Posts Tagged ‘ዘመነ ዮሐንስ’
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 13, 2020
የመጥምቁ የቅዱስ ዮሐንስን በዓል በማስመልከት የቀረበ ግሩም ትምሕርት
ሰይጣን አዳም አባታችንንና ሔዋን እናታችንን በገነት በነበሩበት ጊዜ በሥጋ ከይሲ (በእባብ አካል) ተሰውሮ ተሸሽጎ ክፉ ምክርን መክሮ አምላክ አታድርጉ ያላቸውን እንዲያደርጉ በማድረግ እግዚአብሔርን እንዲበድሉ ኃጢአት እንዲሠሩ ትዕዛዙን እንዲያፈርሱ አድርጓቸው እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምርናል።
ቅዱስ ዮሐንስ ሲያገለግል ዓላማው ሰዎችን ከእግዚአብሔር ጋር ማገናኘት እንጂ ሰዎችን በእርሱ ዙሪያ መሰብሰብና መክበር አልነበረም፡፡ ቅዱስ ማቴዎስ በወንጌሉ እንደሚነግረን «ከኢየሩሳሌም፣ ከመላው ይሁዳ፣ በዮርዳኖስ ዙሪያ ባለው ነገር ሁሉ ሰዎች ወደ እርሱ ይጎርፉ ነበር፡፡» /ማቴ.፫÷፭-፡፮/ እርሱ ግን «እኔ በውኃ ለንስሐ አጠምቃችኋለሁ፤ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ያጠምቃችኋል፡፡» እያለ ሰዎቹ እርሱን እንዲከተሉ ሳይሆን የጌታችንን መምጣት ተስፋ እንዲያደርጉ የሚያደርግ ትምህርት ያስተምራቸው ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት የቅዱስ ዮሐንስ ደቀመዛሙርት በኋላ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብተዋል፡፡
የመጀመሪያዎቹ ጌታችንን የተከተሉት ደቀመዛሙርት የዮሐንስ ደቀመዛሙርት ነበሩ፡፡ ስለዚህ በዚህ ዘመን መታጀብ /በሕዝብ መከበብ/ ለሚያስደስተን የእግዚአብሔርን ሳይሆን የእኛን ተከታዮች እንደ ፈሪሳውያን ለምንፈልግ አገልጋዮች ትልቅ ተግሳጽ ነው፡፡
እግዚአብሔር ከመልካም ምክር እንዲያገናኘን ክፉውን እና መልካሙን ምክር እንድለይ ማስተዋሉን እንዲሰጠን ቅዱስ ፍቃዱ ይሁን!
_____________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith, Life | Tagged: መጥምቁ ዮሐንስ, ቅዱስ ዮሐንስ, ነብዩ ኤልያስ, አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ, ኢየሱስ ክርስቶስ, ዘመነ ዮሐንስ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት, ጥምቀት, ፪ሺ፲፩, Christmas, Ethiopian Orthodox Tewahedo Faith, John The Baptist | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 14, 2019
ቅዱስ ዮሐንስ ሲያገለግል ዓላማው ሰዎችን ከእግዚአብሔር ጋር ማገናኘት እንጂ ሰዎችን በእርሱ ዙሪያ መሰብሰብና መክበር አልነበረም፡፡ ቅዱስ ማቴዎስ በወንጌሉ እንደሚነግረን «ከኢየሩሳሌም፣ ከመላው ይሁዳ፣ በዮርዳኖስ ዙሪያ ባለው ነገር ሁሉ ሰዎች ወደ እርሱ ይጎርፉ ነበር፡፡» /ማቴ.3÷5-6/ እርሱ ግን «እኔ በውኃ ለንስሐ አጠምቃችኋለሁ፤ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ያጠምቃችኋል፡፡» እያለ ሰዎቹ እርሱን እንዲከተሉ ሳይሆን የጌታችንን መምጣት ተስፋ እንዲያደርጉ የሚያደርግ ትምህርት ያስተምራቸው ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት የቅዱስ ዮሐንስ ደቀመዛሙርት በኋላ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብተዋል፡፡
የመጀመሪያዎቹ ጌታችንን የተከተሉት ደቀመዛሙርት የዮሐንስ ደቀመዛሙርት ነበሩ፡፡ ስለዚህ በዚህ ዘመን መታጀብ /በሕዝብ መከበብ/ ለሚያስደስተን የእግዚአብሔርን ሳይሆን የእኛን ተከታዮች እንደ ፈሪሳውያን ለምንፈልግ አገልጋዮች ትልቅ ተግሳጽ ነው፡፡
እግዚአብሔር ከመልካም ምክር እንዲያገናኘን ክፉውን እና መልካሙን ምክር እንድለይ ማስተዋሉን እንዲሰጠን ቅዱስ ፍቃዱ ይሁን!
_____________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: ሄሮድስ, መጥምቁ ዮሐንስ, ቅዱስ ዮሐንስ, ነብዩ ኤልያስ, አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ, ኢየሱስ ክርስቶስ, ዘመነ ዮሐንስ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት, ጥምቀት, ፪ሺ፲፩, Christmas, Ethiopian Orthodox Tewahedo Faith, John The Baptist | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 13, 2019
እያንዳንዳችን ከጥምቀታችን ቀጥሎ በሚፈጸምልን ምሥጢረ ሜሮን አማካኝነት መንፈስ ቅዱስ ያድርብናል፡፡ ይህንን ተጠቅመን ሥራ ለመሥራት እኛም እንደ መጥምቁ የራሳችን በረሃ ያስፈልገናል፤ በትህርምትና ራስን በመግዛት መኖር አለብን፡፡
ይህንን ማድረግ የሚገባቸውና የሚችሉት በገዳም ያሉ ሰዎች ብቻ አይደሉም፡፡ በዓለም የምንኖር ሰዎችም ብቻችንን የምንሆንበትና በጸሎት፣ በተመስጦ፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን በማንበብ፣ ራሳችንን በመመርመር የምናሳልፈው ጊዜ በመመደብ መኖሪያ ቤቶቻችንን ገዳማት ማድረግ እንችላለን፡፡ ሁኔታዎችን እያመቻቸን ወደተለያዩ ገዳማት እየሄድን ጊዜ ማሳለፍም ጠቃሚ ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ምግባችንን፣ መጠጣችንን እና ልብሳችንን በልክ እያደረግን መጥምቁን ባለ ብዙ ፍሬ በሆነበት ጎዳናው ልንከተለው ያገባናል፡፡
ሲሰርቁ፣ ሲያመነዝሩ፣ በዝሙት ሲወድቁ፣ ሲሰክሩ፣ ሲዘሉ፣ ሲያብዱና ሲያጨበጭቡ ከመሞት እግዚአብሔር ሁላችንንም ይጠብቀን!
የቅዱስ ዮሐንስ ጸሎቱና በረከቱ ይደርብን! አማላጅነቱ ይደረግልን!
______________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: ሄሮድስ, መጥምቁ ዮሐንስ, ቅዱስ ዮሐንስ, ነብዩ ኤልያስ, አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ, ኢየሱስ ክርስቶስ, ዘመነ ዮሐንስ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት, ጥምቀት, ፪ሺ፲፩, Ethiopian Orthodox Tewahedo Faith, John The Baptist | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 12, 2019
የቅዱስ ዮሐንስ ክብር እና መዓርጋት
ቅዱስ ዮሐንስ ክብሩ በጣም ከፍ ያለ ነው፡፡ የክብሩ ምስክሮችም ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እና መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ናቸው፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ ሲል የመጥምቁን ክብር ተናግሯል፡፡
«ምን ልታዩ ወደ ምድረ በዳ ወጥታችኋል? ከነፋስ የተነሣ የሚወዛወዛውን ሸንበቆ ነው? ወይስ ምን ልታዩ መጥታችኋል ቀጭን ልብስ የለበሰ ሰውን ነውን? እነሆ ቀጭን ልብስ የሚለብሱማ በነገሥታት ቤት አሉ? ምን ልታዩ መጥታችኋል ነቢይ ነውን? አዎን እርሱ ከነቢያት እጅግ ይበልጣል፤ እነሆ በፊትህ መንገድህን የሚጠርግ መልእክተኛዬን እልካለሁ ተብሎ ስለ እርሱ የተጻፈለት ይህ ነውና፡፡ እውነት እውነት እላችኋለሁ ሴቶች ከወለዷቸው ወገን ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም» /ማቴ.11÷7-11/
መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም እንዲህ ሲል ክብሩን ተናግሮለታል፡– «እርሱ በእግዚአብሔር ፊት ታላቅ ይሆናል» /ሉቃ.1÷15/
የቅዱስ ዮሐንስ ጸሎቱና በረከቱ ይደርብን! አማላጅነቱ ይደረግልን!
____________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: ሄሮድስ, መጥምቁ ዮሐንስ, ቅዱስ ዮሐንስ, ነብዩ ኤልያስ, አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ, ኢየሱስ ክርስቶስ, ዘመነ ዮሐንስ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት, ጥምቀት, ፪ሺ፲፩, Christmas, Ethiopian Orthodox Tewahedo Faith, John The Baptist | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 7, 2019
ኢትዮጵያ በእግዚአብሔር የተመሰረተችና በቅዱሳን ቃል ኪዳን የተጠበቀች፤ ከሁል በላይ ደግሞ የእመቤታችን አስራት አገር ናትና ሃገራችንን አይተዋትም
ዘመን አልፎ ዘመን ሲተካ
ሳር ቅጠሉ ሁሉ ሲፈካ
ዝናም በሙቀት ሊተካ
ብርሃን ጨለማን ሲተካ
እንቁጣጣሽ፡ እንቁጣጣሽ!!
ደህና ጊዜን ይዘሽ ደግሞ ደግሞ ያምጣሽ።
እርቅ ነው ፍቅር ነው ለኛ አዲስ ዘመን፡
የሚታረቀውን እናቀናለን፡ አረሙን እንነቅላለን።
አዲሱ ፪ሺ፲ ዓመት
የበረከት፣ የፍቅርና የሰላም ይሁንልን
እንቁጣጣሽ
እንቁጣጣሽ በያመቱ ያምጣሽ!
እንኳን ከዘመነ ሉቃስ
ወደ ዘመነ ዮሐንስ በሰላምና
በጤና አሸጋገረን!
መልካም አዲስ አመት!
ብሩክ አዲስ ፪ሺ፲፪ አመት – Happy Ethiopian New 2012 Year!
መጭውን ፳፻፲ ወ ፪ ዓ.ም አመት፡ የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና እና የደስታ ዘመን ያድርግልን !!!
_____________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: አዲስ ዓመት, እንቁጣጣሽ, ዘመነ ዮሐንስ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት, Ethiopian New Year, Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on August 28, 2019
የሉሲፈር ጉዳይ ነውና የአውሮፓውያኑን ቀን አቆጣጠር ልጠቀም። በ 2016 (እ.ኤ.አ.) በ ናይትድ ስቴትስ ውስጥ በሚገኘው ክሊቨላንድ የተፈጥሮ ሣይንስ ቤተ–መዘክር፥ በሰው ዘር አመጣጥ ጥናት ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ዮሐንስ ኃይለ ሥላሴ “በሚያስደንቅ ሁኔታ የተሟላ” ቅሪተ–አካላት፡ ሉሲ/ ድንቅ ነሽ ተገችታበት በነበረበት የአፋር ቦታ አካባቢ አገኘን ይላሉ። እድሜውም ሶስት ሚሊየን ስምንት መቶ ሽህ ዓመት ነው ተብሏል። መጠሪያው ላኪ/ Lucky ሆኗል። Lucy – Lucky, „k“ ሲነሳ Lucy ይሆናል።
በቅድመ–ታሪክ ጥናት የመስክና የቤተ–መኩራ መስክ ሰፊ ምርም ያደረጉት ዶ/ር ዮሐንስ ኃይለሥላሴ እስካሁን በተገኙ መረጃዎች እና ጥናቶች መሰረት ኢትዮጵያ የዘመናዊው ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ የሰው ዘር መገኛ መሆኗን ይገልጣሉ።
ኢትዮጵያዊው “ሉሲ” (እድሜዋ 3.2 ሚሊየን ዓመት) እ.አ.አ በኅዳር 24 / 1974 ዓ.ም ነበር የተገኘችው። እንግዲህ ሉሲ በተገኘችበት ዓመት ሦስት ወራት ቀደም ሲል እ.አ.አ በመስከረም 12 / 1974 ዓ.ም፤ ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ ከኤርትራ በመጣው ጴንጤ ጄነራል አማን አንዶም ተተኩ። ያውም በዕለተ ቅዱስ ዮሐንስ። ዶ/ር ሀይሌ ላሬቦ በቀደም ዕለት ” ከአፄ ኃይለ ሥላሴ መስተዳደር በኋላ ኢትዮጵያ ጠንካራ አገር እንዳትሆን መንግስቷ ከጦርነት እንዳይላቀቅ ማድረግ አለብን” ማለታቸው ትክክል ነው። ነጠብጣቦቹን እናገናኝ፦ ቅዱስ ዮሐንስ + አፄ ኃይለ ሥላሴ + ዶ/ር ዮሐንስ ኃይለ ሥላሴ
በነገራችን ላይ፡ “ሉሲ” የሚለው ስያሜ የተሰጠው፡ አግኝቷል የተባለው አሜሪካዊ ተመራማሪ፡ ዶናልድ ዮሃንሰን Donald Johanson (ስሙ የ ዮሐንስ ልጅ ማለት ነው) ቅሪተ–አካላቱን ባገኘበት ወቅት “ሉሲ ከአልማዝ ጋር በሰማይ” / “Lucy in the Sky with Diamonds” በመባል የሚታወቀውን የእንግሊዝ የሙዚቃ ቡድን ቢትልስ/ Beatles ዘፈን እያዳመጥኩት ስለነበር ነው ብሏል። የሙዚቃ ቡድኑ ደግሞ ይህን ዘፈን ያወጣው ለሉሲፈር ነው። ሰይጣን አምላኪዎች ይህን የቢትልስ ዝማሬ በጣም ይወዱታል፤ በሰይጣናዊ ሥነ ሥርዓቶቻቸው ላይ ዛሬም ሲዘምሩት ይሰማሉ። በድብቅ “ሉሲፈር ከአጋንንት ጋር በሰማይ / Lucifer In The Sky With Demons” መሆኑ ነው።
[ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ ፲፬፥ ፲፪፡፲፭]
“አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ፥ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! አሕዛብንም ያዋረድህ አንተ ሆይ፥ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቈረጥህ! አንተን በልብህ። ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ፥ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፥ በሰሜንም ዳርቻ በመሰብሰቢያ ተራራ ላይ እቀመጣለሁ፤ ከዳመናዎች ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፥ በልዑልም እመሰላለሁ አልህ። ነገር ግን ወደ ሲኦል ወደ ጕድጓዱም ጥልቅ ትወርዳለህ።“
[ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕራፍ ፳፰፥፲፫ ]
“በእግዚአብሔር ገነት በዔድን ነበርህ፤ የከበረ ዕንቍስ ሁሉ፥ ሰርድዮን፥ ቶጳዝዮን፥ አልማዝ፥ ቢረሌ፥ መረግድ፥ ኢያስጲድ፥ ሰንፔር፥ በሉር፥ የሚያብረቀርቅ ዕንቍ፥ ወርቅ፥ ልብስህ ነበረ፤ የከበሮህና የእንቢልታህ ሥራ በአንተ ዘንድ ነበረ፤ በተፈጠርህበት ቀን ተዘጋጅተው ነበር።“
ከአምስት አመት በፊት “ሉሲ / Lucy“ የተባለና ከኢትዮጵያዋ ሉሲ/ Lucy ጋር የተያያዘ ፊልም ተሠርቶ ነበር። የፊልሙ ዋና ተዋናይት ታዋቂዋ ስካርሌት ዮህናሰን / Scarlett Johansson ( የ ዮሐንስ ልጅ) ናት። ከዶናልድ ዮህንሰን ጋር ስጋዊ ዝምድና የላትም። ዮሐንስ + የዮሐንስ ልጅ + ዶ/ር ዮሐንስ ኃይለ ሥላሴ።
መጭው ዘመነ ዮሐንስ ነው፤ ብዙ ተዓምራትን የምናይበት ድንቅ ዘመን ነው የሚሆነው።
_____________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Curiosity, Ethiopia, Ethnicity, Genetics & Anthropology, Faith | Tagged: ሉሲ, ሉሲፈር, ሰማይ, ቅሪተ-አካላት, አሜሪካ, ዘመነ ዮሐንስ, ድንቅነሽ, ዶ/ር ዮሐንስ ኃይለ ሥላሴ, Cleveland Museum, Hominin Cranium, Lucifer, Lucy, Yohannes, Yohannes Haile-Selassie | Leave a Comment »