Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • May 2023
    M T W T F S S
    1234567
    891011121314
    15161718192021
    22232425262728
    293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘የቤተክርስቲያን ፈተና’

እኅተ ማርያም | አቤቱ ሕዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ፤ ጠብቃቸው፥ ለዘለዓለሙ ከፍ ከፍ አድርጋቸው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 27, 2019

__________________

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

በተዋሕዶ ትግሬ ኢትዮጵያውያን ላይ የተቀሰቀሰው ጥላቻ ሰውን እንደ እብድ ውሻ ያደርገዋል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 17, 2019

መለስ ዜናዊ ፊት አበበ ገላው የተባለ ሰው እንደጮኸ ዜናውን በጊዜው እንደሰማሁ ቪዲዮውን ማየት እንኳን አላስፈለገኝም – ያየሁት ገና ባለፈው ወር ላይ ነው፣ ኢሳት ቴሌቪዥንንም አልፎ አልፎ ማየት የጀመርኩት እንዲሁ ገና ባለፈው ወር ላይ ነው – ለዚህ ምክኒያቱ አበበ ገላውና ኢሳት የሲ.አይ. ኤ ምልምሎች፣ በባለ ኃብቱ ጆርጅ ሶሮስ ዓይነት አገራትአፍራሾች የሚደገፉ መሆናቸውን የሚነግረኝ ነገር ስለነበረ ነው። አሁን ሁሉንም አንድ ባንድ እያየን ነው።

እብዱ አበበ ገላው፡ ልክ እንድ አጋሮቹ እንደነ ዶ/ር አብዮት የተዋሕዶ ኢትዮጵያ ማዕከል በሆነችው በትግራይ ላይ ከፍተኛ ጥላቻ እንዳለው ይህ ቪዲዮ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ አጋጣሚዎች የተሳተፈባቸው ሌሎች ቪዲዮዎች ያሳዩናል። እብዱ ገላው መለስ ዜናዊ ፊት ሲለፈልፍ ብዙ ጥፋቶች ያጠፋውን ፖለቲከኛ መለስን ሳይሆን እና አባቶቹ ከተዋሕዶ የሆኑትን ትግራይ ኢትዮጵያዊውን መለስን ለማዋረድ ነው።

ጠቅላይ ሚንስትር መለስን እና አቡነ ጳውሎስን ያስገደላቸው ፕሬዚደንት ኦባማ፣ ሼክ አላሙዲንና የግብጹ ፕሬዚደንት መሀመድ ሙርሲ ቡድን ነው በማለት በተደጋጋሚ አውስቼ ነበር። አሁን የቡድኑ ተዋናዮች ቀስበቅስ እየተሰባሰቡ ማንነታቸውን እንዲያሳዩን እየተደረገ ነው። ኢንጂነር ስመኘውን የገደለው ቡድን እነ መለስ ዜናዊንም አስገድሏል።

ፀረኢትዮጵያ፣ ፀረተዋሕዶ የሆነው የእነ ኦቦ አብዮት አህመድ + ኦቦ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ + ኦቦ ሰመኦን በረከት + ኦቦ ለማ መገርሳ + ኦቦ አበበ ገላው + ኦቦ ሲሳይ አጌና ቡድን

እንዴት? ተከታዩን በሚቀጥለው አጋጣሚ አቀርበዋለሁ

[የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፲፥፳፮]

እንግዲህ አትፍሩአቸው፤ የማይገለጥ የተከደነ፥ የማይታወቅም የተሰወረ ምንም የለምና።”

__________________

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የምዕራብ ሉሲፈራውያን “ኢትዮጵያን”፣ ሰዶማውያን “ባንዲራዋን”፣ ሙስሊሞች ደግሞ “ክቡር መስቀሏን” ሊሠርቁ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 4, 2019

አዎ! እየተካሄደ ያለው ይህ ነው፤ ከታሪክ መማር ካልቻልክ ስተቶችን ከመደጋገም አትቆጠብምና ሞኞቹ ኢትዮጵያውያን በውጭ ጠላቶቻቸው በመታለል የራሳቸው ጠላቶች በመሆን ላይ ናቸው።

ቀደም ሲል፡ ሱዳኖች የተባሉት ኢትዮጵያውያን “የሱዳን አረቦች ነን ኢትዮጵያውያን አይደለንም” አሉ፤ ከዚያ የጂቡቲ ኢትዮጵያውያን “ጂቡቲያውያን ነን ኢትዮጵያውያን አይደለንም” አሉ፣ ቀጥለውም ሰሜን ኢትዮጵያውያን “እኛ ኤርትራውያን ነን ኢትዮጵያውያን አይደለንም” አሉ፣ ብዙም አልቆየም ደቡብ ኢትዮጵያውያን፤ “የለም እኛ ኢትዮጵያውያን አይደለንም ኦሮሞዎች ነን” አሉ፣ ዛሬ ደግሞ “ትግሬ እና አማራ” የተባሉት “አይ እኛ በቅድሚያ ትግሬዎች እና አማራዎች ነን” በማለት ላይ ናቸው።

እንግዲህ እነዚህ ኢትዮጵያውያን የጠላትን ተንኮል ባለመረዳትና ከጠላት ጋር፡ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መልክ በማበር “ኢትዮጵያን” ከማንንነታቸው ላይ ለመፋቅ በፈቃዳቸው ተግተው በመሥራት ላይ ናቸው። እራስን ለማጥፋት!

ሰሞኑን “አማራ” በተባሉት ኢትዮጵያውያን ላይ እየተካሄደ ያለው ጥቃት ሆን ተብሎ፣ ሰው ሠራሽ በሆነ መንገድ በመንደርተኛ ብሔር ግንባታ ላይ በተናጠል ትኩረት እንዲያደርጉ ለመገፋፋት ነው፤ ልክ ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ ሲዳማ ወዘተ እንደተባሉት፡ ከኢትዮጵያዊነታቸው በፊት መንደርተኛነታቸውን ያስቀድማሉ ማለት ነው። “ዕንቁላል ወይስ ዶሮ?” የሚለውን የተለመደ ዕንቆቅልህ ምን አውቅልህ ጨዋታ ይመስል”።

የዚህ ሁሉ ዲያብሎሳዊ አጀንዳ አላማም የእኔ የሚሉትን አዲስ ማንነትን እንዲይዙ እና “ኢትዮጵያን” እንዲረሱ፣ አማርኛ ቋንቋን ከብሔራዊ ቋንቋነት ለማስወገድ፣ የኢትዮጵያን አረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀይ ሰንደቅ ዓላማ ለማስተው፤ በመጨረሻም፡ ዋናው ግባቸው ነው፤ የተዋሕዶ ክርስትናን ለማጥፋት ነው።

በቀጥተኛነታቸውና በግልጽነታቸው የማደንቃቸው ኢንጂነር ይልቃል እንኳን ባንድ ወቅት “አማራ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ማለቱ አስጠቅቶታል” ብለው ነበር።

አይ! ይህማ አይሆንም፤ “ኢትዮጵያዊነታችንንማ በፍጹም አንተውም” ልትሉ ትችላላችሁ፤ ነገር ግን አይምሰላችሁ፤ በዚህ ከቀጠለ፤ በዛሬው ውጥቅንቅጥ ሥርዓት እያደጉ ያሉት ሕፃናት በሚቀጥሉት ሃያ አመታት ውስጥ ሁሉንም ነገር እርግፍ አድርገው በመተው ዲያብሎስ የፈጠረላቸውን አዲስ ማንነት ይቀበላሉ። ለዚህም የእነ ዶ/ር አብዮት አህመድን ፀረኢትዮጵያ አጀንዳ አራማጆች እና እየተሠራ ያለውን ፀረኢትዮጵያ ሤራ ማየት የተሳናቸው እውሮች ከተጠያቂነት አያመልጡም። ኢትዮጵያን በመተው ባንዲራዋን እና መስቀሏን ያልተሸከም ሁሉ ጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ እንደሚወድቅ፡ ሱዳን፣ ጂቡቲ እና ኤርትራ ምስክሮች ናቸው።

__________________

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

እኅተ ማርያም | በመስቀል አደባባይ ለ666ቱ አውሬ የደም መስዋዕት ያደረገው መሪያችሁ ትክክለኛ ስሙ አብዮት አህመድ ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 17, 2019

መስቀል አደባባይን ግራኙ መንግስቱ ኃይለ ማርያም የአብዮት ብሎ ሰየመው፤ የደም መስዋዕት አደረገበት፤ ግራኝ አብዮት አህመድ ተረከበው፤ የደም መስዋዕት አደረገ፤ ለግራኙ ዋቄዮ አላህ ሰጠው፤ የደም መስዋዕት ተቀበለበት፤ በደሙ ሰከረ። ግን፤ ሁሉም መስዋዕት በመጥረጊያ ወይም “በቆሻሻ ጠረጋ”ሳይሆን በክቡር መሰቀሉ በአንድ ዕለት ተጠራረገ።

አዎ! ግራኝ አብዮት አህመድ ሥልጣን ላይ በወጣ በወሩ የድጋፍ ሰልፍ ጥሪ ሲያደርግ፤ አንዳንዶቻችን “ገና ምንም ሳይሠራ ለምኑ ድጋፍ ነው ሕዝብ እንዲወጣለት የፈለገው?“ በማለት ጠይቀን ነበር። ለካስ ደም ለማፍሰሰና ለዋቄዮ አላህ መስዋዕት ማድረግ አቅዶ ነበር። ከዚህ በኋላ ነበር እነ መሀንዲስ ስመኘው፣ በጅጅጋ መነኮሳትና ቀሳውስት፣ በቡራዮ፣ ጌዲኦ፣ ለገጣፎ፣ አጣዬ ወዘተ ነዋሪዎች ላይ ጭፍጨፋ የተካሄደባቸው። ይህ እንዳቀደው የዓለም አቀፍ ማሕበረሰን ትኩረት አልሳበለትም፤ ስለዚህ ከመላው ዓለም የመጡ መንገደኞችን የተሸከመው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላንን በይበልጥ አትኩሮትን ያገኝለት ዘንድ ለመስዋዕት ሥነ ስርዓቱ መረጠው – የዋቄዮ አላህ ዙፋን በሚገኝበት በሆራ ቢሸፍቱ ሸለቆ ውስጥ መቶ አምሳ ሰባት ሰዎች የደም መስዋዕት እንዲከፍሉ አደረገ። የሚገርም ነው፤ ባንዲራችን ላይ ያረፈውን ባለአምስት ማዕዘን ኮከብ ሙጭጭ አድርጎ መያዙ ለደም መስዋዕቱ ይረዳው ዘንድ ነው፡ ማለት ነው።

የሚገርም ነው፤ ዶ/ር አብዮት አህመድ ልጆች እንደሌሉት እኔም ጥርጣሬ ነበረኝ፤ እህታችን የተነገራት ነገር ትክክል ሳይሆን አይቀርም፤ ልጆቹ የተባሉት የእርሱ አይመስሉኝም። ልክ የባራክ ሁሴን ኦባማ “ዱርዬ” ሴት ልጆች የእርሱ እንዳልሆኑ። ዶ/ር አብዮት፡ ልጆች ከሌላቸው ከ ሦስቱ “M”ኦች፤ ከፈረንሳዩ ፕሬዚደንት አማኑኤል ማክሮን(በሰላሳ ዓመት የምትበልጠውን ሴት አግብቶ ይኖራል)፥ ከጀርመኗ ካንዝለር አንጌላ ሜርከል እና ከብሪታኒያዋ ጠቅላይ ሚንስትር ተሪዛ ሜይ ጋር በ 666ቱ አውሬ መንፈስ ስም አብሮ ተደምሯል፤ ስለዚህ ልክ እንደ እነሱ ሥልጣን ላይ እስቆየ ድረስ የደም መስዋዕት ማድረጉን እና ዓብያተ ክርስቲያናትን ማፈራረሱን ይቀጥልበታል። ለዚህም ተጠያቂው እርሱ ብቻ ሳይሆን፤ ይህን ሁሉ ጉድ እያየ ለእርሱ ድጋፉን በመስጠት ላይ ያለው ግብዝ ሰው ሁሉ ነው። ዋ! ብለናል።

__________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

እኅተ ማርያም | ዶ/ር አህመድ ቀን ሰው ሌሊት አውሬ ነው፤ መሀንዲስ ስመኘውን አስገድሎታል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 15, 2019

“ደሙ አብይ አህመድን፣ ሰመኦን በረከትን እና አዜብ መስፍንን ይጣራል”

“ልክ እንደ ግራኝ አህመድ ዘመን ተዋሕዶን ለማጥፋት ሩጫ ላይ ናቸው”

ግራኝ አህመድ ሲያደርገውም የነበረው ቤተክርስቲያንን ማቃጠል ነው፤ የዛሬዎቹ የእርሱ ልጆችም፣ በእርሱ እምነት ነን የሚሉትም ዓብያተክርስቲያናትንና ደኖችን በማቃጠል የኢትዮጵያን ታሪክ ሙልጭ አድርገው ለማጥፋት በመታገል ላይ ናቸው። ጠቅላይ ሚንስትሩም ዓላማ ስላለው ምንም ማድረግ አይፈልግም፤ ሰውዬው ቀን ሰው ሌሊት አውሬ ነው፤ ይህን አስመልክቶ ሕዝቡ ዓይኑ ሊገለጥለት አልቻለም፤ እግዚአብሔር ግን መልስ ይሰጣቸዋል።”

ካልደፈረሰ አይጠራም፤ አገራችን መጽዳት አለበት።”

ታዛቢዎች፣ ተንታኞች ወይም የሜዲያ ባለሙያዎች ተብለው ብዙ ተከታዮችን ካተረፉት ሺህ ወንዶች፡ አንዷ እህታችን በጀግነነቷና በግልጽነቷ በሺህ እጥፍ ትበልጣቸዋለች፤ የምትናገረው ሁሉ ትክክል ነው፤ መታወቅም ያለበት ሃቅ ነው፤ የእኛ እውርነትና ድንቁርና ነው እንጅ ይህ የአደባባይ ምስጢር ነው፤ በመሀንዲሱ ወንድማችን እና በሕዳሴው ግድብ ላይ ዶ/ር አህመድ ከግብጽ እና አረቦች ጋር በመመሳጠር የሠራውን በታሪካችን ተወዳዳሪ የማይገኝለትን ደባ በማጋለጥ በፍጥነት ለፍርድ ማቅረብ ነበረብን/ አሁንም ማቅረብ አለብን።

በእኔ በኩልም፡ በተለይ፡ ግራኙ አብይ አህመድ ኢንጂነር ስመኘውን ብቻ ሳይሆን ሌሎች ብዙ ያልተነገረላቸውን ኢትዮጵያውያንን፤ ክንፈ ገብርኤልን ጨምሮ፤ አስገድሏል፣ በጅጅጋ እና ሰሜን ሸዋ ዓብያተ ክርስቲያናትንና መነኮሳቱን አቃጥሏል፣ እናቶችን ከለገጣፎ አፈናቅሏል፣ በጌዲኦን ሕዝብ ላይ የተካሄደውን “የሱዳን ዳርፉርመሰል” ጭፈጨፋ፣ የባንኮች ዘረፋ ወዘተ። በአጭር ጊዜ ውስጥ ዓይኖቻችን እያዩ የተሠራው ወንጀል ተቆጥሮ አያልቅም።

ሰውዬው ስልጣን እንደያዘ ፈጥኖ “የቀን ጅቦች” ማለት የጀመረው ወይም ሰዶማውያንን የሚመለከትና የኢንሳ ጥናታዊ ፊልሞች እንዲሠሩ ያዘዘው፡ ብሎም የማሕበራዊ ሜዲያዎች ላይ ሳንሱር ለማድረግ የሚንቀሳቀሰው፡ እራሱ የራሱን ማንነት እና የሚያደርጋቸውን ጽንፈኛ ድርጊቶች ለመሸፈን ሲል ነው። ይህ ዓይነት ባሕርይ በብዛት በመሀመዳውያንና ዘረኛ ሰዎች ዘንድ ነው በግልጽ የሚታየው፤ በእንግሊዝኛው Projection„ አንጸባራቂነት / ማሳየት/ ይባላል፤ ማለትም እራሳቸው ቆሻሾች መሆናቸውን ስለሚያውቁ ከመቀደማቸው በፊት እራሳቸውን ንጹህ አድርገው ሌላውን ቆሻሻ ያደርጋሉ። እነርሱ መናፍቅ ሆነው ሌላውን ኩፋር/ መናፍቅ ይላሉ፣ እነርሱ በምንዝርነት፥ በዝሙት፥ በሌብነት፥ በውሸትና በስድብ ዓለማቸው ውስጥ ተዘፍቀው በእነዚህ ሃጢአቶች ሌላውን ቀድመው ይኮንናሉ፣ እነርሱ በዳዮች እና ገዳዮች ሆነው እኛ ተበድለናል እያሉ ሌላውን ይወቅሳሉ። የዋቄዮ አላህም ልጆች የዚህ ዓይነት ባሕርይ ነው ያላቸው።

____________________

Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የእኅተማርያም እህቶችና ወንድሞች | “ዶ/ር አብይ ጥምቀትን አስመልክቶ የተናገረው ቃል ፀረ-ተዋሕዶ ነው”

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on January 27, 2019

እኅቶቻችን እና ወንድሞቻችን ከተናገሯቸው ነገሮች መካከል፦

  • + /ር አብይ የተናገሩት እንኳን አንድ አገር እመራለሁ ከሚል ሰው፤ ከአንድ ምዕመን እንኳን የማይጠበቅ ነው፤ ጠቅላይ ሚንስትሩ ለሕዝቡ ይቅርታ መጠየቅ አለባቸው

  • + ጠቅላይ ሚንስትሩ ይህን ማለታቸው፤ ሃይማኖታችን ጠፍቶ ሁሉ ነገር እንደ ፌስቲቫል እንዲሆን ነው

  • + እራሱን የመቻል ብቃት ያለው ቅዱስ ታቦት ለምንድን ነው በታጠቁ ወታደሮች ታጅቦ እንዲሄድ የሚደረገው? ምን ዓይነት ቅሌት ነው?!

  • + አብይ አህመድ ኦርቶዶክስን ወዴት እየወሰደው ነው? የሚለውን ጥያቄ ሁሉም ሰው ሊጠይቀው የሚገባው ነገር ነው። ወዴት ወዴት ፎቀቅ እያልን ነው? ሃይማኖቱን ሁሉ ጨምቀው አንድ ሃይማኖት ለመፍጠር እየታገሉ ነው፤ አባቶች ስለዚህ ጉዳይ መናገር ይጠበቅባቸዋል።

  • + ትናንትና ስልጣን ላይ የወጣ ሰው እንዴት ይህን ያህል ተዋሕዶን ደፍሮ ሊናገር ቻለ?!

ቃለ ሕይወት ያሰማለን፤ እኅቶች እና ወንድሞች፤ ጀግኖች! ምን አለ እያናዳንዱ የተዋሕዶ ልጅ እንደ እናንተ መሆን ቢችል! ቸኩለው “አብይ አብይ” ሲሉ የነበሩት የአንዳንድ አባቶች ዝምታ ያደነቁራል። እየተካሄደ ስላለው ነገር እንዴት ዝም ማለት ይቻላል?

ዔዶማውያኑ ምዕራባውያን እና እስማኤላውያኑ ሕዝባችንን ከውስጥ እስከ ውጭ አብጠርጥረው አጥንተውታል፤ ቀስ በቀስ በማለማመድ ሕዝባችንን ፀረክርስቶሱን እንዲቀበል ለማድረግ ማዘጋጀት ከጀመሩ ቆይተዋል። ምን እንደሚፈልግ፣ ምን መስማት እንዳለበት፣ ማንን መቀበል እንደሚችል በደንብ አውቀውታል። ስለዚህ ሕዝባችንን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር ይችሉ ዘንድ ሰዎች እራሳቸው ፈቃደኛ ሆነው መርዛቸውን እንዲቀበሉላቸውና የፈጠሩት አጋጣሚም እንዳያመልጣቸው አሁን በጣም በመጣደፍ ላይ ናቸው።

ልክ ከዚህ በፊት ሻለቃ መንግስቱ ኃይለማርያም እና አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ እንዳደረጉት እነ ዶ/ር አብይ አህመድ አሊም (ስሙ ላይ በደንብ እናተኩር፤ ቍልፍ ሚና ይጫወታልና) በሲ.አይ.ኤ እና ኤፍ..አይ እንዲሁም በእንግሊዝ የስለላ ድርጅቶች አማካኝነት ስልጠናን አድረገዋል። እነዚህ ድርጅቶች የ666ቱ ዋና ተዋንያን ናቸው። መሪዎቻችን የእነርሱን ትዕዛዝ መቀበል አለባቸው፤ የማይቀበሉ ከሆነ፡ ልክ እንደ አቶ መለስ ዜናዊ ይገደለሉ።

እነ ዶ/ር አብይ አኅመድንና አቶ ለማ ለገሰን ሰልጣን ላይ ለማውጣት የወሰኑት ገና ከ፳፯ ዓመታት በፊት ነበር፤ ኦነግ የኢሕአዴግ መንግስትን ለቅቆ እንዲወጣ የተደረገው በሉሲፈራውያኑ ፕላን ነው፤ ምክኒያቱም፡ ፩ኛ. በቋንቋ የተከፋፉሉ ክልሎች ተመሥርተዋል፤ “እስከ መገንጠል” የሚለው ሕገ መንግስት በመጽደቁም ግቡን መትቷል፣ ፪ኛ. የመስተዳደሩን ኃላፊነት በተለይ ለትግርኛ ተናጋሪዎች በማስረከብ የተዋሕዶ የጀርባ አጥንት በሆኑት ትግሬዎች ላይ መጥፎ ስም በመስጠትና በመኮነን ሕዝቡ ጥላቻ እንዲኖረው ለማድረግ ይችላሉና ነው። በ፳፭ ዓመት ውስጥ የኢትዮጵያን ታሪክ እና ሁኔታ መረዳት የማይችል አንድ ትውልድ ተፈጥሯልና። ይህን አሁን በተከታታይ በግልጽ የምናየው ነው።

ኢትዮጵያውያን መስማት የሚፈልጉትንና ማየት የሚመኙትን ድራማ እንዲነግሯቸውና እንዲያሳዩአቸው እነ ዶር አብይ አህመድን መረጡ፤ ግን እነርሱን በደንብ ከማስተዋወቃቸው በፊት፡ ሉሲፈራውያኑ ያዘጋጇቸው ምሁራኑ እና ሜዲያዎቹ “ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ” አሉ (መንግስቱ ኃይለማርያምም “ያለምንም ደም፤ ኢትዮጵያ ትቅደም! እያለ ነበር ሥልጣን ላይ የወጣው) ፣ “ባንዲራችን ላይ ኮከቡ መስፈሩ ተገቢ ነው አይደለም ” እያሉ የመረጧቸውን ሰዎች በማወያየት ኢትዮጵያውያንን አጠኑ፤ ሕዝቡ የት ድረስ አብሯቸው ሊጓዝ እንደሚችል ተገነዘቡ።

በኢትዮጵያዊነት ፍቅር የተጠሙ አገር ወዳዶቹ ኢትዮጵያውያን በየዋህነት “ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ” የሚለውን መፈክር አብረው ማሰማት፣ ኮከቡ ያላረፈበትንም ባንዲራ በየአደባባዩ ይዘው በመውጣት መፈንደቅ ጀመሩ። አሁን ይህ አገር ወዳድ የሆነው ኢትዮጵያዊ፡ ልክ፡ ቀደም ሲል “ነፍጠኛ” በማለት አማርኛ ተናጋሪውን ሲኮንኑት እንደነበረው፤ አሁን ደግሞ “ወያኔ” በማለት ትግርኛ ተናጋሪውን መኮነን እንዲበቃ ተደረገ፤ አንጎሉ ታጠበ። “ነፍጠኛ” እና “ወያኔ” የሚሉት የመወንጀያ ቃላት መግቢያ ሆኖ ለ “ተዋሕዶ ክርስቲያኖች” የተሰጠ ኮድ ናቸው።

የእኅተማርያም ማሕበር አባላት ግሩም በሆነ መልክ በትክክል ጠቁመውታል፤ ኮከቡ ያላረፈበትን ባንዲራችንን በየቤተክርስቲያኑ መሰቀል ጀምረው ነበር፤ አሁን ግን ሁሉም ኮከቡን እንደገና እንዲለጥፉ ታዘዋል።

/ር አብይ ሥልጣኑን በተረከበ ማግስት፤ “እውነት ሕዝባችንን ለማገልገል የመጣ ሰው ከሆነ እነዚህን ሦስት ነገሮች በፍጥነት መፈጸም ይኖርበታል” ብዬ ነበር፦

  • ፩ኛ. በቋንቋ የተከፋፈልውን የክልል ሥርዓት እንዲያፈርስ

  • ፪ኛ. ኮከቡን ከባንዲራችን ላይ በአዋጅ እንዲየነሳ

  • ፫ኛ. ከአረብ አገሮች ጋር ያለንን ጥብቅ ግኑኝነት እንዲያላላ

አመት ሆነው፤ ግን ሦስቱንም ጉዳዮች እስካሁን ለማስተካከል ሙከራ አላደረገም፤ እንዲያውም ሁኔታዎችን ወደ ባሰ መንግድ እየመራቸው ነው፤ በዚህም ሉሲፈራውያኑ ምዕራባውያን፣ አረቦችና የተባበሩት መንግስታት ፈላጭ ቆራጮች ታይቶ በማይታወቅ መልክ እያጨበጨቡለት ነው። ይህም በጣም ስላደፋፈረው፡ መጀመሪያ በትግርኛ ተናጋሪዎች ላይ ሤራ መጠንሰስ ጀመረ፤ አሁን ደግሞ ወደ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ዞረ። አቤት ድፍረት!

የእኅተ ማርያም እኅቶችና ወንድሞች ያሉት ትክክል ነው፤ ሁኔታዎችን በደንብ የሚቃኝ እያንዳንዱ የተዋሕዶ ልጅ ሊወስደው የሚገባው ግንዛቤ ነው። አዎ! /ር አብይ እና አጋሮቹ የ666ቱን ማህተብ ካልተቀበሉ በቀር ሥልጣን ላይ አይወጡም፤ አይቆዩምም። ሥልጣን ላይ ከወጡ ደግሞ የሉሲፈራውያኑን ትዕዛዝ መቀበል ግድ ነው፤ አሻፈረን ካሉ የመለስ ዜናዊ ዓይነት ዕጣ ስለሚደርሳቸው ይፈራሉ፤ ስለዚህ ፀረኢትዮጵያ፣ ፀረተዋሕዶ የሆነውን አጀንዳ የማራመድ ግዴታ አለባቸው ማለት ነው። እንደነርሱ ከሆነ የኢትዮጵያ ምሰሶ የሆነችው ተዋሕዶ መጥፋት አለባት፤ እርሷ ከጠፋች የአንድ ዓለም ሃይማኖት እና መንግስት መመስረት ይቀላቸዋል።

ግን አይሳካላቸውም፤ ወዮላቸው! ሁሉን የሚያይ እግዚአብሔር አምላክ የቀዳውን ቪዲዮ አንድ ባንድ ተንትኖ በኋላ ያሳያቸዋል። እነርሱን አያድርገን!

አዎ የሚያምን ከማያምን ጋር ምንም ሕብረት ሊኖረው አይገባም፦

[፪ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕራፍ ፮፥ ፲፬፡ ፲፭]

ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ፤ ጽድቅ ከዓመፅ ጋር ምን ተካፋይነት አለውና? ብርሃንም ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው? ክርስቶስስ ከቤልሆር ጋር ምን መስማማት አለው? ወይስ የሚያምን ከማያምን ጋር ምን ክፍል አለው?

[የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፲፥ ፴፬፡፴፮]

በምድር ላይ ሰላምን ለማምጣት የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ሰይፍን እንጂ ሰላምን ለማምጣት አልመጣሁም። ሰውን ከአባቱ፥ ሴት ልጅንም ከእናትዋ፥ ምራትንም ከአማትዋ እለያይ ዘንድ መጥቻለሁና፤ ለሰውም ቤተ ሰዎቹ ጠላቶች ይሆኑበታል።

__________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የእኅተ ማርያም ማኅበር | እምቦጩ የኢትዮጵያን ቅዱሳት ቦታዎች ለማጥፋት የተፈጠረ አረም ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 31, 2018

ያውም ገዳማቱ መግቢያ መግቢያ ቦታ ላይ ነው እንዲበቅል የተደረገው

ወንድማችን ትክክል ነው፤ ከእምቦጩ አረም መብቀል ጋር በተያያዝ ሤራው የተጠነሰሰው በየኢትዮጵያ ጠላቶች ነው። ይህ አያጠራጥረን! እንዲያውም ይህ በአይናችን ለማየት የበቃነው አንዱ ክስተት ብቻ ነው። መታየትና መታወቅ ያለባቸው ገና ብዙ ብዙ ነገሮች አሉ። ጎብኚዎች ብቻ ሳይሆኑ የአረሙ ተካዮች፡ በዚያ በኩል የሚይልፉ አውሮፕላኖች በእነ ዋልድባ፣ አክሱም፣ ላሊበላ፣ ጊሸን፣ ዝቋላ፣ ቍልቢ በኩል እያለፉ መርዛቸውን በውሃና ደኑ ላይ ይረጫሉ። በአባቶቻችን ጊዜ ተደጋግሞ ይከሰት የነበረው የወሎና ትግራይ ድርቅ መንስዔ በዚህ መልክ ነበር የተካሄደው።

ወንድማችን እንዳወሳው፡ ከመቶ አመት በፊት አንስቶ ወደ ውጭ አገር እየተላክንና ስለ ጠላቶቻችንን ተንኮል ለመማርና ለማወቅ እድሉ ያለን “ኢትዮጵያውያን” ይህን ሤራ ለማጋለጥ ፈቃደኞች አለመሆናችን ሁልጊዜ የሚከነክነኝና የሚያሳዝነኝ ጉዳይ ነው። በኢትዮጵያውያን የዘር ውርስ ወይም ጀነቲክስ ላይ ምርምር የሚያካሂድ አንድ የስታንፎርድ ወይም ኬምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ ምሩቅ “ኢትዮጵያዊ” ለምሳሌ ሴቶቻችንን መኸን ለማድረግ ሕጻናቶቻችን ለማኮላሸት የተጠነሰሰ ሤራ እንዳለ በደንብ ነው የሚያውቀው። ታዲያ እንዴት ነው፡ በድብቅ እንኳን ለሕዝባችን ሹክ ከማለት የተቆጠቡት? በጣም ያሳዝናል፡ ለንስሃ እንኳን ሳንበቃ የዶክተርና የማስተርስ ማዕረጉን ይዘን ወደ አፈር ውስጥ መግባታችን እኮ ነው።

ድንቅ ሥራ እየሠራችሁ ነው እኅቶቻችን እና ወንድሞቻችን፤ እግዚአብሔር ይስጥልን!!!

 ______

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

እኅት ፅጌ ማርያም | “የኢትዮጵያ ታላቁ ኃብቷ ተዋሕዶ ክርስትናዋ”

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 18, 2018

ከልጅነቱ ጀምሮ መርፌ እየተወጋ ያደገው ትውልድ ገና አልገባውም፤ የተስፋቢስነት ወጥመድ ውስጥ እንዲገባ፣ ማንነቱን እንዳያውቅ፣ ምድራዊ መሲህን እንዲጠብቅ ተደርጓል፣ እንደ ዔሳው ብኩርናውን በቀይ ምስር ወጥ/ በሃምበርገር ለነጮች ለመሸጥ ይፈቅዳል።

እስኪ እንታዘብ፤ እኅታችን ፅጌ ማርያም ኢትዮጵያ ስላላት ታላቅ ኃብት ቆንጆ በሆነ መልክ ሃቁን ስትናገር ስቱዲዮ ውስጥ ያሉት “ኢትዮጵያውያን” አድናቆታቸውን በሞቅታና በድንገተኛ መልክ በጭብጨባ እንደመግልጥ፤ ሰይፉ “አጨብጭቡላት እንጂ” ብሎ እስኪነዳቸው ይጠብቃሉ።

______

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: