ከሞት አስነሣው ወደ ነገሥታቱም ተመለከተ ንጉሡም አይቶ ደነገጠ ስለ ሕይወቱም አደነቀ፡፡

ከዚህም በኋላ ይሸነግለው ዘንድ ጀመረ በመንግሥቱ ላይም ሁለተኛ ያደርገው ዘንድ ቃል ገባለት ቅዱስ ጊዮርጊስም እየዘበተበት ነገ በጥዋት ለአማልክቶችህ መሥዋዕትን አቀርባለሁ አንተም ሕዝቡ እንዲሰበሰቡ እዘዝ እኔ ስሠዋ እንዲአዩ አለው፡፡ ንጉሡም ዕውነት የሚሠዋ መስሎት ደስ አለው ወደ ቤተ መንግሥቱም እልፍኝ አስገብቶ አሳደረው፡፡

ለጸሎትም ተነሣ የዳዊትንም መዝሙር አነበበ የዱድያኖስ ሚስቱ እለስክንድርያ ንግሥት ሰምታ ቃሉ ደስ አሰኛት የሚያነበውንም ይተረጒምላት ዘንድ ለመናቸው፡፡ እርሱም እግዚአብሔር ዓለምን ከፈጠረበት ሰው እስከሆነበት ጊዜ የሆነውን ሁሉ ሊያስረዳትና ሊያስገነዝባት ጀመረ፡፡ ትምህርቱም በልቡዋ ተቀርጾ በክብር ባለቤት በጌታችን አመነች፡፡

በማግሥቱም ቅዱስ ጊዮርጊስ ለአማልክት ሲሠዋ ለማየት ሰው ሁሉ እንዲሰበሰብ ዐዋጅ ነጋሪ ዞረ የቤቷን ምሰሶ ያበቀለላት ያቺ መበለት ሰምታ ዕውነት መስሏት እጅግ እያዘነች ልጅዋን ተሸክማ እያለቀሰችም ወጣች፡፡

ቅዱስ ጊዮርጊስም በአያት ጊዜ ፈገግ አለ ልጅሽን በምድር ላይ አኑሪው አላት፡፡ ከዚያም ልጅዋን ጠርቶ ወደ አጵሎን ሒድ ወደእኔም ይመጣ ዘንድ በክብር ባለቤት በጌታዬ ኢየሱስ ስም እዘዘው አለው፡፡ ያን ጊዜ ያ ልጅ ድኖ ቅዱስ ጊዮርጊስ እንዳዘዘው ወደ ጣዖቱ ቦታ ሒዶ አዘዘው፡፡ በጣዖቱ ያደረ ያ ርኵስ መንፈስም ከማደሪያው ወጥቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ አለት መጥቶ እኔ ሰውን ሁሉ የማስት እንጂ አምላክ አይደለሁም ብሎ በሕዝቡ ሁሉ ፊት አመነ፡፡ ቅዱሱም ትውጠው ዘንድ ምድርን አዘዛትና ወዲያውኑ ዋጠችው ጣዖታቱንም ከአገልጋዮቻቸው ጋራ አጠፋቸው ንጉሡም ከወገኖቹ ጋር ዐፈረ፡፡

ብስጭትና ቁጣንም እንደተመላ ወደ ንግሥት ሚስቱ ዘንድ ገባ፡፡ እርሷም አምላካቸው ጽኑዕና ኃያል ነውና ክርስቲያኖችን አትጣላቸው አላልኩህምን አለችው፡፡ ይህንንም ከእርስዋ ሰምቶ በእርሷ ላይ እጅግ ተቆጣ ወደ ክብር ባለቤት ክርስቶስ እምነት የከበረ ጊዮርጊስ እንደአስገባት አወቀ፡፡

ከዚህም በኋላ ከከተማ ውጭ እንዲጐትቷትና በመጋዝም እንዲሰነጥቋት አዘዘ፡፡ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለች፡፡

በዚያም ጊዜ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሥራ ነገሥታቱ ሁሉም ደነገጡ ኀፍረት ደግሞ እንዳይጨምርባቸው ከእርሱም እንዲአርፍ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ እንዲጽፍ ንጉሥ ዱድያኖስን መከሩት፡፡

ያን ጊዜም የክቡር ጊዮርጊስን ራስ በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ፡፡ ድል አድራጊ ጊዮርጊስም እጅግ ደስ አለው፡፡ እሳት ከሰማይ አውርዶ ሰባውን ነገሥት ያቃጥላቸው ዘንድ መከራውም ከክርስቲያን ወገን ጸጥ ይል ዘንድ ጌታችንን ለመነው፡፡ ወዲያው እሳት ወርዶ ከሠራዊታቸው ጋር ሰባውን ነገሥታት አቃጠላቸው፡፡

ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተገልጾ ብዙ ቃል ኪዳን ሰጠው፡፡ በምድር መታሰቢያህን ለሚያደርግ ሁሉ እኔ ኃጢአቱን ሁሉ እደመስሳለሁ በመከራም ውስጥ ሁኖ በባሕርም ሆነ በየብስ ወይም በደዌ በስምህ የሚለምነኝን እኔ ፈጥኜ ከመከራው አድነዋለሁ፡፡ ይህንንም ጌታችን ተናግሮ በክብር ወደ ሰማይ ወጣ፡፡

ከዚህ በኋላ ራሱን ዘንበል አድርጎ በሰይፍ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያት አክሊላትን ተቀበለ፡፡ ከአገልጋዮቹም የቀሩት ሥጋውን ወስደው በልብስ ጠቀለሉት ወደሀገሩ ልዳም ወሰዱት፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው በውስጥዋ አኖሩት ከእርሱም ቍጥር የሌላቸው ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ፡፡

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የቅዱስ ጊዮርጊስም በረከቱ ረድኤቱ ሁላችን የክርስቲያን ወገኖችን ከሥጋና ከነፍስ መከራ ይጠብቀን ለዘላለሙ አሜን፡፡

ምንጭ

እሙሀይ ብርሐን ዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም

በዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም በቤተክርስቲያን ቅፅር ግቢ ውስጥ የሚኖሩት እሙሀይ ብርሐን እናታችን የተሰጣቸው ፀጋ በጣም ለሰሚው ጆሮ በጣም ሊከብድ ይቻላል እናታች በቤተክርስታን ቅፅር ጊቢ መኖር ከጀመሩ ከ30 ዘመናት በላይ ሆኗቸዋል በነዚህ ዘመናት ባዶ ሜዳ ላይ ተቀምጠው ☞ ዝናብ ሲዘንብ እሳቸው የተቀመጡበት ቦታ ደረቅ ሆኖ እሳቸውንም ሆነ የተቀመጡባትን አካባቢ ዝናብ አያገኘውም እሙሀይ በዚህ ሲኖሩ የሚመገቡት ቱልት የተባለውን ቅጠል ሲሆን እናታችን ብዙ ተማዕራትን በተለያየ ግዜ ሲያደርጉ በአካባበው ምዕመናን ታይተዋል ከዚህ አልፎ በዋልድባ ገዳም ሚኖሩ አባቶች ከሰማይ በቀስተደመና አምሳል ከሰማይ ብርሐን ሲወርድላቸው አይተው መጥተው እሙሀይን በረከት በረከትዎ ይድረስብን እናታችን ብለው እጅ ነስተዋል የእናታችን በረከት በጣም አስገራሚ እና አስደናቂ ነው እሰኪ ሁላችንም የእሙሀይ ብርሐን በረከት በየአለንበት ይድረሰን እሙሀይንም በቦታው ተገኝተን የበረከቷ ተካፍይ ያድርገን።

ምንጭ

__

__

__

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , | 1 Comment »

ክርስቶስ በደመራ ታየ – እኛን “አትፍሩ” – ጠላቶቻችንን “ተጠንቀቁ”! ይላል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 28, 2016

Jesus Seen Inside The Ethiopian Bonfire

Christ redeemed us through His death on the Cross. The Cross has thus become the sign of victory for Christians. It is the symbol of our freedom from evil and our rebirth for a new life in Jesus Christ.

Even after the resurrection of Jesus Christ, the Cross kept on making numerous miracles among believers. Indeed, The True Cross on which our Lord was crucified is in Ethiopia.

Every year, The Ethiopian Orthodox Church organises a ceremony to light a huge bonfire at Meskel Square in central Addis Ababa.

jesus1

jesus7

jesus9

The above video (+snapshots) segment is taken from this year’s ceremony of setting the DEMERA bonfire in Addis Abeba.

While the Demera is set on fire you can clearly see Jesus Christ (no statue or figure there, just normal eucalyptus wood) standing in the middle of the fire giving an inner feeling of brightness and warmth for all those who are around it, and sending a message to the rest of us.

ከዚህ በኋላ ንጉሥ ናቡከደነፆር በአድናቆት ከተቀመጠበት ዘሎ በመነሣት አማካሪዎቹን “አስረን በእሳት ውስጥ የጣልናቸው ሰዎች ሦስት አልነበሩምን?” ሲል ጠየቀ።

እነርሱም፣ “ንጉሥ ሆይ፤ እውነት ነው” አሉ።

እርሱም፣ “እነሆ፤ ያልታሰሩና ያልተጎዱ አራት ሰዎች በእሳቱ ውስጥ ሲመላለሱ አያለሁ፤ አራተኛውም የአማልክትን ልጅ ይመስላል” አላቸው።” [ዳንኤል 324-25]

jesusdemera

Then King Nebuchadnezzar leaped to his feet in amazement and asked his advisers, “Weren’t there three men that we tied up and threw into the fire?”

They replied, “Certainly, Your Majesty.”

He said, “Look! I see four men walking around in the fire, unbound and unharmed, and the fourth looks like a son of the gods.” [Daniel 3: 24 – 25]

__

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: