Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘እንክብል’

አዲስ አበባ | ወገኔ፡ አሳሳቢና አስደንጋጭ የሆነ ውፍረት በእህቶቻችን ላይ እየታየ ነው!!!

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 23, 2017

በየአብያተክርስቲያናቱ አባቶች፦“ሴቶቻችን ውስጥ የገባው ጋኔን ይውጣልን!”

እያሉ ጸሎት ማድረስ ጀምረዋል።

ዛሬ፤ እንደገና፡ ቀኑን ሙሉ ሲያሳስበኝ የዋለ ጉዳይ ነው

ጌታዬ አምላኬ፣ ፈጣሪዬ ሆይ፡ ጠላቶችህ፡ በጥቁር አሜሪካውያን ላይ የተጠቀሙትን ዓይነት ዲያብሎሳዊ ትሪክ በየዋሆቹ እህቶቼ ላይ እየተጠቀሙ ነው፤ አባቴ ሆይ፡ አንተ ታያቸዋለህና ዝም አትበል

በጣም ብዙ የሆንት እህቶቻችን የወሊድ መከላከያውን እንደ ክረሜላ ነው የሚወስዱት፤ የሚያስጠነቅቃቸው፣ የሚመክራቸውና የሚያስተምራቸው አካል የለም፤ በጣም ነው የሚያሳዝነው።

ምግብንም በሚመለክት፤ እንደ ምሳሌ አድርጌ ቪዲዮ ውስጥ “በርገር” ቤቱን አቅርቤዋለሁ፦

ቦሌ መድኃኔ ዓለም ፊት ለፊት፤ መድኃኔ ዓለም እየተባለ የሚጠራው ህንፃ ሥር፡ በእንግሊዝኛው ይጠራል፡ “InN Out Burgerየሚባል ትልቅና “ዘመናዊ/ፈረንጃዊ” የፈጣን ምግብ ቤት አለ። ዶሮና ድንች ጥብስ፣ በርገሮችና የመሳሰሉትን የፈረንጅ ምግቦች ነው የሚያቀርቡት። ባጠቃላይ፡ ቦሌና ሃያሁለት በመሳሰሉት አካባቢዎች ጣፋጩንና ጤነኛውን ኢትዮጵያኛ የእንጀራ ምግብ ማግኘት በጣም ከባድ ነው። የሚገኝ ከሆነ እንኳን ምግቡ ሁሉ በአደገኛው ዘንባባ ዘይት የተሠራ ነው።

አንን ቀን አመሻሽ ላይ፡ እስኪ ልቅመሰው ብዬ በረንዳው ላይ ቁጭ አልኩ፤ የተቆራረጡ ዶሮዎችና (ሁሉ ነገር በእንግሊዝኛ ነው„Chicken Nuggetsብለውታል)የድንች ጥብሶች አቀረቡልኝ። ለመግለጽ ያዳግተኛል፤ አንዷን ቁራጭ ዶሮና ድንቹን እንደቀመስኩ በጣም አጥወለወልኝ፣ አፈር አፈር ይላል ብል አፈርን መስደብ ይሆንብኝል፤ አፈር የተሻለ ይጣፍጣል፡ የበለጠም ጥቅም ይኖረዋል፤ ይህ ግን ዶሮውም ድንቹም፡ ከፈርንጅ አገሩ እንኳን ሲነጻጸር በጣም የተለየ ነው።

አሳላፊውን ጠርቼ ይቅርታ ስለምቸኩል አልጨረስኩትም ብዬ ሂሳቤን ከከፈልኩ በኋላ ወርጄ ሄድኩ። ምነው ብለው ደነገጡ። ትንሽም ሄደት እንዳልኩ፤ አንዲት ወጣት እህታችን መንገድ ዳር ቁጭ ብላና ጨቅላዋን አቅፋ ትለምናለች…..ኩምሽሽ ብዬ አብሪያት ቁጭ አልኩእዚያ ሬስቶራንት ለዚያ ምግብ 95 ብር ነበር የከፈልኩትሬስቶራንቱ ውስጥ እስከ መቶ የሚጠጉ ወጣቶች እየተጯጯሁ ይመገባሉ፤ በብዙ ብር የሚገመት ምግብ ያዛሉበሽተኞች የሚያደርጋቸውን/ የሚያደርገንን ምግብ ይወስዳሉ/ እንወስዳለንእዚህ ደግሞ እህታችን፡ ልክ እንደ ማርያም ልጇን አቅፋ፡ ትለምናለች….. ያው እስካሁን ልረሳው የማልችለው ገጠመኝ ነው፣ ልክ እንደ ኃይለኛ ነገር ሆኖ ነው የሚትየኝ።

እዚያ ምግብ ቤት እንዲሁ ለመታዘብ አልፎ አልፎ አለፍ እያልኩ ወደ ውስጥ አይ ነበር። ሁሌ ሙሉ ነበር። አንድ ሌላ የታዘብኩት ነገር ቢኖር፦ ባካባቢው የሚገኙት ብዙ ፈረንጆች ወደ እዚህ ቤት ገብተው ሲመገቡ አለማየቴ ነው። እለምን ይሆን? የሚያውቁት ነገር ይኖር ይሆን? ለነገሩማ ለእነርሱ የት፣ ምን መብላት እንዳለባቸው ብዙ ጊዜ አስቀድሞ ባገራቸው/በኢንባሲዎቻቸው በኩል ይነገራቸው የለ!?

ዔዶማውያኑ እና እስማኤላውያኑ የሳጥናኤል ልጆች በተገኘው ቀዳዳ ሁሉ ነው እየገቡብን ያሉት፣ ዓይናችን እያየ ጆሮአችን እየሰማ ዲያብሎሳዊ ድርጊታቸውን በፈርኦናዊ ትዕቢትና ድፍረት በመፈጸም ላይ ናቸው። በተለይ አሁን ትኩረቱን ያደረጉት የሕብረተሰባችን ምሶሶዎች በሆኑት ሴቶቻችን እና ህፃናቶቻን ላይ ነው፤ በቅርቡ ደግሞ የወንዱን ዘር ለማድከም የተለያዮ ኬሚካሎችን፣ ጀርሞችንና ባክቴሪያዎችን እያዘጋጁልን ነው። ይህን እያንዳንዳችን ያልቸልተኝነት ልናውቅና ልናሳውቅ ግዴታ አለብን።

ለእህቶቻችን ውፍረት፦

መንስዔ

ዲያብሎሳዊ ምግብና መጠጥ

ይህ ምግብ ፈረንጁ አገር “ጃንክ/ቆሻሻ” ምግብ ይባላል፤ የሚመገቡትም፤ ብዙ ያልተማሩና ድኾች የሚባሉት ናቸው።

በአዲስ አበባችን ደግሞ፣ ተምሯል፣ ያውቃል፣ ኃብታም ነው የሚባለው ነው በፈቃዱ ይህን ቆሻሻ የሚበላው።

+ የሚረጋ የዘንባባ(ፓልም)ዘይት(በውስጡ ፓልሚክ አሲድ የተባለ አደገኛ ኬሚካል የያዘ ነው)

+ ኦርጋኖፓስፌት በተባለ መርዝ የተቀቀለ የእርዳታ(አሜሪካ)ስንዴ

+ የፈረንጅ በርገር እና ጥብሳጥብስ

+ የ ”ፈረንጅ” ዶሮና እንቁላል

+ የ “ፈረንጅ” ወተትና እርጎ

+ ሚሪንዳና ኮካኮላ

+ የአረብ ዱቄቶች

+ የቱርክና ፓኪስታን ስኳር

+ ኤታኖል የተሽከራሪ ነዳጅ

መንስዔ ፪

ዲያብሎሳዊ የወሊድ መከላከያዎች

+ ውርጃ

+ እንክብሎች

+ ክትባቶች

+ ቅባቶች

መንስዔ ፫

ዲያብሎሳዊ የማሕበረሰብ ግኑኝነት መርዞች

+ በየጎረቤቱ ምግብና ውሃ ውስጥ የሚቀላቀሉ የአረብ ቅመሞች፣ ሽታዎች(መርዝ ጂሃድ)

+ በጎረቤት እንስሶች ላይ የሚካሄድ ጭካኔ፤ በተለይ በውሻ ላይ

+ በየትምህርት ቤቱ በህፃናት የምሳ እቃ ውስጥ በድብቅ የሚጨመሩ ጠብታዎች(መርዝ ጂሃድ)

+ የቱርክ የ”ፍቅር” ድራማዎች (የፍቅር ጂሃድ)

መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፹፫:

አቤቱ፥ እንደ አንተ ማን ነው? አቤቱ፥ ዝም አትበል፥ ቸልም አትበል።

እነሆ፥ ጠላቶችህ ጮኽዋልና፥ የሚጠሉህም ራሳቸውን አንሥተዋልና።

ሕዝብህን በምክር ሸነገሉአቸው፥ በቅዱሳንህም ላይ ተማከሩ።

ኑ ከሕዝብ እናጥፋቸው፥ ደግሞም የእስራኤል ስም አይታሰብ አሉ።

አንድ ሆነው በአንተ ላይ ተማከሩ፤ በአንተ ላይ ቃል ኪዳን አደረጉ፤

የኤዶማውያን ድንኳኖች እስማኤላውያንም፥ ሞዓብም አጋራውያንም፥

ጌባል አሞንም አማሌቅም፥ ፍልስጥኤማውያንም ከጢሮስ ሰዎች ጋር፤

አሦርም ከእነርሱ ጋር ተባበረ፥ ለሎጥ ልጆችም ረዳት ሆኑአቸው።

______

Posted in Conspiracies, Faith, Health, Infos | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: