Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘እየሱስ ክርስቶስ’

Apostle Matthew in Ethiopia | ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ በአክሱማዊቷ ኢትዮጵያ | በፍርድ ቀን፤ ከ፪ሺ ዓመት በኋላ፤ “ወንጌል አልተሰበከልንም” ማለት የለም

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on October 22, 2022

✞✞✞

ጥቅምት ፲፪/ 12፤ የሐዋርያውና ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ በዓለ ዕረፍቱ ነው፤ ከቅዱስ ማቴዎስ ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡

💭 ፊልሙን ከዚህ ድንቅ ጽሑፍ ጋር እናነጻጽረው፦

👉 በ መሪራስ አማን በላይ

የዓለም መድኃኒት እየሱስ ክርስቶስ እኔን ማቴዎስን መርጦ ተከተለኝ አል እኔም ስላመነታ ተከተልኩት የመዳን ተስፋ የሆነውን የወንጌሉን ቃል እንድንሰማና ከእርሱ አፍ የሰማሁትንም ለዓለም እንዳሰማ ልኮኛል።

መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ሊያድን ከእግዚአብሔር አብ የመጣ ከእርሱም ሌላ አዳኝና መሐሪ ወደ እግዚአብሔር መንግሥትም የሚያገባ እንደሌለ የአየሁትን ልመሰክር የሰማሁትን ቃል ለእናንተ ለአሰማ ከቃሉ የተነሣ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ትሆኑ ዘንድ በስሙም ትጠመቁ ዘንድ ልኮኛል። ከአብና ከልጁም ከእኛም ህብረት እንዳላችሁ ያንጊዜ ታውቃላችሁ፤ ዓለሙ ግን የፈጠረውን ተጣሪውን ትቶ ላልፈጠረው ምህረት የአደረገለትን ጌታውን ትቶ ሥቃይንና መአትን ለሚያመጣበት ለክፉ መንፈስ እየተገዛና የክፉ መንፈስ ባሪያ በመሆን የኃጢአትን ንጉሥ ዲያብሎስን እያገለገለ ይገኛል።

ይህ ክፉ መንፈስ በሰዎች ልብ ላይ መርዙን እንደረጨ ሁሉ እንዲሁ በእግዚአብሔር ልጆች ላይ ደጋኑን ወጥሮ ቀስቱን እንደቀተረ ነው። አንዳንዶች ወገኖች ለእርሱ ሲማረኩለት ጥቂቶችም የሆኑ የእግዚአብሔር ምርጥ ሕዝቦች ከፍጹም እምነታቸውና ከመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የተነሣ በጸሎት ድል ያደርጉታል፡ በጾምም ያሸንፉታል ያሳፍሩታልም። ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣው ለእግዚአብሔር ልጅ ለእየሱስ ክርስቶስ ታማኝ ሠራዊቱ ናቸው። መንፈሱን ተላብሰዋል፣ ጸጋውን ተሞልተዋል፣ ኃይሉንም ታጥቀውታል። ሥልጣንም በአፋቸው ተሰጥቷል። እኒሁ እናንተም የእግዚአብሔር አብን ምህረት የልጁንም የእየሱስ ክርስቶስን አዳኝነት የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ልትቀበሉትና ልትለብሱት ለመጣችሁ ሁሉ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንላችሁ። የልጁም የእየሱስ ክርስቶስ ፍቅር ይፅናላችሁ። አሜን።

እቴ ህንድኬ ዣን ንግሥተ ነገሥታት ዘኢትዮጵያ በሆነች በአሥራ አንደኛው ዘመነ መንግሥትዋ ከእየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርት አንዱ ቅዱስ ማቴዎስ በመርዌ ከተማ የሚኖሩትን ህዝቦች ቃለ ወንጌል እየሰበከ አስተምሮ ማጥመቁን ሰማች፤ ይዘውት ወደ እርስዋ እንዲመጡ መልእክተኞችን ወደ ወንጌላዊ ማቴዎስ ላከች፡ ነገር ግን ስለክርስቶስ መወለድና ብዙ ታእምራትንና ድንቅ የሆኑ ሥራዎችን እየሱስ ክርስቶስ መሥራቱን ሰምታ ስለነበረ የእየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ነው ሲሏት መልኩን ለማየት የሚያስተምረውንም ለመስማት ጓጉታ እርሱ የእግዚአብሔር አገልጋይ ከመምጣቱ እኔ መሄድ አለብኝ ብላ በብዙ ሺህ ሠራዊት ታጅባ ወደ መርዌ /መርዋ/ በ70 ዓ.ም. ሄደች።

በዚያም ቅዱስ ማቴዎስን አግኝታ እንዲህ አለችው፦

“እየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እኛ እንደተላከና የሰላም አለቃ የዘለዓለም አባት እንደሆነ ከነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተነሣ አምናለሁ፤ ነገር ግን በውኃ ጥምቀት ከእግዚአብሔር መወለድን የእግዚአብሔር ልጅ መባልን አላውቅም ነበር፡ አሁን ግን አንተን ወደ እኛ የላከህና ከአንተ ላይ የአለ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ከስብከትህ የተነሣ ገለፀልኝ፡ የምትነግረን ቃለ ወንጌል ህይወት መድኃኒት እንደሆነ አወኩ በእርሱም አመንኩ ስለዚህ አጥምቀኝ።” አለችወ።

ቅዱስ ማቴዎስም እግዚአብሔር ወደ እርሱ እንደላካት አውቆ በደስታ ከሠራዊትዋ ጋር ወደ ግዮን ወንዝ ወረዱ ከዚያም ከእርሱዋ ጋር የነበረው ሠራዊትና መኳንንት ሁሉ በእየሱስ ክርስቶስ ስም አጠመቃቸው። እንዲህ ሲል፦

“በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠቃችሁ አለሁ!” እያለ።

እቴ ህንደኬ ዣን እንደህዝብዋ ተጠመቀች፤ ፍጹም ክርስቲያን ሆነች፤ ከዚያም ቅዱስ ማቴዎስን ከደቀ መዛሙርቶቹ ጋር ወደ አክሱም አምጥታ አክሎስ የሚባለውን ባልዋን ልጆችዋን ቤተሰብዋን ሁሉ በእየሱስ ክርስቶስ ስም አስጠመቀች። ቅዱስ ማቴዎስ በአክሱም አድርጎ ወደ ኢየሩሳሌም ሄደ፤ ከበርቶሎሜዎስ ቀጥሎ ለመጀመሪያ ጊዜ የኑብያን፣ የኢትዮጵያንና የናግራንን ሰዎች የአጠመቀ ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት አንዱ ወንጌላዊ ማቴዎስ ነው።

እንደዚህም ሆነ እቴ ህንደኬ ዣን ክርስቲያን በሆነች በአሥራ ሦስት አመትዋ አቡሳውያን /አበሾች/ የሚባሉት የአክሱም የአዶሊስ ሕዝቦችና ፈላስያን /ፈላሾች/ በሌዋውያን ምክር ወንድሙዋን ንጉሠ ባህር ዘዝቃሌስ ተብሎ የነበረውን ከተብን አፄ ባህር ሰገድ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ብለው በበላዩዋ ላይ አነገሡት፤ እቴ ህንደኬን ዣንና አክሎስ ልጆቸዋን ገድለው አቃጠሏት። እርሷም በሰማእትነት በሰማንያ ሦስት /83/ በነገሠች በ24 ዘመነ መንግሥቱዋ አረፈች።

አፄ ባህር ሰገድ ተብሎ በነገሠው በከተብ ዘመነ መንግሥት እየሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ክርስቶስ ተወልዶአል ብሎ የሚያስተምርና የሚአምን ሰው ቢገኝ እንዲገደል በአዋጅ ተነገረ።

የእስራኤል ልጆች የሆኑ ሌዋውያን ካህናት እየሱ ክርስቶስም አይደለም ስሙንም መድኃኒት አይደለም ለማለት “ኢየሱስ” እንጂ “እየሱስ” ብላችሁ አትጥሩ ብለው በምኩራብ በአደባባይ በቢተ መቅደስ በገበያ አስተማሩ።

እግዚአብሔርም የእስራኤልን ልጆችን ጥጦስ የሚባለውን አስነስቶ በጭካኔ እንደገደላቸው ሁሉ እንዲሁ የባህር ሰገድን መርከብ ሠራተኞችና በአዶሊስ በዳህቂቅ የሚኖሩትን ቤተ እስራኤል ሂክሶስ የሚባሉት የግሪኮችን ሰዎች አስነስቶ አስገደላቸው።

ንጉሠ ነገሥቱ ባህር ሰገድ ክርስቶስ እየሱስ በተወለደ 105 መታራ ከሚባለው አገር ላይ ከግሪኮች ከሮማውያን ጋር ጦርነት አድርጎ ተማርኮ በ81 ዓመት እድሜው በነገሠ በ22 ዘመነ መንግሥቱ ሞተ።

አንዳንድ ጎሣዎችና በጎሣዎች ውስጥ የሚገኙ ነገዶች ቃለ ወንጌል ያልተሰበከላቸው በጨለማ ዓለም ውስጥ ከመኖራቸው የተነሣ ከንቱ የሆነ አምልኮት ያመልኩና ለሚያመልኩት ነገር እንስሳና አእዋፍ ዶሮ ያርዱለት ነበር። ከዚያም አልፈው ሰውን አስረው እንደ እንስሳ የሚያቀርቡና የሚሰው ነበሩ። የሚያመልኳቸው ተራራዎች ዛፎች ሸለቆዎች ኮረብታዎች አራዊቶች ነበሩ። እንደዚሁ አስቀያሚ መልክ ያላቸው ቅርጾችን ያመልኩባቸው ነበር።

ነገር ግን የሰው ልጅ ክቡር ፍጥረት እንደሆነ ከሁሉም በላይ መሆኑን የሚያምኑና ሁሉን የፈጠረና ቻይ ጌታ እግዚአብሔር ብቻ አንድ አምላክ እንደሆነ በነቢያት ላይ አድሮ ለሰው ልጆች ህግና ሥረአት እንዲኖራቸው የፈቀደ ወይም የአዘዘ ትእዛዙንም የሚፈጽሙ የመልከ ጼዴቅ ካህን ዘሮች የእግዚአብሔር ልጆች ተብለው የሚጠሩ ኢትዮጵያውያን ብቻ ነበሩ። በኋላ ዘመን ደግሞ የአብርሃም ዘሮች በሙሴ አማካኝነት አንድ እግዚአብሔርን ማምለክ ጀመሩ። ከዚህ በኋላ ነው ሁለቱ ጎሣዎች አንድ እግዚአብሔርን በማምለክና በማመን ሲኖሩ የአለም መድኃኒት እየሱስ ክርስቶስ በቤተ ልሔም በተወለደ ጊዜ ሊሰግዱለት ሄደው ከሌላው ዓለም በፊት የተገኙትና ገጸ-በርከት አቅርበው ወደ ሀገራቸው በሰላም የተመለሱ።

አሁንም እኛ ኢትዮጵያውያን የክርስቶስን ትእዛዝና ትምህርት የተቀበልን እንደ ኃዋርያት ማለት ብሉያት መጽሐፍትን አስቀድመን እንደተቀበልን፡ መጽሐፍተ አዲሳትንም ወዲያውኑ ነው የተቀበልንና አምነን በጌታችን በእየሱስ ክርስቶስ ስም የተጠመቅነው፤ በስሙ ክርስቲያኖች የተባልነው እንጂ ሐዲሳትን መጻሕፍትን ብቻ እንደተቀበሉት እንደ አሕዛቦች አይደለም። ለዚህ ሁሉ ምስክራችን ፈጣሪያችን እግዚአብሔርና እግዚአብሔር ያዘዘው የአምልኮታችን ሥርአት ነው። እሄውም የማይታየው አምላክ በነቢያት ሰው እንደሚሆን አስቀድሞ መነገሩ በሐዋርያት ሰው መሆኑ መሰበኩን የሚያበስሩትን ብሉያትና ሐዲሳትን /በማስማማታችን/ በማዋሐዳችን እምነታችን ተዋሕዶ ሃይምንት ተብሏል። ምስጢሩም ቃል ሥጋ በመሆኑ የነቢያት ትንቢት በመፈጸሙ ተዋሕዶ ሃይማኖት አሰኝቶታል።

እሄን ክብርና ጸጋ ለሰጠን ለአንድ እግዚአብሔር የአምልኮት ምስጋናና ሥግደት ይገባዋል። እግዚአብሔር ለዘለዓለም ለሰው ልጆች ሰላምንና ፍቅርን ሕብረትንም ይስጠን። ምህረቱና ቸርነቱም በሰማይ እንደሆነ በምድርም ይሁን። አሜን።

______________

Posted in Ethiopia, Faith, Saints/ቅዱሳን | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የይሑዳ አንበሣ ሞትን ድል አድርጎ ተነሥቷል | ጎይታ ተንሢኡ | He Is Risen

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 2, 2021

👉 ገብርኤል 👉 ማርያም 👉 ኡራኤል 👉 ጊዮርጊስ 👉 ተክለ ሐይማኖት 👉 ዮሴፍ 👉 መድኃኔ ዓለም

✞✞✞ተነስቷል!✞✞✞

ሰማያት (ሰማያውያን መላእክት) የደስታ በዓልን ያደርጋሉ፤ ደመናት (ቅዱሳን) የደስታን በዓል ያደርጋሉ። ምድር (ምድራውያን ሰዎችም) በክርስቶስ ደም ታጥባ (ታጥበው) የፋሲካን በዓል ታደርጋለች (ያደርጋሉ)። ያከብራሉ (ታከብራለች)። ዛሬ በሰማያት (በመላእክት ዘንድ) ታላቅ ደስታ ኾነ፤ ምድርም በክርስቶስ ደም ታጥባ የፋሲካን የነጻነት በዓል ታደርጋለች። የትንሣኤያችን በኵር ክርስቶስ ከሙታን ሰዎች ዂሉ ተለይቶ ቀድሞ ተነሣ፤” (ድጓ ዘፋሲካ)

✞ ✞ ✞በችግር፣ በፈተና፣ በመከራ፣ በድካም፣ በስቃይና በስደት ላይ ያሉትን አባቶቻችንና እናቶቻችንን፣ ወንድሞቻችንና እኅቶቻችንን እንዲሁም ልጆቻቸውን ሁሉ እግዚአብሔር ወልድ ተነስቶላቸዋልና በየሰዓቱ ያስባቸው፤ አሜን።✞ ✞ ✞

✞✞✞ተነስቷል!✞✞✞

ተነስቷል ጌታ ተነስቷል

ከሙታን መሃል የለም ጌታ ተነስቷል

ከሙታን መሃል የለም ክርስቶስ ተነስቷል

በመቃብር ተኛ ተነስቷል

ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ……….

ሞትን አሸንፎ ……….

የዓለም መድኀኒት ……….

ግርማን ተጐናጽፎ ………

ይኸው ተነሳልን ………

ሞትን አሸንፎ መውጊያውን ሰባብሮ

ተነስቷል ክርስቶስ ጠላትን መዝብሮ

በሞት ያሸለበው ተነስቷል

የሞት ባለጸጋ ……….

የትንሣኤው በኩር ………..

አልፋና ኦሜጋ ……….

ግርማን ተጐናጽፎ ………

እሁድ በማለዳ ……..

ማኅተሙን ተፈታ ድንጋዩም ደቀቀ

ሲኦልም ተሻረ ዲያብሎስ ወደቀ

ሞትና መውጊያውን ተነስቷል

ከጥልቁ ጣለልን ………

የልባችን መብራት ………

ይብራ ለአምላካችን ……….

ወተንሥአ እንበል ………..

ሲኦል ተሻረልን ………..

ትንሣኤው ልዩ ነው ………..

የመከራ ቀንበር ከእኛ አርቆልናል

የሞት ኃይልን ሰብሮ ጌታችን ተነስቷል።

[፩ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕራፍ ፲፭]

፶ ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እላለሁ። ሥጋና ደም የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊወርሱ አይችሉም፥ የሚበሰብሰውም የማይበሰብሰውን አይወርስም።

፶፩-፶፪ እነሆ፥ አንድ ምሥጢር እነግራችኋለሁ፤ ሁላችን አናንቀላፋም ነገር ግን የኋለኛው መለከት ሲነፋ ሁላችን በድንገት በቅጽበት ዓይን እንለወጣለን፤ መለከት ይነፋልና ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ እኛም እንለወጣለን።

፶፫ ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሊለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሊለብስ ይገባዋልና።

፶፬ ዳሩ ግን ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሲለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሲለብስ፥ በዚያን ጊዜ። ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈጸማል።

፶፭ ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ? ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሣትህ የት አለ?

፶፮ የሞት መውጊያ ኃጢአት ነው የኃጢአትም ኃይል ሕግ ነው፤

፶፯ ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።

በዐቢይ ጾም አጋማሽ በደብረ ዘይት/ዘመነ ሃጋይ ባሰብነው የጌታችን ዳግም ምጽአት መሠረት ጌታችን በታላቅ ክብርና በልዕልና እንዲሁም እጅግ በጣም በሚያስፈራ ግርማ ለሁለተኛ ጊዜ በቅርቡ ለፍርድ ይመጣልና ([ራዕይ ፳፪፥፲፪] እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ።)ሁላችንም የፍርድ ቤት ቀጠሮ እንያዝ። በተለይ በክርስቲያኖች ላይ ግፍ እየሠሩ ያሉት፤ በትግራይ/አክሱም ጽዮን ጭፍጨፋውን ዛሬም በማካሄድ ላይ ያለው ከሃዲ ትውልድ ለመጭው የፍርድ ቀን እራሱን ያዘጋጅ። ዝም ያለ ሁሉ የዚህ ከሃዲ ትውልድ አባል ነው። በአክሱም ጽዮን ብቻ አንድ ሺህ ምዕመናን ሰማዕትነትን ተቀብለዋል፤ የሰይጣን ጭፍሮች የሆኑት አረመኔ ገዳዮቻቸው ግን ተገቢውን ፍርድ ያገኛሉ። አንድ ሺህ የዋልድባ መነኮሳትን ያንገላቷቸው፣ ያፈናቀሏቸውና የገደሏቸው በዚህም ኢትዮጵያ ለአንድ ሺህ ዓመታት ርቃኗን እንድትቀር፣ እንድትዋረድና እንድትወድቅ ያደረጓትና ለጉዳዩም ተገቢውን ትኩረት ለመስጠት ያልፈለጉት ግብዞች ሁሉ ምን ዓይነት ፍርድ እንደሚጠብቃቸው ከእኔ ይልቅ እነርሱ እራሳቸው የተሻለ ያውቁታል።

በትግራይ አክሱም ጽዮን ላይ የፀረክርስቲያን ዘመቻ/ጂሃድ በመክፈት እስከ ዛሬዋ ዕለት ድረስ ጭፍጨፋውን፣ ደፈራውን፣ ማሳደዱን፣ ዘረፋውንና ጥላቻውን ያለምንም ሃፍረትና መጸጸት ቀጥለውበታል። ኦሮሞዎች፣ አማራዎች፣ ኢአማንያን፣ አህዛብና መናፍቃን የዋቄዮአላህ ጭፍሮች የትግራይን ሕዝብ ለማጥፋት ከተነሳሱ በዛሬው የፃድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሐይማኖት ዕለት ስድስተኛ ወር ሞላቸው።

👉 እነዚህ ወንጀለኞች፤

በአክሱም ጽዮን ላይ፣

በዋልድባ ላይ፣

በደብረ አባይ ላይ፣

በደንገላት ቅድስት ማርያም ላይ፣

በደብረ ዳሞ አቡነ አረጋዊ ላይ፣

በውቅሮ አማኑኤል ላይ፣

በዛላምበሳ ጨርቆስ ላይ፣

ገዳም ማርያም ውቅሮ እምባስነይቲ

የቸሊ/ግጀት ከሁለት መቶ በላይ ተዋሕዷውያን ሕፃናትና ወጣቶች ጭፍጨፋ!

የእንዳ ማርያም መድኃኒት አዲ ዳዕሮ ጭፍጨፋ

በሌሎች ባልተወራላቸው የትግራይ ዓብያተ ክርስቲያናት፣ ገዳማት እንዲሁም ሌሎች ቦታዎች ላይ

እጅግ በጣም ከባድ ወንጀል ሠርተዋልና የፍርድ ቤት ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል፤ እረፍት የላቸውም፣ እንቅልፍ አይኖራቸውም፤ እንደ ቃኤል እየተቅበዘበዙ ያችን ቀን ይጠብቁ ዘንድ ተወስኗል።

እንግዲህ ይህን በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ በጣም ከባድ የሆነ ወንጀል እየሰሩ ስላሉትና “እግዚአብሔር አያይም፤ አይ እርሱ እንዴትስ ያውቃል? ምን ቸገረን?” እያሉ በክህደት፣ በአመጽና በትዕቢት መንፈስ የሚኩራሩት ኦሮሞዎች፣ አማራዎች፣ ኢአማንያን፣ አህዛብና መናፍቃን የዋቄዮአላህ ወንጀለኞች ሁሉ የዘሯትን በቅርቡ ያጭዷታል፤ የጭንቀት ቀናት በሮቻችሁን ያንኳኳሉ፤ የበቀል ጊዜም እየመጣ ነው፤ ወዮላችሁ! ወዮልን!

[የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፲፮፥፳፯]

የሰው ልጅ ከመላእክቱ ጋር በአባቱ ክብር ይመጣ ዘንድ አለውና፤ ያን ጊዜም ለሁሉ እንደ ሥራው ያስረክበዋል።”

[የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ ፳፩፥፳፪፡፳፯ ]

የተጻፈው ሁሉ እንዲፈጸም ይህ የበቀል ጊዜ ነውና። በዚያን ወራት ለእርጕዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው፤ ታላቅ ችግር በምድር ላይ፥ በዚህም ሕዝብ ላይ ቍጣ ይሆናልና፤ በሰይፍ ስለትም ይወድቃሉ፤ ወደ አሕዛብ ሁሉም ይማረካሉ፤ የአሕዛብም ዘመን እስኪፈጸም ድረስ ኢየሩሳሌም በአሕዛብ የተረገጠች ትሆናለች።

በፀሐይና በጨረቃም በከዋክብትም ምልክት ይሆናል፤ በምድር ላይም አሕዛብ ከባሕሩና ከሞገዱም ድምፅ የተነሣ እያመነቱ ይጨነቃሉ፤ ሰዎችም ከፍርሃትና በዓለም የሚመጣበትን ከመጠበቅ የተነሣ ይደክማሉ፤ የሰማያት ኃይላት ይናወጣሉና። በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ በኃይልና በብዙ ክብር በደመና ሲመጣ ያዩታል።”

✞✞✞የዘ/ት ምርትነሽ ጥላሁን “ሂዱ ንገሩ ለዓለም”✞✞✞

ሂዱ ንገሩ አውሩ ለዓለም

ተነስቷል በዚህ የለም

ተነስቷል በዚህ የለም

መድኃኔዓለም

ሞት የማይችለው የበረታ

ኃያል ነው የማይረታ

ማህተሙን የፈታ

የትንሳኤው ጌታ

ሂዱ ንገሩ አውሩ ለዓለም

ተነስቷል በዚህ የለም

ተነስቷል በዚህ የለም

መድኃኔዓለም

ሞት የማይችለው የበረታ

ኃያል ነው የማይረታ

ማህተሙን የፈታ

የትንሳኤው ጌታ

ገዳዩ ሞት በእርሱ ድል መንሳት ተዋጠና

ሰንሰለቴን ቀንበሬን ተካው ብብገና

ሞት ሆይ መውጊያህ የታል እያልን የምንዘምረው

መስቀልህ ጦር ስምህ ጋሻችን ሆኖልን ነው

ዳንን የምንለው

ሂዱ ንገሩ አውሩ ለዓለም

ተነስቷል በዚህ የለም

ተነስቷል በዚህ የለም

መድኃኔዓለም

ሞት የማይችለው የበረታ

ኃያል ነው የማይረታ

ማህተሙን የፈታ

የትንሳኤው ጌታ

ተሻግረናል ስላሻገርከን ለዘላለም

በመቃብር ሞት ይይዝህ ዘንድ ከቶ አልቻለም

ኃይለኛውን በኃይል አስረኽው ላይፈታ

ዘመርንልህ አሸናፊ ነህ የኛ ጌታ

ከፍ በል በዕልልታ

ሂዱ ንገሩ አውሩ ለዓለም

ተነስቷል በዚህ የለም

ተነስቷል በዚህ የለም

መድኃኔዓለም

ሞት የማይችለው የበረታ

ኃያል ነው የማይረታ

ማህተሙን የፈታ

የትንሳኤው ጌታ

ሞቶ ማዳን ለማን ተችሏል ከአንተ በቀር

ጌትነትህ ስራህ ይኖራል ሲመሰከር

ወዳጄ ሆይ ውበትህ ውብ ነው የሚያበራ

ተጨነቀ ተንቀጠቀጠ ጠላት ፈራ

ዕፁብ ያንተ ሥራ

ሂዱ ንገሩ አውሩ ለዓለም

ተነስቷል በዚህ የለም

ተነስቷል በዚህ የለም

መድኃኔዓለም

ሞት የማይችለው የበረታ

ኃያል ነው የማይረታ

ማህተሙን የፈታ

የትንሳኤው ጌታ

መስክሩለት የምሥራች ነው ታላቅ ዜና

መለክቱ ነጭ ለብሰዋል ድል ነውና

ከተማዋ አንዳች ሆናለች በሌሊቱ

በዝማሬ ተንቀጠቀጠ ወህኒ ቤቱ

ከበሮውን ምቱ

ሂዱ ንገሩ አውሩ ለዓለም

ተነስቷል በዚህ የለም

ተነስቷል በዚህ የለም

መድኃኔዓለም

ሞት የማይችለው የበረታ

ኃያል ነው የማይረታ

ማህተሙን የፈታ

የትንሳኤው ጌታ

ሂዱ ንገሩ አውሩ ለዓለም

ተነስቷል በዚህ የለም

ተነስቷል በዚህ የለም

መድኃኔዓለም

ሞት የማይችለው የበረታ

ኃያል ነው የማይረታ

ማህተሙን የፈታ

የትንሳኤው ጌታ

______________________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የጌታችን ትንሣኤ፣ የድኅነታችን ብሥራት ነው | እንኳን አደረሰን!

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 28, 2019

ሰማያት (ሰማያውያን መላእክት) የደስታ በዓልን ያደርጋሉ፤ ደመናት (ቅዱሳን) የደስታን በዓል ያደርጋሉ፡፡ ምድር (ምድራውያን ሰዎችም) በክርስቶስ ደም ታጥባ (ታጥበው) የፋሲካን በዓል ታደርጋለች (ያደርጋሉ)፡፡ ያከብራሉ (ታከብራለች)፡፡ ዛሬ በሰማያት (በመላእክት ዘንድ) ታላቅ ደስታ ኾነ፤ ምድርም በክርስቶስ ደም ታጥባ የፋሲካን የነጻነት በዓል ታደርጋለች፡፡ የትንሣኤያችን በኵር ክርስቶስ ከሙታን ሰዎች ዂሉ ተለይቶ ቀድሞ ተነሣ፤” (ድጓ ዘፋሲካ)፡”

__________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , | 1 Comment »

ሞትን ድል አድርጎ ተነሥቷል! | እንኳን አደረሰን!

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 8, 2018

ሰማያት (ሰማያውያን መላእክት) የደስታ በዓልን ያደርጋሉ፤ ደመናት (ቅዱሳን) የደስታን በዓል ያደርጋሉ፡፡ ምድር (ምድራውያን ሰዎችም) በክርስቶስ ደም ታጥባ (ታጥበው) የፋሲካን በዓል ታደርጋለች (ያደርጋሉ)፡፡ ያከብራሉ (ታከብራለች)፡፡ ዛሬ በሰማያት (በመላእክት ዘንድ) ታላቅ ደስታ ኾነ፤ ምድርም በክርስቶስ ደም ታጥባ የፋሲካን የነጻነት በዓል ታደርጋለች፡፡ የትንሣኤያችን በኵር ክርስቶስ ከሙታን ሰዎች ዂሉ ተለይቶ ቀድሞ ተነሣ፤” (ድጓ ዘፋሲካ)፡”

በጥንተ ጠላታችን ዲያቢሎስ አሳሳችነት አዳምና ሔዋን የእግዚአብሔርን ሕግ በመተላላፋቸው ሞተ ሥጋና ሞተ ነፍስ ተፈርዶባቸው ነበር፡፡ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ካለው ፍጹም ፍቅር የተነሣ የተፈረደባቸውን ሞት በሞቱ ሊደመስስ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ (ዮሐ. ፩፥፩)፡፡ ሠላሳ ዓመት ሲሞላው በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ፡፡ እንደ ተጠመቀም ልዋል ልደር ሳይል ወደ ገዳመ ቆሮንቶስ ሔደ፡፡ በዚያም ጾመ፤ ጸለየ፡፡ በዲያቢሎስም ተፈተነ፡፡

ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ካስተማረ በኋላ የአዳምና የሔዋንን ዕዳ ደምስሶ ነጻ ሊያደርጋቸው በገባው ቃል ኪዳን መሠረት መከራ ተቀበለ፡፡ በአይሁድ ሸንጎ ፊት ቆመ፤ ምራቅ ተተፋበት፤ ተገረፈ፤ በገመድ ታሥሮ ተጎተተ፤ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሞተ፡፡ በሞቱ ሞትን ድል አድርጎ የአዳምን፣ የሔዋንንና የልጆቻቸውን ዕዳ በደል ደመሰሰ (ማቴ. ፳፯፥፳፰)፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ “ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፤” በማለት እንደ ገለጸው (ሮሜ. ፮፥፭)፣ ሞቱ ሞታችን፤ ትንሣኤው ትንሣኤያችን ነውና የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች በየዓመቱ ጌታ የጾመውን ጾም በመጾም፣ በሰሙነ ሕማማት ደግሞ መከራውንና ስቃዩን በማሰብ የክርስቶስን ቤዛነት እንዘክራለን፤ የነጻነትና የድል በዓላችንንም እናከብራለን፡፡

በጥንተ ጠላታችን ምክንያት አይሁድ ክብርህን ዝቅ ቢያደርጉ፣ ቢያዋርዱህ፣ ቢገርፉህ፣ ርቃንህን ቢሰቅሉህና ቢገድለህ እኛ ግን ‹ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለም ዓለም አማኑኤል አምላኪየ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለም ዓለም ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለም ዓለም – ኃይሌ፣ መከታዬና ረዳቴ ለኾንኸው ለአንተ ለአምላኬ ለአማኑኤል ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ክብርና ምስጋና ጽናትም ለዘለዓለሙ ይገባሃል›፤” እያልን አምላካችንን እናመሰግነዋለን፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ በፊልጵስዩስ ፫፥፲ ላይ “እርሱንና የትነሣኤውን ኃይል እንዳውቅ በመከራወም እንድካፈል ወደ ሙታንም ትንሣኤ ልደርስ ቢኾንልኝ በሞቱ እንደመስለው እመኛለሁ፤” በማለት እንደ ተናገረው ምእመናን እንደ አቅማቸው እያዘኑ፣ እያለቀሱ፣ ከምግብ እየተከለከሉ፣ ጸጉራቸውን እየተላጩ የአምላካንን መከራ ያስባሉ፡፡

ሞትን ድል አድርጎ ተነሥቷል!” የሚለውን የምሥራች ከቤተ ክርስቲያን ለመስማት በናፍቆት ይጠባበቃሉ፡፡ የትንሣኤውን ብሥራት ሰከሙ በኋላም “ጌታ በእውነት ተነሥቷል!” እያሉ ትንሣኤዉን ይመሰክራሉ፡፡ የጌታችን ትንሣኤ፣ የድኅነታችን ብሥራት በመኾኑ ለአምሳ ቀናት ያህል በቅዳሴው፣ በማኅሌቱ፣ በወንጌሉ፣ በሌሎችም ቅዱሳት መጻሕፍት በልዩ ሥርዓት ይዘከራል፡፡ በየአብያተ ክርስቲያኑ “ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን በዓቢይ ኃይል ወሥልጣን አሠሮ ለሰይጣን አግዐዞ ለአዳም ሰላም እምይእዜሰ ኮነ ፍሥሐ ወሰላም” እየተባለ ሞት መደምሰሱ፣ ነጻነት መታወጁ ይበሠራል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

ምንጭ

______

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

የሳውዲ ልዑል መሀመድ፡ በካይሮ ቅዱስ ማርቆስ ቤ/ ክርስቲያን፡ እየሱስ ክርስቶስ እግር ሥር ሆነው ታዩ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 8, 2018

የናቁሽ ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ!!!

የሳውዲ ልዑል መሀመድ ቢን ሳልማን ባለፈው ሰኞ ያልተጠበቀ ጉብኝት በግብጽ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አድርገው ነበር። ልዑሉ ከግብጹ ፓትርያርክ ከብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ታውድሮስ 2ኛ ጋር ሆነው ካይሮ ሚገኘው የቅዱስ ማርቆስ ኮፕቲክ ካቴድራል ውስጥ ተገኝተው ነበር።

ሊቀ ጳጳስ ታዋድሮስ እንደገለጹት ከሆነ ልዑል ቢን ሳልማን ለግብጻውያን ኮፕት ያላቸውን አድናቆት ገልጸው ነበር። በዚሁ አጋጣሚ ሁሉም ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቀሳውስት ሳዑዲ ዓረቢያን እንዲጎበኙ ጥሪ አቅርበውላቸዋል።

______

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

Jim Caviezel: ‘Passion of the Christ’ Sequel Will Be ‘Biggest Film in History’

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on February 1, 2018

Jim Caviezel, the actor who memorably portrayed Jesus in director Mel Gibson’s 2004 blockbuster The Passion of the Christ, says that Gibson is planning a sequel that will be “the biggest film in history. It’s that good.”

The Passion is already one the biggest films in history. Fourteen years on it still holds the domestic box office record for an R-rated movie ($371 million). From Gethsemane to Golgotha, The Passion told the story of the last 12 hours of Christ’s life — his arrest, trials, torture, and crucifixion. The Faithful turned out in droves despite an unprecedented campaign within the elite media to smear a film they had not seen as anti-Semitic — which it is not.

The 49-year-old Caviezel says he is back on board to portray Jesus. The story will reportedly revolve around Christ’s resurrection. “There are things that I cannot say that will shock the audience,” he told USA Today. “It’s great. Stay tuned.”

Hollywood’s anti-Christian bigotry was apparent in every major studios’ incomprehensible refusal to distribute The Passion, a film helmed by a huge star, a proven talent who had already won a Best Director Oscar for Braveheart. Gibson, however, got the last laugh.

Off a mere $30 million budget, Gibson still managed to get his film seen in enough theaters worldwide to gross a breathtaking $611 million.

The success of The Passion, which surprised no one who lives in the real world, immediately changed Hollywood. An industry that had been openly hostile to Christians almost immediately began producing and releasing faith-based films, a sea change that continues to this day.

Last year, Gibson talked a little bit about his plans, “The Resurrection. Big subject. Oh, my God,” he told USA Today. “We’re trying to craft this in a way that’s cinematically compelling and enlightening so that it shines new light, if possible, without creating some weird thing.”

Selected Comments:

Finally! A movie I can go see!!

Gibson is proof that God can use fallible humans for His purposes. Gibson is not perfect, but the message of Christ told through Gibson’s work, (namely, The Passion of The Christ) certainly is.

The Passion of the Christ saved a lot of Souls, and if this Movie sticks to the Truth of the Bible, many more Souls will be saved.

I’m not even a religious person, but I am very excited for this film. It’s bound to upset a lot of people. Plus, Passion was by far the best film ever made about Jesus’s last moments. If its anything like the first movie, it will be a massive success. PLEASE just make it accurate.

Then you can do one on the life of Paul since Hollywood seems desperate to suppress what he teaches. Something about that Grace message….

Jesus Christ =

1. God with us
2. The Light of the world
3. Son of David
4. The Lamb of God…
5. WHO TAKES AWAY THE SIN OF THE WORLD
6. SALVATION
7. DELIVERANCE
8. SON OF GOD
9. SECOND PERSON OF THE TRINITY
10. Lion of the Tribe of Judah

I refuse to go to the theaters but for this movie I will make an exception

Source

My Note: Intersting, some of the actors who’ve played in „The Passion of The Christ“ have identical initials as:

  • Jesus Christ = JC
  • Jim Caviezel: JC – The Passion of The Christ (2004)
  • Christo Jivkov: CJ – ‘JohnThe Passion of The Christ (2004)
  • Mother Mariam / Mary = MM
  • Maia Morgenstern = MM (also Mary Magdalene)
  • Monica Anna Maria Bellucci = MM (Played Mary Magdalene)

______

Posted in Ethiopia, Faith, Infotainment | Tagged: , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ቅዱሳንን ለምን ፈረንጆች አደረግናቸው?

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 24, 2013

 

በአሜሪካኑ ቴሌቪዥን፡ በ ታሪክ ጣቢያ” (History Channel) “The Bible” “መጽሐፍ ቅዱስየተሰኘ አንድ ባለ አሥር ሰዓት ፊልም እስከ መጪው የፈረንጆች ፋሲካ ድረስ እሁድ እሁድ በመታየት ላይ ነው። ይህ ፊልም፡ እንደ አሜሪካን አይድልየመሳሰሉትን ተወዳጅ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች በተመልካች ብዛት የቀጣ ከመሆኑም ሌላ፡ የመጸሐፍ ቅዱስን ባለ ታሪኮች ማን እንደተጫወተ/መጫወት እንደነበረበት በመርመር የሜዲያውን ዓለም ስሜታዊ በሆነ መልክ በማወያየት ላይ ይገኛል።

የብሉይ እና አዲስ ኪዳናትን ታሪኮችና መልዕክቶች ለማስተፋፈል ታስቦ የተሰረውን ይህን ፊልም መቅረጽ የጀመሩት ገና ፕሬዚደንት ኦባማ ለፕሬዚደንት ከመብቃታቸው በፊት ቢሆንም፡ ፊልሙ ላይ የ ሰይጣን ባለ ታሪክነቱን የሚጫወተው ከመካከለኛው ምስራቅ የመጣ ተዋናይ ከኦባማ ጋር ይመሳሰላል በማለት ብዙዎቹን እያነጋገረ ነው።

ነጭ ክርስቶስ፡ ጥቁር ሰይጣን

ObamSatአፍሪካዊአሜሪካኖች ፊልሙ ላይ ያሉትን መጥፎ መጥፎዎቹ ሰዎች ሲመለከቱ፡ ሁሉም እነርሱን የሚመሳሰሉ ገጽታ አሏቸው። ታዲያ አንዲት ህጻን ልጅ፡ ለምንድን ነው ሁልጊዜ ጥሩዎቹና ክርስቶስ ፈረንጆች የሚሆኑት? ሰይጣን ደግሞ ኦባማን የሚመስለው?” በማለት ታላቋን ጠየቀች። እሷም፡ ፈረንጆች ሁልጊዜ ፈረንጅ የሆነ ነገር ነው የሚሠሩት!” ብላ መለሰችላት።ይላል ክርስቲያን ሳይንስ ሞኒተር

እየሱስ ክርስቶስ ማን እንደነበር ከኢትዮጵያውያን የበለጠ የሚያውቅ ይኖራልን?

በሚከተለው የ ንቡረ እድ ኤርሚያስ ከበደ ጠቃሚ ትምሕርት ሙሉ በሙሉ እስማማለሁ፦

ለአብርሃም፥ ለይስሓቅና ያዕቆብ በገባላቸው ቃል ኪዳን ምክንያት፥ እንዲሁም ስለስሙ ሲል እግዚአብሔር ለእሥራኤል ሕዝብ በነፍስና በሥጋ፥ በመንፈስም የሰጣቸው የቃል ኪዳን ጸጋና በረከት ዘርና መንግሥት፡ ኹሉም ወደ ኢትዮጵያና ወደ ኢትዮጵያውያን ተመልሰው ለእነርሱ የኾነበት የመለኮት ዕፁብ ድንቅ ሥራ የተገለጠበት፥ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን በሚመለከት ቀደም ብሎ በአብርሃም (በኢትዮጵያውያኖቹ በ መልከ ጼዴቅ፥ በ አቤሚለክ እና በሁለተኛ ሚስቱ በኬቱራ በኩል) ቀጥሎም በሙሴ (የሙሴ ባለቤት ሲጶራ ኢትዮጲያዊት ነበረች፣ ሙሴም ለ40 ዓመታት ያህል ኢትዮጵያን በንጉሥነት አገልግሏል፡ የአብርሃምና ኬቱራ ዘር ኢትዮጵያዊው ዮቶር መምህሩ ነበር) ሰውነትና ሕይወት ላይ ደርሰው የታዩትንና እነርሱን የመሰሉትን፥ ያለፉትን ኹሉ በበለጠ አጠናክሮ የሚያጸና ሌላ አራተኛ ትንግርት ደግሞ አለ።

ያም የመለኮት ዕፁብ ድንቅ ሥራ የተገለጠው በታላላቁ ሊቃውንት፥ በታወቁት ከበርቴዎችና በገናናዎቹ ኃያላን ዘንድና ላይ አይደለም፥ በቤተ ብዕል በቤተ ክህነት እና/ወይም በቤተ መንግሥት አዳራሾችም ውስጥ አይደለም። ከብቶቹን በሜዳ አሰማርቶ ለሚጠብቅ ለአንድ ተራ ብላቴና እረኛ ነበር እንጂ። የዚያ እረኛም ስም፡ ዳዊትነበር።

ይህ ጻድቅና ነቢይ፡ ከኢትዮጵያዊውና አቤሚሌክየሚል ስም ካለው የትውልድ ሓረግ የተወለደ በመኾኑ ኢትዮጵያዊነቱ በዘሩ ብቻ ሳይኾን እውነተኛ ሃይማኖቱና ምግባሩ በታላላቅ የገድል ፈተናዎቹ ስለተረጋገጠለት እግዚአብሔር ለሉዓላዊው አገልግሎትና ክብር መርጦ ሾመው። አዎን! ከበግ እረኝነት ጠርቶ በእሥራኤልና በይሁዳ ሕዝብ ላይ፡ ንጉሥ አድርጎ ቀብቶ አነገሠው። ከእርሱም አብራክ ከወጣው ዘር በመጨረሻው ዘመን ኢየሱስ ክርስቶስ ተወልዶ ዓለሙን እንደሚያድን መንግሥቱንም ዘለዓለማዊ አድርጎ እንደሚያጸናለት ቃል ኪዳን ገባለት።

የእግዚአብሔር አገልጋይ የኾነው ይኽው ዳዊት ኢትዮጵያዊውን ታማኝ ወታደሩን፡ ኦርዮንን በግፍ በማስገደል የሠራውን እጅግ ከባድ ኃጢአት በእውነተኛ ንስሓ ካነጻ በኋላ የሟቹን ኢትዮጵያዊት ሚስቱን ቤትሳባን አግብቶ ሰሎሞንን ወለደ፤ ልጁ ሰሎሞንም ከኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ከማክዳ/ ከሣባ ቀዳማዊ ምኒልክን ወለደ።

ከዚህ የተነሣ የእሥራኤል የኾነው ሃይማኖታዊውና ምግባራዊው ሥርዓታዊውና ባህላዊው ውርስና ቅርስ ብቻ ሳይኾን እግዚአብሔር ለዳዊት የሰጠው ቃል ኪዳኑንና የቃል ኪዳኑ ዘር ጭምር ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን ኾኑ።

ዳዊትና የእግዚአብሔር መንግሥት ከእርሱ ከዳዊት ዘር ከተገኘችው ከድንግል ማርያም በተወለደው በኢየሱስ ክርስቶስ ንጉሥነትና በርሷ በቅድስት እናቱ ንግሥትነት ለዘለዓለም ጸንታ የምትኖርለት በመኾኑ ፈጣሪው ቃል ኪዳን ገባለት።” (‘ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት‘ 3ኛ መጽሐፍ)

ይህን የንቡረ እድ ኤርምያስ ጽሑፍ ከማንበቤ በፊት የክርስቶስ አመጣጥ ኢትዮጵያው ሊሆን እንደሚችል፡ ልክ እንደ ብዙዎች ኢትዮጵያውያን ፡ በውስጤ ይታወቀኝ ነበር። ታዲያ በጣም የሚገርመኝ፣ ግራ አጋብቶ የሚረብሸኝና የሚያበሳጨኝ አንድ ነገር ቢኖር፣ እኛ ኢትዮጵያውያን ይህን የመሰለ ኃብታም ታሪክ፣ ይህን ዓይነት ተወዳዳሪየለሽ ታላቅ ጸጋ ተሰጥቶን እንዴት ዋጋ በሌለውና ዓለማዊ በሆነው ቆሻሻ ሁሉ በቀላሉ ልንበላሽ ቻልን? የሚለው ጥያቄ ነው።

ኔልሰን ማንዴላ የሕይወት ታሪካቸውን በሚያበሥረው መጽሐፋቸው፤ የነጮቹን የአፓርታይድ ሥርዓት ለመዋጋት አንድ ጊዜ ለስብሰባ ወደ አዲስ አበባ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሲበሩ ኢትዮጵያውያን ፓይለቶችን ዓይተው፡ እንዴ! ጥቁር አውሮፕላን አብራሪዎችም አሉ እንዴ? እንዴት ሊሆን ቻለ?” የሚለውን ጥያቄ ከአድናቆት ጋር መጠየቃቸውን እናስታውሳለን።

እካሁን ድረስ ከነጮች የዘር አድሎ ሥርዓት መላቀቅ የተሳናቸው አፍሪቃዊአሜሪካውያን፡ እዚህ እናንብብ፡ ኢትዮጵያን የመጎብኘት አጋጣሚ ሲያገኙ፡ በቅድሚያ የሚደነቁበት/ የሚገረሙበት አንድ ትልቅ ነገር ቢኖር፡ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን፣ የእመቤታችንን የቅድስት ማርያምን እንዲሁም የቅዱሳንን እና የመላእክትን በኢትዮጵያዊና በጥቁር መልክ ተመስለው በየዓብያተክርስቲያናቱ ለማየት መብቃታቸውን ነው። ጥቁር እየሱስ ለመጀመሪያ ጊዜ ያየሁት ኢትዮጵያ ውስጥ ነው!” በማለት አንድ ታዋቂ አፍሪቃዊአሜሪካዊ ምሁር በኩራት ሲናገሩ አንድጊዜ ሰምቼ ነበር።

ታዲያ አሁን ሁላችንም፡ በተለይ በዚህ የጾም ጊዜ አጥብቀን ልናስብበትና ልንጠየቀው የሚገባን ጥያቄ፦

ለምንድን ነው በአገራችን፡ ብሎንድ/ወርቃማ ጸጉርና ሰማያዊ ዓይኖች ያሏቸው ወይም ፈረንጆችን የመሳስሉ የ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የቅድስት ማርያምና የቅዱሳን ምስሎች በየቦታው ተሠራጭተው የሚታዩት? የቅዱስ ላሊበላ ዓብያተ ክርስቲያናት እንኳን አልተረፉም!

ፈረንጆቹ እራሳቸውን የመሰለውን የኢየሱስ ክርስቶስ ስዕል ቢስሉ ምንም አይደለም፤ እኛ ግን እንዴት? ለምን? ከፈረንጆቹ አስቀድመን ክርስትናን የተቀበለን ሕዝቦች አይደለንምን? ኢየሱስ ክርስቶስ እና ቅድስት ማርያም ኢትዮጵያዊ አመጣጥ እንዳላቸው እናውቃለን፡ አባቶቻችንም በስዕሎቻቸው ሁሉ የኢትዮጵያውያኑን ገጽታ እንዲይዙ አድርገው ነበር ሲስሏቸው የነበሩት፡ ታዲያ አሁን እኛ ቅዱሳኑን ምን ነክቶን ነው ፈረንጆች ልናደርጋቸው የበቃነው?

ዲያብሎስ አታልሎ ወደ ወገኖቹ ካልወሰደን በቀር፡ ምንም ሳይቸግረን፣ ምንም ሳይጎድለን እንዴት ከፈረንጆቹ የማይጠቅመውን ነገር ብቻ መርጠን በመቀበል መጪውን ትውልድ፡ ለአእምሮ ከንቱነት እና ለመንፈሣዊ ባርነት ልናጋልጥ ፈቀድን? ይህ በጣም የሚከነክንና የሚያስቆጣ ድርጊት ነው። ከአባቶቻችን የተረከብነውን ውድ ፀጋ፡ የነርሱን አደራ መንከባከብ ከባድ ሆኖ ስለምናገኘው፡ ታሪክ ዋጋ እንደሌለው፣ የአባቶችንን ሥራ ማውሳቱ ፍሬቢስነት እንደሆነ አድርገን እራሳችንን በማሳማን ቀላል የሆነውን የክህደት መንገድ መርጠን ለባዕዳውያኑ አላፊ ሥልጣኔበስንፍናችን እንጋለጣለን። በብልጭልጩ ዓይናችን ታውሯልና። ለአባቶቻችን ከአምላክ የተሰጠውን ሥርዓት መናቅ፥ ከእግዚአብሔር የተገኘውን የአባቶቹን ሃይማኖት መተው፥ ትውልዱ፡ አባቶቼ ያቆዩልኝ ትክክል አይደለም፡ የፈረንጁ ትክክል ነው በማለት ነገሮችን ሳይመረመር የማያውቀው ወጥመድ ውስጥ ይገባል። ክርስቶስን በ ጣዖት ፥ ተዋሕዶን በተሃድሶ ፥ ቤተ መቅደስን በቢራ ቤት ፥ መስቀልን በ ፎቅ ፥ ጠበልን በመርዝ ፥ ጥቁርን በ ነጭ ፥ መከዳን በ ሞኒካ ፥ ግዕዝን በላቲን ፥ ነጠላን በ ከረባት ፥ እንጀራን በ ሃምበርገር ፥ እርጎውን በ ኮካኮላ፥ ንጹሑን አየር በመኪና ጭስ በመተካት ምን የሚጠቅመንና የተሻለ ነገር ያገኘን እየመሰለን ይሆን? ለመደንቆር ፥ ልፍስፍስ ለመሆን፥ ለመታመም እና እራቁት ለመቅረት ካልሆነ በቀር!

ግድየለሽነታችን፡ ከኔ ጀመሮ፡ እጅግ በጣም የሚገርም ክስተት ነው። ሌላው ቢቀር፡ ሥጋዊነት ወይም አካላዊነት የሌላቸው መላእክት እንኳን በነጮች ምስል እኮ ነው እየቀረቡልን ያሉት። ውጭ አገር የሚኖሩትና ብዙ ነገሮችን በቅርብ ለመታዘብ ዕድሉ ያላቸው አባቶች ሳይቀሩ ነው ኢትዮጵያዊውን ክርስቶስ በመተው የፈረንጆቹን ክርስቶስ ደረታቸው ላይ አንጠልጥለው የሚታዩት። ይህ መቸም በመጥፎ ታስቦ ሳይሆን ሌላውን በማክበርና በመውደድ ከመጣ በጎነት የመነጨ ነው። ይህ ተግባር ግን በዚህች በአሁኗ ዓለማችን ከፍተኛ ስህተት ነው ሊሆን የሚችለው። እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑየሚለውን ቅዱስ ቃል ቸል በማለት።

ይህ ጉዳይ በቀላሉ መወሰድ የለበትም! “ምን አለበት? ልዩነት የለውም!” እየተባለለት መታለፍ ያለበትም ጉዳይ አይደለም። ምስሎችና ምልክቶች እጅግ ከፍተኛ ሚና በሚጫወቱባት ዓለማችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምስል ፈረንጅ ወይም አይሁድ እና ኢትዮጵያዊ መምሰል ትልቅ ቦታ፡ ከፍተኛ ዋጋ ይኖረዋል። ምናልባትም ብዙ ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያዊውን ተዋሕዶ እምነታቸውን እየተው ወደ መጤው የፈረንጅ እምነት ከሚወድቁባቸው ምክኒያቶች አንዱ ይህ የአባቶቻችንን ትክክለኛ ኢትዮጵያዊ የሥዕል ጥበበ ባሕል እየተተወ እና እየተበላሸ በመምጣቱ ሊሆን ይችላል። ይህም እየተሠራ ያለው ጥፋት/ኃጢዓት፡ በአንድ በኩል፡ ወደ መንግስተ ሰማይ የሚወስደውን በር በወገኖቻችን ላይ እየዘጋባቸው መሆኑን፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሃቁን በመካድ፡ የሌለውን የክርስቶስን፣ የማርያምን እና የቅዱሳንን ማንነት ያለአግባብ ቀስበቀስ እየቀየርን መሆኑን ሊያሳየን ይችላል።

እግዚኦ መኻረነ ክርስቶስ!

የፕሮቴስታንት ሃይማኖት ፓስተር የነበሩት የጀርመን ፌደራል ሪፓብሊክ ርዕሰ ብሔር፡ ዮአኪም GermanPresLalibelaጋውክ፡ ባለፈው ማክሰኞ የላሊበላ ቆይታቸው፡ የእነ ቤተ ጊዮርጊስን ተዓምራት በቦታው ተገኝተው ከታዘቡ በኋል የሚከተለውን በመመሰጥ ተናግረው ነበር፦

ኢትዮጵያውያኑ ጽኑ እምነታቸውን በቋጥኙ ቅርጽ ያንጸባርቁታል፡ እዚህ ተገኝቼ ይህን ድንቅ ሥራ በዓይኔ ለማየት ስበቃ የጉዞ ፊልሞች የሚያቀርቧቸው ምስሎች ስሜትን የመቀስቀስ ብቃት እንደሌላቸው አሁን ተገነዘብኩ፡ ላሊበላ በመምጣቴ፡ ይህች ቦታ በርግጥም የሰው ልጅ ዘር ምንጭ መሆኗን ለመገንዘብ በቅቻለሁ፡ ክርስቲያናዊ ስሜቴም ተቀስቅሷል፡ ተደንቄአለሁ።

አስደናቂ የሕይወት ታሪክ ያላቸው እኚህ ሰው፡ በኮሙኒስቷ ጀርመን (ቻንስለሯም ከዛው ናቸው) በፕሮቴስታንት ፓስተርነት የሃይማኖት ጠላት ከነበረው የምስራቅ ጀርመን መንግሥት ጋር እየተፋለሙ ነበር ሲኖሩ የነበሩት። አዲስ አበባ እንደገቡም የፕሮቴስታንቶችን የመቃብር ቦታ በቅድሚያ ለመጎብኘት መሻታቸው ከዚህ ታሪካቸው ጋር የተያያዘ በመሆኑ ሊሆን ይችላል። ጀርመኖች፡ ግማሹ ካቶሊክ ግማሹ ፕሮቴስታንት ናቸው። በማርቲን ሉተር የተጀመረው የፕሮቴስታንቶች ተሃድሷዊ እንቅስቃሴ መሠረቱ ጀርመን እንደመሆኑ፤ ይህ እንቅስቃሴ ክርስቲያናዊ ሕይወትን አስመልክቶ የትኛውን መንገድ እንደተከተለና ምን ዓይነት ውጤት እንዳመጣ ፕሬዚደንቱም፡ እውነተኛ የሆኑ ጀርመናውያንም ያውቁታል። እንቅስቃሴው ባጭር ጊዜ ውስጥ (500 ዓመት አይሞላም) ክርስቲያናዊ ሕይወትን/ክርስትናን ከሕብረተሰቡ ለማጥፋት በቅቷል፡ ሕዝቡን ከፍተኛ መንፈሳዊ ውድቀት ላይ ጥሎታል። ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ። ከእሾህ ወይን ከኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን?” ፕሬዚደንቱም በላሊበላዋ አጭር ቆይታቸው ይህን የተገነዘቡ መሰለኝ።

በብዙ አውሮፓውያን ሕዝቦች ዘንድ ጥቁር ማዶናወይም ጥቁር ማርያምተብላ የምትጠራዋ እመቤታችን ከፍተኛ አክብሮት እንዳላት ይታወቃል። ከፊሊፒንስ አገር እስከ ፖላንድና ሜክሲኮ ድረስ በመላው ምድራችን ብዛት ያላቸው የክርስትና እምነት ተከታዮች ጥቁሯ ማዶና የሚሏትን ኢትዮጵያዊቷን ጽዮን ማርያምን በጥልቁ ማክበር ልዩ መለያቸው ከሆነ ብዙ ዘመናት አሳልፏል።

11ኛው እስከ 13ኛው ምዕተዓመት ባለው ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ተጉዘው እንደነበር የሚነገርላቸው፡ ናይትስ ኦፍ ቴምፕላርስ፡ የጥቁሯ ማዶናን ምስጢር ከኢትዮጵያ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አግኝተው ወደ አውሮፓ፡ በተለይ ወደ ፈረንሳይ ይዘው በመሄድ ለአብዛኞቹ አውሮፓውያን እንዳስተዋወቋቸው የሚዘክር ታሪክ አለ። አንዴ ንግሥት ሣባ ሌላ ጊዜ ደግሞ ማርያ ማግዴላ ነች ይሏታል። የተዋሕዶ ክርስትና ተከታዮች፡ እመቤታችን ማርያምን የ ብርሃን እናትብለው ስለሚጠሯት እንዲሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በ ብርሃንናፀሐይ ስለሚመሰል፡ ቴምፕላሮቹም ይህን የጽኑ እምነት መግለጫ ከኢትዮጵያ ወስደው በጨለማ ውስጥ ለነበሩት አውሮፓውያን አድርሰው ይሆናል የሚል ሃሳብ አለ። መቼም እውነትንደባቂዎቹ አውሮፓውያን ባለ ታሪኮች ለሁሉም ነገር የቴምፕላሮችን ስም እያነሱ ያልተፈጸመውን ሁሉ ተጽፍሞ ይሆናል በማለት ታሪክን ማበላሸት ይቀናቸዋልና፡ መንፈሳዊ ተሰጥኦ ያላቸው አውሮፓውያን በራዕይ ኢትዮጵያዊቷ ጽዮን ማርያምን ለማየት አልተቻላቸውም፡ ቴምፕላሮች ናቸው ምስሏን ከኢትዮጵያ ይዘውት የመጡት ብለው ይናገራሉ። የላሊበላን ዓብያተ ክርስቲያናት እነዚሁ ቴምፕላሮች ናቸው የሠሯቸው፡ ኢትዮጵያውያን ለዚህ ብቃት የላቸውም እስከ ማለት ደርሰው የለም። ከኛም መኻል ይህን ቅሌታማ የፈጠራ ወሬ የሚያስተጋቡ አሳፋሪዎች አልጠፉም።

QedistMaryamምስጢሩ ግን፡ ኢትዮጵያዊቷ እመቤታችን በመንፈስ ድኻ ለሆኑት የዓለማችን ነዋሪዎች በራዕይ እየተገለጠችላቸው ነው። ማንነቷንም ባለመደበቋ፡ ለአሕዛቡ ሁሉ ጠቆር ብላ ስለታየቻቸው ጥቁር ማዶና የሚል ስም ሰጥቷል። በፓላንድ እና በ ክሮኤሺያ የሚገኙት ጥቁር ማዶናዎች ንግሥት ማከዳን / ሣባን እንደሚያስታውሷቸው፡ በርሷም በኩል በየአገሩ ተዓምራተ ማርያምን በየጊዜው በማየታቸውና እመቤታችንንም በማክበር ህይወታቸውን በጥሩ መልክ ለመለወጥ እንደበቁ ብዙ መረጃዎች ይመሰክራሉ። አብዛኛው ዓለም ግን ይህን ምስጢር ላለማውጣት እስካሁን ድረስ አፍኖ ይዞታል። ኢትዮጵያዊ ዝርያ አለባት የምትባለዋ (እንዳለባት በጣም እጠረጥራለሁ) የታላቋ ብሪታንያ ንግሥት ኤልሣቤጥ እንኳ፡ ትክክለኛው ማንነቷ እንዳይታወቅባት ያው አፍና እንድትኖር ተገድዳለች። አንጋፋዎቹ ሩሲያዊው አሌክሳንደር ፑሽኪን፣ እንግሊዛዊው ሰር ፒተር ኡስቲኖቭ በኢትዮጵያዊው አመጣጣቸው ይኮሩ ነበር።

በፖላንዷ ቼስቶኾቫ(Częstochowa) የምትገኘው ጥቁሯ ማዶና በአገሬው ሕዝብ ዘንድ ከማንም በላይ ከፍተኛ አክብሮት ያላት፣ በብዙ መቶ ሺህ የሚቆጠሩ ጎብኝዎችን በየሣምንቱ የምትስብ፣ ለናዚዝምና ኮሙኒዝም ውድቀት ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረከተች፣ የፖላንድ ጥብቅ የካቶሊክ እምነት መሠረት የሆነች፡ እንዲሁም የሮማውን ጳጳስ፡ ዮሐንስጳዎሎስ ሁለተኛውን፡ ካርዲናል ቮይቲላን ያፈለቀች ድንቅ ቦታ ነች። በ ቼስቶኾቫ የሚገኘው የእመቤታችን ምስል በሐዋርያው ቅዱስ ሉቃስ የተሳለ እንደሆነ ይነገርለታል።

ይህ ሁሉ ምንን ያሳየናል? አዎ! የንግሥታችን ሣባ ዘር የሆነችው እመቤታችን ቅድስት ማርያም ብርሃኗን ከአገራችን ከኢትዮጵያ እያፈነጠቀች መንፈሣዊ ጨለማ ወደሰፈነባቸው ሩቅ አገራት፡ ቦታና ጊዜ ሳይወስናት ለዘመናት ተዓምር በመሥራት ላይ እንደምትገኝ ነው። መዳን የሚፈልጉትም የርሷን ብዙ ተዓምራት እያዩ በጌታችንና መድኃኒታችን ዓማካይነት ለመዳን መብቃታቸውን ነው። እመቤታችንን ከድተው የነበሩት በዙ ፕሮቴስታንቶች እንኳ ቀስ በቀስ ወደርሷ በመመለስ ላይ ይገኛሉ። የወደቁት ወገኖቻችንም ይህ እድል ይድረሳቸው።

ይህ አሜሪካን አገር በመታየት ላይ ያለው የመጽሐፍ ቅዱስ ፊልም ብዙ ተመልካቾችን ሊስብ መብቃቱ የሚያሳየን፡ የምዕራቡ ዓለም ሰው ወደ መንፈሳዊነት፡ ወደ ክርስትና ሕይወት ለመመለስ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለው ነው። አሁን የምንገኝበት ዘመን በክርስቶስ ላይ፡ በክርስትና ላይ ኃይለኛ ዘመቻ የሚካሄድበት ዘመን እንደመሆኑ፡ የደከመውንና የተበላሸውን ዓለም እንደገና ለማደስ ከማንኛውም ሃይማኖት ይልቅ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ተቀዳሚ ሚና የመጫወት እድል አላት። ክርስቶስ በድንጋይ ላይ ሠርቶ ያቆያት ቤት ናትና። የእመቤታችንን ተዓምራት፣ የርሷን አማላጅነት ለማየት፡ የኢትዮጵያ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ተንከባክባ ያቆየቻቸውን ምስጢራት እና ሥርዓት ለመካፈል በጣም የጓጉ ሕዝቦች አሉ። ለተጨማሪ መረጃ እዚህእዚህ እና እዚህ እንመልከት።

ኃይሉም ይበረታል፥ ነገር ግን በራሱ ኃይል አይደለም፤ በድንቅም ያጠፋል፥ ያደርግማል፥ ይከናወንማል፤ ኃያላንንና የቅዱሳንን ሕዝብ ያጠፋል። በመታለሉ ተንኰልን በእጁ ያከናውናል፤ በልቡም ይታበያል፥ ታምነውም የሚኖሩትን ብዙዎችን ያጠፋል፤ በአለቆቹም አለቃ ላይ ይቋቋማል፤ ያለ እጅም ይሰበራል። የተነገረውም የማታውና የጥዋቱ ራእይ እውነተኛ ነው፤ ነገር ግን ከብዙ ዘመን በኋላ ስለሚሆን ራእዩን ዝጋ።” [ትንቢተ ዳንኤል ምዕራፍ 824-26]

__

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: