Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • May 2023
    M T W T F S S
    1234567
    891011121314
    15161718192021
    22232425262728
    293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ካናሪያስ’

A Meteor Has Crashed in The Canary Islands, Big Explosion Heard | ተዓምረ ኅዳር ጽዮን

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 1, 2022

👉 ገብርኤል 👉 ማርያም 😇 ኡራኤል 👉 ጊዮርጊስ 👉 ተክለ ሐይማኖት 👉 ዮሴፍ 👉 መድኃኔ ዓለም

🔥 በካናሪ ደሴቶች ተወርዋሪ ኮከብ ወድቋል፣ ትልቅ ፍንዳታም ተሰምቷል

🛑 የእሳት ኳሱ በስፔይን ደሴቶች በ ላስ ፓልማስ እና ቴነሪፌ እንደ ተወርዋሪ ኮከብ ሰማዩን ሲሻገር የታየ ሲሆን ከባቢ አየርን ሲያቋርጥ ያስከተለው የድምጽ ሞገድ በተለይ በግራን ካናሪያ ከፍተኛ ድምጽ አሰምቷል። አንድ ቀን በእሳተ ገሞራም ሆነ በተወርዋሪ ኮከብ አማካኝነት ከእነዚህ ደሴቶች ሊነሳ የሚችለው የባሕር ሞገድ “የበስተ ምስራቁን የአሜሪካ ጠረፍን ሙሉ በሙሉ የማውደም ብቃት አለው” ተብሏል።

🛑 The fireball was seen crossing the sky like a shooting star from Las Palmas and Tenerife, and the sonic wave that it caused when crossing the atmosphere was heard as a loud noise, especially in Gran Canaria

👉 Source / ምንጭ

💭 ቪዲዮው መጨረሻ ላይ የቀረበውን ሰውዬ ምስል እናስታውስ! ሰሞኑን ካጋጠመኝ አስደናቂ ክስተት ጋር የሚያያዝ ነገር አለ። አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምናልባት

የቀረበው ሥዕል ላይ እንደሚታየው ሳይመስል አይቀረም የሚሉ አሉ። በትናንትናው የኅዳር ጽዮን ዕለት ገላጣ በሆነ መንገድ ላይ ስራመድ በሰማይ የሚበሩ እርግቦች ከአካባቢዬ ከነበሩ ሰዎች ሁሉ ነጥለው ‘ሸክማቸውን’ መላው ሰውነቴ ላይ አራገፉብኝ። አንዳንዶቹ፤ “በል ሎተሪ ተጫወት!” ይሉኝ ነበር፤ በመገረም።

ኮከብ እንደ ፀሐይ የራሷ ብርሃን አላት፤ ታበራለች ፥ ጨረቃ ግን ብርሃን ትሰርቃለች እንጅ የራሷ ብርሃን የላትም፣ ጨለማ ናት።

[መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፲፱፡፩፥፪]

ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል። ቀን ለቀን ነገርን ታወጣለች፥ ሌሊትም ለሌሊት እውቀትን ትናገራለች።

ቅዱስ ኡራኤል ምስጢረ ሰማይንና እውቀትንም ሁሉ ለሔኖክ እንደገለጸለት ሁሉ ለሔኖክ የልጅ ልጅ ለኖኅም በዚያ መከራ ቀን መርከብ ለመስራት በሚያዘጋጅበት ጊዜ ምክር በመለገስ ቁሳቁስ በማቅረብ ከመርከብም ከወጣ በኃላ በሽምግልናው ዘመን ቅዱስ ኡራኤል አልተለየውም ነበር።

  • 👉 ኡራኤል የሚለው ስም `ኡር‘ እና ‘ኤል‘ ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
  • 👉 ኡር ማለት በእብራይስጥ ብርሃን ማለት ሲሆን ኤል–ማለት ደግሞ አምላክ ማለት ነው ።
  • 👉 አንድ ላይ ሲነበብ –ኡራኤል ማለት የብርሃን አምላክ ወይም የብርሃን ጌታ ማለት ነው ።

ቅዱስ ኡራኤል ከ፯/7ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ፣ ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልዓክ ነዉ። በመሆኑም መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል። [መጽሐፈ ሔኖክ ፮፥፪] ፣ ምስጢረ ሰማይና እውቀትንም ሁሉ ለሄኖክ የገለጸለት የፀሀይን የጨረቃን የከዋክብትንና የሰማይ ሰራዊትን ብርሃንን የሚመራ እርሱ መሆኑን ለሄኖክ ነግሮታል። ፟[መጽሐፈ ሔኖክ ፳፰፥፲፫]

❖ ድርሳነ ኡራኤል ❖

ምድረ ኢትዮጵያ ፦ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዮሴፍና ሰሎሜ በደመና ተጭነው ከግብጽ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ናግራን ከተባለ ሀገር ደረሱ። በናግራን ሳሉ ጌታ እንዲህ አለ። ከቀኝ ጎኔ የሚፈሰው ደሜ በብርሃናት አለቃ በዑራኤል እጅ ተቀድቶ በቅድሚያ በዚች ሀገር ይፈሳል ወይም ይረጫል። እናቱንም እንዲህ አላት አንቺ በድንግልና ጸንሰሽ በድንግልና እንደወለድሽኝ አምነው የሚያከብሩሽ በእኔም የሚያምኑ ብዙ የተቀደሱ ሰዎች በዚህ ሀገር ይወለዳሉ። ከናግራን ተነስተው ለትግራይ ትይዩ ከሚሆን ሐማሴን ከሚባለው ሀገር ሲደርሱ በምሥራቅ በኩል ከፍተኛ ተራራ ተመለከቱና ወደ ተራራው ሄዱ። ጌታም በተራራው ላይ ሳሉ እናቱን እንዲህ አላት ይቺ ተራራ ምስጋናሽ የሚነገርባት ቦታ ትሆናለች። የተራራዋም ስም ደብረ ሃሌ ሉያ ወይም ደብረ ዳሞ ይባላል። ትርጓሜውም የአምላክ ልጅ የመስቀሉ ቦታና የስሙ መገኛ ወይም አደባባይ ማለት ነው።ከዚያም በኋላ ታቦተ ጽዮን ወደምትኖርበት ወደ አክሱም ደረሱ። ታቦተ ጽዮን ባለችበት ቦታ ሳሉ ባዚን የተባለው የኢትዮጵያ ንጉሥ ታቦተ ጽዮንን ለመሳለም መጣ። የካህናቱ አለቃ አኪን ለንጉሡ የኢሳይያስን መጽሐፍ አነበበለት። የተነበበውም የመጽሐፍ ክፍል ድንግል በድንግልና ጸንሳ በድንግልና ወንድ ልጅ ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ትለዋለች የሚል ነበር። ስደተኞቹ ግን ለንጉሡም ሆነ ለካህናቱ ሳይገለጡ የመጽሐፉን ቃል ከሰሙ በኋላ በደመና ተጭነው ወደ ደብረ ዐባይ ሄዱ ። ጌታም እናቱን እንዲህ አላት ይህች ሀገር እንደአክሱም ለስምሽ መጠሪያ ርስት ትሁን በኋላ ዘመን በቀናች ሃይማኖት ጸንተው ሕጌን የሚያስተምሩ አንቺን የሚወዱ ሰዎች ይኖሩባታል። ከዚያም በኋላ ከደብረ ዐባይ ተነስተው ዋሊ ወደ ሚባለው ገዳም /ወደ ዋልድባ / ሄዱ። በዋልድባ በረሃም ሳሉ በራባቸው ጊዜ ጌታ በዮሴፍ ብትር የአንዱን ዕንጨት ስር ቆፈረ። ሦስት መቶ አስራ ስምንት ስሮችን አወጣና ለእናቱ ብይ ብሎ ሰጣት። እናቱም ይህን የሚመር ዕንጨት አልበላም አለችው። ጌታም በኋላ ዘመን ስምሺን የሚጠሩ አንቺን የሚያከብሩ ብዙ መናንያን ይህን እየበሉ በዚህ ቦታ ይኖራሉ። ዕንጨቱም የሚጣፍጥ ይሆንላቸዋል አላት። ከዚህ በኋላ በደመና ተጭነው ከዋልድባ ወደ ጣና የባሕር ወደብ ሄዱ። በጣና ደሴትም ደጋግ ሰዎች ተቀብለዋቸው ሦስት ወር ከአስር ቀን ተቀመጡ። የኢትዮጵያ ሰዎች በደስታ ተቀብለዋቸዋል እንደ ግብፃውያን አላሰቃዩአቸውም ። በጥር አስራ ስምንት /፲፰/18/ ቀን ዑራኤል መጥቶ የሄሮድስን መሞት ነገራቸው ወደ ሀገራቸው ይመለሱ ዘንድ በደመና ከተጫኑ በኋላ ጌታ እናቱን እንዲህ አላት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙትን ተራራዎች ሁሉ ለስምሽ መታሰቢያ ይሆኑሽ ዘንድ አሥራት አድርጌ ሰጥቼሻለሁ ። ብሎ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙትን ተራራዎችን ሜዳዎችን ኮረብታዎችን አሳያት። እመቤታችን ሁሉንም ቦታዎች እየተዘዋወረች እንድታይ ልጅዋን ጠየቀችው። ልጅዋም የሚመለሱበት ጊዜ እንደደረሰ ነገራት። በብሩህ ደመና ላይ ተቀምጠው ክፍላተ አህጉር እየተዘዋወሩ ተራራዎችን ወንዞቸን አስጐበኛት የኢትዮጵያን ምድር ከጐበኙ በኋላ በደመና ተጭነው ጥር 29 ቀን ምድረ ግብፅ ደረሱ። ወደ ኢትዮጵያ የገቡት በቅዱስ ዑራኤል መሪነት ነው። ከግብፅ ወደ ኢትዮጵያ የመግባት ታሪክ በድርሳነ ዑራኤል ላይ በስፋት ተጽፏል።

❖❖❖ የቅዱስ ኡራኤል ፀሎት በያለንበት ይድረስ!ቅዱስ ኡራኤል ኢትዮጵያን የጽዮንን ልጆችን አደራ፤ በእሳት ሰረገላ በነበልባል ታጅበህ ለተልዕኮ የምትፋጠን የአምላካችን አገልጋይ ወራዙተ ኢትዮጵያን በብርሐናዊ ክንፍህ ሸፍነህ ከመርዘኞች የሞት ቀስት ከቀሳፊ ነገር ሁሉ ሰውረን!❖❖❖

❖ Colors of Zion / የጽዮን ቀለማት

የኅዳር ጽዮን ማርያም / Annual feast of St. Mary of Zion

This is a feast colorfully celebrated every year on Hidar 21 (November 30) at every church dedicated to St. Mary. The day is observed with special fervor particularly in Axum Tsion where the Ark of the Covenant is housed safely. The occasion is attended by massive Christian pilgrimages from all over Ethiopia and also foreign visitors making it one of the most joyous annual pilgrimages in Axum, the sacred city of Ethiopians.

The Church of Our Lady Mary of Zion claims to contain The original Ark of the Covenant.The Feast of the Ark of the Covenant (locally known as Tabote Tsion) is held in commemoration of different historical events including the coming of The Ark of the Covenant to Ethiopia and the construction of the first church dedicated to St. Mary in Axum.

The day also marks the destruction of Dagon by the power of The Ark of God, as recorded in the Bible, and the return of The Ark to Israel after seven months of exile at the Dagon’s house in Philistine. (1 Samuel 4; 6)

________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

Monkeypox Likely Spread By Sex at Two Gay Raves in Europe, Expert Says

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 23, 2022

💭 የጦጣ ፈንጣጣ ወረርሽኝ በአውሮፓ በሁለት የግብረ ሰዶማውያን የጭፈራ ቦታዎች ላይ በጾታ ግኑኝነት አማካኝነት ተሰራጭቶ ሊሆን ይችላል ሲሉ የዓለም ጤና ድርጅት ባለሙያ ተናግረዋል።

💭 A leading adviser to the World Health Organization described the unprecedented outbreak of the rare disease monkeypox in developed countries as “a random event” that might be explained by risky sexual behavior at two recent mass events in Europe.

In an interview with The Associated Press, Dr. David Heymann, who formerly headed WHO’s emergencies department, said the leading theory to explain the spread of the disease was sexual transmission among gay and bisexual men at two raves held in Spain and Belgium. Monkeypox has not previously triggered widespread outbreaks beyond Africa, where it is endemic in animals.

“We know monkeypox can spread when there is close contact with the lesions of someone who is infected, and it looks like sexual contact has now amplified that transmission,” said Heymann.

That marks a significant departure from the disease’s typical pattern of spread in central and western Africa, where people are mainly infected by animals like wild rodents and primates and outbreaks have not spilled across borders.

To date, WHO has recorded more than 90 cases of monkeypox in a dozen countries including Britain, Spain, Israel, France, Switzerland, the U.S. and Australia.

Madrid’s senior health official said on Monday that the Spanish capital has recorded 30 confirmed cases so far. Enrique Ruiz Escudero said authorities are investigating possible links between a recent Gay Pride event in the Canary Islands, which drew some 80,000 people, and cases at a Madrid sauna.

Heymann chaired an urgent meeting of WHO’s advisory group on infectious disease threats on Friday to assess the ongoing epidemic and said there was no evidence to suggest that monkeypox might have mutated into a more infectious form.

Monkeypox typically causes fever, chills, rash, and lesions on the face or genitals. It can be spread through close contact with an infected person or their clothing or bedsheets, but sexual transmission has not yet been documented. Most people recover from the disease within several weeks without requiring hospitalization. Vaccines against smallpox, a related disease, are also effective in preventing monkeypox and some antiviral drugs are being developed.

Source: NBC

❖❖❖[የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ ፲፮፥፪]❖❖❖

“ፊተኛውም ሄዶ ጽዋውን በምድር ውስጥ አፈሰሰ፤ የአውሬውም ምልክት ባለባቸው ለምስሉም በሚሰግዱ ሰዎች ክፉኛ የሚነዘንዝ ቍስል ሆነባቸው።”

❖❖❖[ወደ ሮሜ ሰዎች ምዕራፍ ፩፥፳፮፡፳፯]❖❖❖

ስለዚህ እግዚአብሔር ለሚያስነውር ምኞት አሳልፎ ሰጣቸው፤ ሴቶቻቸውም ለባሕርያቸው የሚገባውን ሥራ ለባሕርያቸው በማይገባው ለወጡ፤ እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ለባሕርያቸው የሚገባውን ሴቶችን መገናኘት ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወታቸው ተቃጠሉ፤ ወንዶችም በወንዶች ነውር አድርገው በስሕተታቸው የሚገባውን ብድራት በራሳቸው ተቀበሉ።”

❖❖❖ [Revalation 16:2] ❖❖❖

The first angel went and poured out his bowl on the land, and ugly, festering sores broke out on the people who had the mark of the beast and worshiped its image.

❖❖❖ [Romans 1:26-27] ❖❖❖

“For this reason God gave them up to vile passions. For even their women exchanged the natural use for what is against nature. Likewise also the men, leaving the natural use of the woman, burned in their lust for one another, men with men committing what is shameful, and receiving in themselves the penalty of their error which was due.”

💭 ገዳዩ የጦጣ በሽታ ሰዶማውያንን አጠቃ | ስሕተት ያበዙት ሊቀ ትጉሃን በዚህ ትንቢት ትክክል ነበሩ

______________

Posted in Ethiopia, Health, Infos, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

Strong mag. 5.0 earthquake in Ethiopia | ጠንካራ የመሬት መንቀጥቀጥ በኢትዮጵያ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 24, 2021

Strong mag. 5.0 earthquake – Somalia Regional State, 92 km northwest of Dire Dawa, Ethiopia, on Sunday, Oct 24, 2021 5:26 PM

❖❖❖ ያው! በድጋሚ በአቡነ አረጋዊ ዕለት!❖❖❖

✞✞✞[የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ ፲፮፲፰]✞✞✞

መብረቅና ድምጽም ነጎድጓድም ሆኑ፥ ትልቅም የምድር መናወጥ ሆነ፤ ሰው በምድር ከተፈጠረ ጀምሮ እንዲህ ያለ ታላቅ መናውጥ ከቶ አልነበረም፤ ከሁሉ በለጠ። ታላቂቱም ከተማ በሦስት ተከፋፈለች፥ የአሕዛብም ከተማዎች ወደቁ። ታላቂቱም ባቢሎን የብርቱ ቍጣው ወይን ጠጅ የሞላበትን ጽዋ እንዲሰጣት በእግዚአብሔር ፊት ታሰበች። ደሴቶችም ሁሉ ሸሹ ተራራዎችም አልተገኙም።”

✞ይህ ከአክሱም/ አድዋ ጋር የተያያዘ ነው፤✞ ዛሬ አድዋ በፋሺስቱ የኦሮሞ አገዛዝ ተዋጊ አውሮፕላኖች ተደብድባለች

በትግራይ በጽዮናውያን ላይ ከተከፈተው የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ጋር የተያያዘ ነውን? አዎ! የሚገርም ነው በሶማሊያ እና ኦሮሚያ ህገወጥ ክልሎች መከሰቱ ለዚያውም “አድዋ” የተሰኘው የተኛ እሳተ ገሞራ ነቃ ነቃ በሚልበት አቅራቢያ። ዋው!

በተጨማሪ ከዚሁ ጋር በተያያዘ፤ እርቀት የማይወስነው መለኮታዊ ኃይል በአትላንቲክ ውቂያኖስ አፍሪቃ ጠረፍ በምትገኘውና የስፔይን ግዛት በሆነችው የላስ ፓልማስ ደሴት ኃይለኛ የእሳተ ገሞራን ቀስቅሷል። ይህ በጣም የሚፈራው እሳተ ገሞራ የሚፈጥረው የመሬት መንሸራተትና፣ የሱናሚ ጎርፍ አውሮፓን እና ምስራቅ አሜሪካን አውድሞ በብዙ ሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሊገድል ይችላል። ይህ ለብዙ ዓመታት ሲጠብቅ የነበረ አስፈሪ ትንቢት ነው። የቱሪስቶች መናኸሪያ ከሆኑት ከካናሪ ደሴቶች መካከል በሆነችው ላስ ፓልማስ ልክ ከወር በፊት እሳተ ገሞራው ፈንድቶ የላቫ ፍሰቱ እስከ ዛሬው ዕለት ድረስ ቀጥሏል። ከደሴቲቷ ሰማኒያ አምስት ሺህ ነዋሪዎች መካከል አሥር ሺህ የሚሆኑት ተፈናቅለዋል።

አንዳንድ ታዋቂ ሳይንቲስቶች እርግጠኞች ሆነው እንደሚናገሩት ከዚህች ደሴት የሚቀሰቀሰው ከፍተኛ የእሳተ ገሞራ በሰሜን አሜሪካ ምስራቃዊ ዳርቻ (ኒው ዮርክ) እና የሜዲትራንያን ባሕር አዋሳኝ በሆኑ የአውሮፓ ሃግራት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሊገድል ይችላል፤ ይህ እስኪሆን ድረስ የጊዜ ጉዳይ ብቻ እንደሆነም ያስጠነቅቃሉ።

❖❖❖“ሰዶምና ገሞራ | የጣልያኑ እሳት ገሞራ በድጋሚ ፈነዳ | አክሱም ጽዮን + ደብረ አባይ + ደብረ ዳሞ”❖❖❖

❖❖❖ ጥንታዊው የአቡነ አረጋዊ ገዳም ደብረ ዳሞ በድጋሚ ተዘረፈ፣ በቦምብ ተደበደበ ❖❖❖

🔥 👉 ❖ አደገኛውና የአውሮፓ ከፍተኛው በጣሊያን ሃገር ኤትና በተሰኘው ተራራ ላይ የሚገኘው ንቁ እሳተ ጎሞራ ትናንትና በሲሲሊ ደሴት የተፋው ቀላጭ አለት ይህን ይመስል ነበር። አባታችን አቡነ አረጋዊውን ያየሁ መስሎ ነው የታየኝ።

በኤዶማውያኑ እና እስማኤላውያኑ የዓለማችን ፈላጭ ቆራጮች የበላይነት እየተመራ በእነ አረመኔው ግራኝ አብዮት አህመድ አሊ በትግራይ ሕዝብ ላይ እየተካሄደ ያለው ግፍ የኛዎቹን ከሃዲዎች ብቻ ሳይሆን መላው ዓለምን በማያውቁትና ባላሰቡት መልክ ያስጨንቃቸዋል፤ ገና ደም ያስለቅሳቸዋል። ቀላል ነገር እንዳይመስለን! የእግዚአብሔር ቅዱሳን ከፍተኛ ጦርነት ላይ ናቸው። የጽላተ ሙሴን እና የቅዱሳኑን ኃይል ለመፈተነ/ለመፈታተን ሲሉ ነው ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እስከ ሃያላኑ ሃገራት ሁሉም በህብረት ጸጥ ብለው ኮሮና ያላጠፋችላቸውን ሕዝባችንን ለመበቀልና የሕዝባችንን ሰቆቃ ዓይኖቻቸውን ገልጠው በማየት ላይ የሚገኙት። ግን ቀድመው አንድ በአንድ በእሳቱ የሚጠረጉት እነርሱው ይሆናሉ።

👉 ኤትና – ኤርታ አሌ – እሳተ ገሞራ – ሰዶምና ገሞራ

ኤርታ አሌ ዝግጁ ነው፤ እነ ግራኝንም እየጠበቃቸው ነው!

በደንብ እናስተውል፤ አክሱም ጽዮን፣ ደብረ አባይ፣ ደብረ ዳሞ ሁሉም በጽዮን ማርያም መቀነት አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ቀለማት ያሸበረቁ ገዳማት ናቸው፤ ይህን ከትግራይ ሕዝብ ለመንጠቅና ተዋሕዷዊውንም ከአምላኩና ከጽዮን እናቱ ጋር ለማጣላት አህዛብ የዋቄዮ-አላህ ልጆች፣ መናፍቃንና ሰለጠንን ባዮቹ “ኢ-አማንያኑ” የክርስቶስ ተቃዋሚዎች በህብረት ተግተው እየሠሩ ነው።

____________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, News/ዜና, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

Earthquake in Ethiopia 6-7? | የመሬት መንቀጥቀጥ በኢትዮጵያ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 17, 2021

✞✞✞[የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ ፲፮፲፰]✞✞✞

መብረቅና ድምጽም ነጎድጓድም ሆኑ፥ ትልቅም የምድር መናወጥ ሆነ፤ ሰው በምድር ከተፈጠረ ጀምሮ እንዲህ ያለ ታላቅ መናውጥ ከቶ አልነበረም፤ ከሁሉ በለጠ። ታላቂቱም ከተማ በሦስት ተከፋፈለች፥ የአሕዛብም ከተማዎች ወደቁ። ታላቂቱም ባቢሎን የብርቱ ቍጣው ወይን ጠጅ የሞላበትን ጽዋ እንዲሰጣት በእግዚአብሔር ፊት ታሰበች። ደሴቶችም ሁሉ ሸሹ ተራራዎችም አልተገኙም።”

🔥 4.5 / 4.3 አማካይ መጠን የመሬት መንቀጥቀጥ

ዓርብ፣ ጥቅምት ፭/፳፻፲፬ ዓ.ም(አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ)

እሑድ፣ ጥቅምት ፯/ ፳፻፲፬ ዓ.ም (ሥላሴ)

‘አድዋ’ በተባለው እሳተ ገሞራ አካባቢ

(ሶማሌ + ኦሮሚያ በተሰኙት ፀረ-ኢትዮጵያ ክልሎች)

🔥 6 እስከ 7 ከፍተኛ መጠን ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ

በመጭው ማክሰኞ ጥቅምት ፱/ ፳፻፲፬ ዓ.ም (ጨርቆስ)

‘አድዋ’ በተባለው እሳተ ገሞራ አካባቢ

(ሶማሌ + ኦሮሚያ በተሰኙት ፀረ-ኢትዮጵያ ክልሎች)

ይህ ከአክሱም/አድዋ ጋር የተያያዘ ነው፤✞

በትግራይ በጽዮናውያን ላይ ከተከፈተው የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ጋር የተያያዘ ነውን? አዎ! የሚገርም ነው በሶማሊያ እና ኦሮሚያ ህገወጥ ክልሎች መከሰቱ ለዚያውም “አድዋ” የተሰኘው የተኛ እሳተ ገሞራ ነቃ ነቃ በሚልበት አቅራቢያ። ዋው!

በተጨማሪ ከዚሁ ጋር በተያያዘ፤ እርቀት የማይወስነው መለኮታዊ ኃይል በአትላንቲክ ውቂያኖስ አፍሪቃ ጠረፍ በምትገኘውና የስፔይን ግዛት በሆነችው የላስ ፓልማስ ደሴት ኃይለኛ የእሳተ ገሞራን ቀስቅሷል። ይህ በጣም የሚፈራው እሳተ ገሞራ የሚፈጥረው የመሬት መንሸራተትና፣ የሱናሚ ጎርፍ አውሮፓን እና ምስራቅ አሜሪካን አውድሞ በብዙ ሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሊገድል ይችላል። ይህ ለብዙ ዓመታት ሲጠብቅ የነበረ አስፈሪ ትንቢት ነው። የቱሪስቶች መናኸሪያ ከሆኑት ከካናሪ ደሴቶች መካከል በሆነችው ላስ ፓልማስ ልክ ከወር በፊት እሳተ ገሞራው ፈንድቶ የላቫ ፍሰቱ እስከ ዛሬው ዕለት ድረስ ቀጥሏል። ከደሴቲቷ ሰማኒያ አምስት ሺህ ነዋሪዎች መካከል አሥር ሺህ የሚሆኑት ተፈናቅለዋል።

አንዳንድ ታዋቂ ሳይንቲስቶች እርግጠኞች ሆነው እንደሚናገሩት ከዚህች ደሴት የሚቀሰቀሰው ከፍተኛ የእሳተ ገሞራ በሰሜን አሜሪካ ምስራቃዊ ዳርቻ (ኒው ዮርክ) እና የሜዲትራንያን ባሕር አዋሳኝ በሆኑ የአውሮፓ ሃግራት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሊገድል ይችላል፤ ይህ እስኪሆን ድረስ የጊዜ ጉዳይ ብቻ እንደሆነ ያስጠነቅቃሉ።

____________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith, News/ዜና, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: