Posts Tagged ‘እርግማን’
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 29, 2020
👉 “ፓቻማማ + አቴቴ + ሺቫ“
ይህ የጣልያን አሳዛኝ ሁኔታ የሚያስተምረን ነገር ቢኖር ከተመሳሳይ መቅሰፍት ለመዳን መስቀል አደባባይ ላይ የተተከሉትን የኢሬቻ ዛፎች ዛሬውኑ ቁረጡ። አዲስ አበባ፣ ደብረዘይት፣ ናዝሬት መላዋ ኢትዮጵያ ከዋቄዮ አላህ፣ ከኢሬቻ ቃልቻ ቆሽሻ መንፈስ በፍጥነት መጽዳት እንዳለባቸውና መመለክና መፈራት ያለበት ብቸኛ አምላክ እግዚአብሔር አምላክ መሆኑን ነው። በመሰቀል–ደመራ ወቅት በመስቀል አደባባይ ሲፈረግጥ የነበረው በሬ እኮ እንደ አንድ ምልክት ሊሆነን በተገባ ነበር።
ዋቄዮ–አላህ የፈጠራቸው ሴት አማልክት በአፍሪቃ /በኦሮሞዎቹ “አቴቴ፣ በደቡብ አሜሪካ አማዞናስ ዙሪያ “ፓቻማማ” በህንድ “ሺቫ ከእነ ሦስት ልጆቿ/ቹ፤ ሳትቫ፣ ራጃስ፣ ታማስ“። ሁሉም የአል–ላት፣ አል–ኡዛ እና አል–ማናት አቻዎች መሆናቸው ነው።
የጨረቃው አምላክ አላህ–ከፀሐይዋ አምላክ ጋር ተጋብቶ ያስገኛቸው ልጆች በአንድነትም “የአላህ (ሴት) ልጆች” የተባሉ ሦስት አማልክት ስምም፦
👉 አል–ላት፤
👉 አል–ኡዛ
👉 አል–መናት
ነበር፡፡
👉 እ.አ.አ ጥቅምት 4 ቀን 2019 ዓ.ም. – ጣዖት አምልኮ ሥነ–ስርዓት በቫቲካን
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስኮ እና ሌሎች ቀሳውስት በቫቲካን የአትክልት ስፍራዎች ላይ ያካሄዱት የዛፍ ተከላ ሥነ–ስርዓት።
***በዓላቱ – መስከረም/ጥቅምት ላይ ተከታትለው ይውላሉ***
(ኢሬቻ + ሺቫ(ሙሩጋን) + ዱርጋ (ሴት የዛፍ አምላክ) + ፓቻማማ + ሃሎዊን)
በአምልኮ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ከአማዞን የመጡ ሰዎች ሁለት ከእንጨት የተሠሩ የእርጉዝ ሴቶች ሐውልቶችን(ፓቻማማ)ጳጳሱ ፊት ተንበርክከው ሲያመልኩ ይታያሉ።
በዛፍ ተከላ ሥነ ስርዓት ላይ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ የጣዖቷን ፓቻማም ሐውልት ባረኳት
👉 ካርዲናል በርክ ጳጳስ ፍራንሲስኮን ወቀሱ፦
ታዋቂው የአሜሪካ ካርዲናልና የቫቲካን ከፍተኛ ዳኛ ሬይመንድ በርክ፦ “የደቡብ አሜሪካው የአማዞን ሲኖድ ያመጣት ጣዖት “ፓቻማማ“፣ እና የዛፍ ተከላ ሥነ–ስርዓቱ አጋንንታዊ ኃይልን በቫቲካን አስገብተውብናል፤ ከፓቻማማ ጋር ሰይጣን ቤተ ክርስቲያን ገባ፤ ብቸኛዋ ወላዲተ አማልክ ድንግል ማርያም ናት። ከዚህች ጣዖት ጋር የመጣው የሰይጣን መንፈስ ከቫቲካን ይወገድ ዘንድ በክርስቶስ ስም መጸለይ ያስፈልጋል፤ የቅዱስ ጴጥሮስ ባሲሊካ ከእነዚህ የክፋት ኃይሎች መጽዳት አለበት።” ሲሉ ብሶታቸውን ገና ኮሮና ከመታወቋ በፊት አሰሙ።
👉 የእስልምና ጣዖት አምልኮ በቫቲካን
ሮማን ካቶሊኮች እ.አ.አ በ1960ዎቹ በ ሁለተኛው የቫቲካን ጉባኤ ላይ ለአንድ ዓለም ሃይማኖት ምስረታ መሰረቱን ከጣሉበት ዕለት አንስቶ በተቻላቸው መጠን “ክርእስላም”/ “Chrislam” የተሰኘ የእነርሱን ክርስትና እና እስልምናን ያጣመረ አዲስ ሉሲፈራዊ ሃይማኖት ለመመስረት እየታገሉ ነው።
👉 ይህ በቫቲካን ታይቶ አይታወቅም፦
አንድ የቱርክ ኢማም ንግግር አድርግ ተብሎ ሲጋበዝ፤ ክርስቲያኖችን እና አይሁዶችን የሚረግመውንና “አል–ፋቲሃ” የተሰኘውን የእስልምና “ፀሎት” ክፍል “ እንደ እባብ እየነዘረ ለቀቀው።
👉 ሁለተኛው የፊሊፒንስ ካቶሊክ ቄስ፦
ጣዖታቱ “ፓቻማማ” + “አቴቴ” + “ዮጋ” + “ሃሪ ፖተር” + “አላህ” ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በመግባታቸው ሰይጣን ዛሬ ብዙ ክርስቲያኖችን በአጋንንቱ ሊበክላቸውና ሊለክፋቸው በቅቷል።
“እግዚአብሔር አምላክህ እኔ ነኝ ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክት አይሁኑልህ፡፡[ዘጸ ፳፥፪፡፫፟]
የሚለውን ትዕዛዝ በመሻራችን ነው “ኮሮና” የመጣችብን።
ቸሩ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ከዋቄዮ–አላህ መንፈስ እና ከታዘዘው መቅሰፍት ሁሉ ይጠብቅልን! ለዘለዓለሙ አሜን!
👉 ገነ ማስተዋሌ ነው፦
ቪዲዮው ልክ የ22፡00 ደቂቃዎች እርዝመት አለው። ፳፪ / 22 ማክሰኞ ይውላል– ኡራኤል
በዚህ ዕለት ምን ይከሰት ይሆን?
___________________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith, Health, Infos | Tagged: ሂንዱ, መቅሰፍት, ሦስት የጣዖት አማልክት, ቫቲካን, ተላላፊ በሽታዎች, ቸነፈር ወረርሽኝ, አማዞናስ, አቴቴ, ኢትዮጵያ, እርግማን, እስላም, ኦሮሞ, ካቶሊክ, ኮሮናቫይረስ, ዋቄዮ አላህ, የቀሳውስት ሞት, የጨረቃ አምላክ, ደቡብ አሜሪካ, ጣልያን, ጳጳስ ፍራንሲስኮ, ፀረ-ኢትዮጵያ ሤራ, ፀረ-ክርስቶስ መንፈስ, ፓቻማማ, Ethiopia, Italy | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 27, 2020
“በብርቱም ድምፅ። ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች፥ ወደቀች፥ የአጋንንትም ማደሪያ ሆነች፥ የርኵሳንም መናፍስት ሁሉ መጠጊያ የርኵሳንና የተጠሉም ወፎች ሁሉ መጠጊያ ሆነች፤” [ራእይ ፲፰፥፪]
“አላሃችን እስላም ያልሆነውን ሁሉ አጥፍቶ እኛ ብቻ በሰላም፣ በጤና እና ብልጽግና እንኖራለን፣ ኩፋሮች ላይ መቅሰፍት ሲደርስና ሲያልቁ እኛ ግን በአላህ መላዕክት የሚጠበቀውን ካባን እየዞርን ጮቤ እንረግጣለን።” ይሉናል ተከታዮቻቸውን ጥላቻ፣ እብሪትና ጥፋት ብቻ የሚያስተምሩት እነዚህ የእስልምና ሊቆች፣ ሸሆች፣ ኢማሞች፣ ኡስታዞችና ጠበቃዎቻቸው።
ሃቁ ግን ሌላ ምስል ይዞ መጥቷል። እኛ ክፉውን አንመኝላቸውም፣ ሆኖም እኛ ለሺህ ዓመታት ያህል “ይሁን” እይልን ታግሰናቸዋል፤ አሁን እነርሱን ለማይመስለው የሰው ልጅ በጎውንና መልካሙን ለማይመኙት ለእነዚህ የዲያብሎስ ልጆች የእኛ አምላክ እግዚአብሔር ተገቢውን መልስ ይሰጣቸዋል።
ይህን አስመልክቶ ቪዲይው ላይ እንደሚሰማው እህተ ማርያም እና ዝነኛው አረብ ክርስቲያን፡ “ክርስቲያን ልዑል” ተገቢውን ድንቅ መልስ ሰጥተዋቸዋል።
የሚከተለው ከአራት ዓመታት በፊት ያቀረብኩት ቪዲዮና ጽሑፍ ነበር፦
ባለፈው ኅዳር ፳፯ ፪ሺ፰፡ ዲሴምበር 7 2015 ፎቶው/ቪዲዮው ላይ እንደሚታየው፡ የተገመሰችዋ ጨረቃ ከነ ኮከቧ ሰማይ ላይ ተሰካክተው ይታዩ ነበር። ዋናው የእስላም ምልክት ይህ ነው። በዚሁ እለት ነበር ለአሜሪካ ፕሬዚደንትነት እጩ ሆነው የሚወዳደሩት ዶናልድ ትራምፕ ሙስሊሞች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ የማድረግ እቅድ እንዳላቸው የተናገሩት፤ በዚሁ ሳምንት ነበር፤ በአንዋር መስጊድ የቦንብ ጥቃት ተፈጸመ ተብሎ የተነገረው።
ቀደም ሲል ተመሳሳይ ድርጊት በቱርክ ተከስቶ ነበር፤ የቱርኩ ፕሬዚደንት እ.አ.አ በ ኦገስት 14 2015፡ በዓርብ ዕለት፡ አንድ ተራራ ላይ የተሠራ አዲስ መስጊድ በሚመርቅበት ወቅት ከ እነዚያ ጅግራ መሰል ወራሪ ወፎች የምትዛመድ አንዲት ወፍ በራሱ ላይ አርፋበት ብዙዎችን ስታስገርም ነበር። በምረቃው ጊዜ፡ ፀረ–ክርስቶሱ የባቢሎኗ ቱርክ ፕሬዚደንት እርግ እና ጅግራ ነበር በአንድ ላይ የለቀቀው፤ ነገር ግን እርግቧ ሸሽታ ስታመልጥሲሄዱ፤ ጅግራዋ ግን መጥታ እራሱ ላይ አረፈች፤ ድንቅ ነው፣ የሚገርም ነው!
መጽሐፍ ቅዱስ እርግቦችን በጥሩ መንፈስ ሲያያቸው ሌሎች ወፎችን ግን የእርግማን ምልክቶች እንደሆኑ አድርጎ ነው የሚያስተምረን። ለምሳሌ፦
የማርቆስ ወንጌል ወፎችን ክርኩስ መንፈስ ጋር ሲያገናኛቸው፡
“እነሆ፥ ዘሪ ሊዘራ ወጣ። ሲዘራም አንዳንዱ በመንገድ ዳር ወደቀና ወፎች መጥተው በሉት።” [ማርቆስ ፬:፬]
የሉቃስ ወንጌል ደግሞ ከዲያብሎስ ጋር፦
“ዘሪ ዘሩን ሊዘራ ወጣ። ሲዘራም አንዳንዱ በመንገድ ዳር ወደቀ ተረገጠም፥ የሰማይ ወፎችም በሉት።” [ሉቃስ ፰፥፭]
ራእይ ዮሐንስ ደግሞ የፍጻሜ ዘመኗ ባቢሎን የርኩስ መንፈስ እና የአጋንንት ማደሪያ እንደምትሆን በመጠቆም ያስተምሩናል፦
“በብርቱም ድምፅ። ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች፥ ወደቀች፥ የአጋንንትም ማደሪያ ሆነች፥ የርኵሳንም መናፍስት ሁሉ መጠጊያ የርኵሳንና የተጠሉም ወፎች ሁሉ መጠጊያ ሆነች፤” [ራእይ ፲፰፥፪]
ይህ ሁሉ ያለምክኒያት አይደልም፤ ካልታወርን፤ እግዚአብሔር ምልክቶቹን በየቦታው እያሳየን ነው። በጣም የሚገርም ነው፡ ተዓምር ነው! ግማሽ ጨረቃ፤ የወራሪ ወፎች ጫጫታ፤ በጥቁር ጨርቅ የተሸፋፈነችው ሙስሊም ሴት፥ የጮኽባት ውሻ፥ የዶናልድ ትራምፕ ጥቆማ፥ አንዋር መስጊድ… አሃ! የዲያብሎስ፣ የአጋንንት ማንነት/ምንነት ግልጥልጥ ብሎ እየታየን አይደለምን?
መቅሰፍቱን ያመጡት ሦስቱ የዋቄዮ–አላህ ሴት ልጆች ናቸው
___________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith, Health, Infos | Tagged: መቅሰፍት, መካ, መዲና, ሦስት የጣዖት አማልክት, ሳውዲ, ሸሆች, ቀማኛ ወፎች, አላህ, አጋንንት, ኢማሞች, ኢትዮጵያ, እርግማን, እስላም, ካባ, የጨረቃ አምላክ, ጋኔን, ፀረ-ክርስቶስ መንፈስ | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 25, 2020
የመሀመድ ሦስት የሴት አማልክት
ከእስልምና መምጣት በፊት ዐረቦች ብዙ ወንድና ሴት አማልክትን ያመልኩ ነበር፡፡ እያንዳንዱ ጎሳም የራሱ “አምላክ” ነበረው፡፡ በዛን ዘመን “አላህ” የሚታወቀው የጨረቃ አምላክ ተብሎ የነበረ ሲሆን፣ ሕዝቡን ከአላህ ጋር የሚያማልዱ ናቸው ተብለው ይታመኑ የነበሩ ሦስት ልጆች ነበሩት፡፡ እነዚህ የጨረቃው አምላክ አላህ–ከፀሐይዋ አምላክ ጋር ተጋብቶ ያስገኛቸው ልጆች በአንድነትም “የአላህ (ሴት) ልጆች” የተባሉ ሦስት አማልክት ስምም፦
👉 አል–ላት፤
👉 አል–ኡዛ
👉 አል–መናት
ነበር፡፡
እንግዲህ መኮረጅና መስራቅ ተግባሩ የሆነው ዲያብሎስ የእግዚአብሔር የሆነውን ሁሉ ለመዋጋት የማይፈጠረው ነገር የለምና፣ ምስጢረ ሥላሴንም በመኮረጅ የራሱ የሆኑ ሥላሴዎችን በየሃገሩ በመፍጠር ተቀባይነትን ለማግኘት ይሞክራል።
ዋቄዮ–አላህ የፈጠራቸው ሴት አማልክት በአፍሪቃ /በኦሮሞዎቹ “አቴቴ፣ በደቡብ አሜሪካ አማዞናስ ዙሪያ “ፓቻማማ” በህንድ “ሺቫ ከእነ ሦስት ልጆቿ/ቹ፤ ሳትቫ፣ ራጃስ፣ ታማስ“። ሁሉም የአል–ላት፣ አል–ኡዛ እና አል–ማናት አቻዎች መሆናቸው ነው። ኮፒ፣ ኮፒ፣ ኮፒ!
የመሀመዳውያኑ ቍርአን “ክርስቲያኖች በሦስት አማልክት ነው የሚያምኑት፤ እነሱም አብ፣ ኢሳ እና መርያም/ማርያም” በማለት ትልቅ ቅጥፈት ቀጥፏል። እርኩሱ መጽሐፉ ከዲያብሎስ ነውና ጣዖት አምላኪዎች ሁሉ በተመሳሳይ መልክ እየተንቀሳቀሱ ነፍሳትን የመግደል ዲያብሎሳዊ ተልዕኮ አላቸው። ኦሮሞዎች “አቴቴ” እና የደቡብ አሜሪካ ህንዶች “ፓቻማማ” “መርያም/ማርያም” ቦታ በማስያዝ፡ “ተመሳሳይ እምነት እኮ ነው ያለን” በማለት ለማወናበድ ይደፍራሉ ማለት ነው።
እግዚአብሔር አምላክ የዋቄዮ–አላህን መቅሰፍት ከሃገራችን ያርቅልን!
_________________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: ሂንዱ, ህንዶች, መቅሰፍት, ሦስት የጣዖት አማልክት, አል-ላት, አል-ማናት, አል-ኡዛ, አማዞናስ, አቴቴ, ኢትዮጵያ, እርግማን, እስላም, ኦሮሞ, ዋቄዮ አላህ, የጨረቃ አምላክ, ደቡብ አሜሪካ, ፀረ-ክርስቶስ መንፈስ, ፓቻማማ | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on July 23, 2019
ይህ በታሪካችን ተደርጎ አያውቅም!
ጀግናዋ እኅታችን ትክክል ነች። ከሦስት ሳምንታት በፊት ለመጀመሪያ ጊዜ ዶ/ር ወዳጄነህ የተባለውን ፓስተር በቪዲዮ አየሁት፤ ወዲያው ፊቱ ላይ የታየኝ መንፈስ ባራክ ሁሴን ኦባማ ላይ የሚታየውን አይነት የክርስቶስ ተቃዋሚ መንፈስ ነው። በዚህ ጉዳይ አንድ ቪዲዮ ለመስራትና የተዋሕዶ ልጆችን ለማስጠንቀቅም እያሰላሰልኩ ነበር፤ ግን ያው እኅታችን ቀደመችኝ… በጣም የሚገርም ነው።
ዶ/ር ወዳጄነህ በጎ ሰው ይመስላል፤ ነገር ግን የ ዶ/ር አብዮት ጠበቃ ይሆን ዘንድ ቀድም ብሎ የተዘጋጀ ሰው ነው የሚመስለኝ። እንዲያውም የዶ/ር አብዮትን “እርካብና መንበር“ የሚለውን መጽሐፍ የፃፈለት የስነ–ልቦና ተመራማሪው ዶ/ር ወዳጄነህ ሆኖ ነው የታየኝ። ጎብዞ ከደፈረ ያለፈውን የምንፍቅና ማንነት እርግፍ አድርጎ መተው አለበት። ቅድስት ማርያም ትርዳው!
____________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: መተት, መናፍቃን, መንግስት, መንፈሣዊ ውጊያ, ቀውስ, አህዛብ, አብይ አህመድ, አጋንንት, ኢትዮጵያ, ኢትዮጵያዊነት, እምነት, እርግማን, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ, ፀረ-ኢትዮጵያ ሤራ | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on July 9, 2019
የኢትዮጵያን ጠላቶች እንዲህ ገላልጦ የሚያሳየን ቸሩ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን!
ዓይኑን እንመለከት….
መቼስ፡ ሁሉም ነገር በደንብ የተቀነባበረ ስለሆነ የሚገርም ነገር የለም። ሰውዬው ለክርስቶስ ተቃዋሚዎቹ ሱዳን እና ግብጽ ጠበቃ ሲቆም አዳመጥን? አዎ! የጀግናውን ኢትዮጵያዊ ንጉሥ አፄ ዮሐንስን አንገት ለቆረጡት ሱዳን ድርቡሾች። ሌላው ደግሞ ሰውዬው ልክ ንግግሩን፡ ያለአግባብ የእግዚአብሔርን ስም በማንሳት፡ ሲያገባድድ ETV ወይም “የኢትዮጵያ” የተባለው ቴሌቪዥን ካሜራውን ወደ ሦስቱ የሃይማኖት መሪዎች አዞረው። ወንበር አያያዛቸው ላይ ስናተኩር፦ በስተቀኝ የተዋሕዶው ፥ በስተግራ የካቶሊኩ ፥ ሁለቱን ክርስቲያኖች ለያይቶ መሀል ላይ ቁጭ ያለው ሙስሊሙ ነው። ይህ ሆን ተብሎ የተደረገ ነው። አይ ሃገሬ!
ግድ የለም፤ ኢትዮጵያዊነትን የተቀበለ፣ ያከበረና ያፈቀረ ዜጋ ብቻ የሚኖሩባትን ኢትዮጵያ የሚረከበው መጭው ትውልድ ይህን ትውልድ እንደሚንቅና እንደሚፈርድ እርግጠኛ ነኝ፤ “እንዴት ኢትዮጵያን ይህን ያህል የሚጠላ እና በጋኔን የተሞላ ወሮበላ ሰው መሪ እንዲሆን ፈቀዳችሁ?” ብሎ መጭው ትውልድ እንደሚኮንነንም በፍጹም አልጠራጠርም።
_______________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Ethiopia, Faith, Photos & Videos | Tagged: መንግስት, መንፈሣዊ ውጊያ, ቀውስ, አምባገነን, አብይ አህመድ, ኢትዮጵያ, ኢትዮጵያዊነት, እምነት, እርግማን, ዛቻ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ, የኦሮሞ እንቅስቃሴ, ጂሃድ, ፀረ-ኢትዮጵያ ሤራ, ፓርላማ | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on July 6, 2019
የፀሎት አባቶች ከደብረዳሞ፣ ከደብረ ሊባኖስ፣ ከዋልድባ ወይም ከ ደብረ ቢዛን ሆነው መካና መዲናን ማናወጥ፡ ካሊፎርኒያን ማንቀጥቀጥ፣ ዶ/ር አህመድን ማቁነጥነጥ/ማስቀበጣጠር ይችላሉ። በዚህ መቶ በመቶ እርግጠኛ ነኝ።
ይህን ቪዲዮ ለአንድ ሞሮካዊ ሙስሊም የሥራ ባልደረባዬ ካሳየሁት በኋላ የሚከተለውን አጫወተኝ፦
“በተለምዶ መስጊድ ውስጥ ከተፈሳ፡ አየሩ ውስጥ ያሉትን ጂኒዎች ሊያሳውራቸው ብሎም ሊገድላቸው ይችላል” ተብሎ ይታመናል አለኝ። ዋው! አልኩና የተዋሕዶ አባቶች ይህን በሚመለከት ኃይለኛ መንፍሳዊ መልዕክት እንዳላቸው…ከእርግማን ጋር የተያያዝ ነገር እንዳለ በማስትወስ ጉዳዩን ለጊዜው ተውኩት…ይህን ጉዳይ አስመልክቶ የተሻለ ዕውቀት ያላችሁ ወገኖች፡ የሰማችሁት ነገር ካለ አንድ ሁለት ብትሉን ደስ ይለን ነበር። ይህ ጉዳይ በማንኛውም ማሕበረሰብ፣ በሁሉም ዓለም ባህል ለምን አሳፋሪ እንደሆነ ሳስበው ነገሩ ቀላል ነገር አይደለም ያስብለኛል።
ለማንኛውም፤ ኢትዮጵያን አትንኳት!
__________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: መሀመድ, መስጊድ, መካ, መዲና, ሙስሊሞች, ኢማም, እርግማን, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ገዳማት, ደብረ ዳሞ, ጋኔን, ፈስ, https://youtu.be/tzOunRkDFRk | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on July 2, 2019
ሰውየው ልክ ከመሀንዲስ ስመኘው ግድያ በኋላ ተደርጎ እንደነበረው አሁንም ስለ ጄነራሎቹ ግድያ ነገሮችን ለማረሳሳት ሲል ዲያብሎሳዊ ተግባሩን በድራማ መልክ ማቅረቡን ቀጥሏል። ከፊሉን ሕዝባችንን ማታለል ይችል ይሆናል፤ እግዚአብሔርን ግን ማታለል አይቻለውም፤ አምላካችን በቪዲዮ የቀረጸውን ሁሉ በቅርቡ እንደሚያሳየን አትጠራጠሩ።
የእግዚአብሔር አምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ
“የእግዚአብሔርን የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ፤ እግዚአብሔር ስሙን በከንቱ የሚጠራውን ከበደል አያነጻውምና።” ዘጸ. ፳፥፯።
* ይህ ሕግ የሚከለክለውና የሚያስተምረው በሆነው ባልሆነው የእግዚአብሔርን ስም ከመጥራት መታቀብን፣ በሐሰት መማልና መገዛትን ብቻ አይደለም። በቀልድ፣ በዋዛ ፈዛዛና በዘፈቀደ የእግዚአብሔርን ስም ማንሣት፣ ሐሰትን እውነት አስመስሎ ለማቅረብ፣ ሐሰትን የእውነት ሽፋን አድርጎ ስሙን በድፍረት መጥራት የማይገባ መሆኑን ይገልጻል።
የእግዚአብሔር ስሙ ቅዱስ፣ ታላቅና ድንቅ ነው
* የልዑል እግዚአብሔር ስም እንደማንኛውም ሰው ስም በልማድ የምንጠራው አይደለም። ስለሆነም በጸሎተ ዕጣን ጊዜ በመኃልየ መኃልይ “ዘይትህ መልካም መዐዛ አለው፤ ስምህ እንደሚፈስስ ዘይት ነው” እንደተባለ ባማረ ቃል ስሙን እንጠራዋለን። መኃ. ፩፥፲፫። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በጸሎቷ “ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ነገር አድርጓልና ስሙም ቅዱስ ነው” ብላለች። ሉቃ. ፩፥፵፱። አባቷ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊትም እንዲሁ “ስሙ የተቀደሰና የተፈራ ነው” በማለት የእግዚአብሔርን የስሙን ቅድስና ተናግሯል። መዝ. ፻፲፥፱። የእግዚአብሔር ስም ቅዱስ በመሆኑ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ ባስተማረው ጸሎት “ስምህ ይቀደስ” እንድንለው ነግሮናል። ማቴ. ፮፥፱።
ስለ ስመ እግዚአብሔር የእኛ ግዴታ
* ይህ ቅዱስ ስም የእግዚአብሔር ስም ነውና ልናከብረው በመፍራትና በመንቀጥቀጥም ልንጠራው ይገባል። ነቢዩ ሙሴ “አምላክህ እግዚአብሔር የተባለውን የተመሰገነውንና የተፈራውን ስም ባትፈራ” በማለት እንዳስጠነቀቀ /ዘዳ. ፳፰፥፶፰/ ስሙን የሚፈሩ የሚያከብሩትም የሚገባቸውን መንፈሳዊ ዋጋ ያገኛሉ፤ በራእይ “ለባሪያዎችህም ለነቢያትና ለቅዱሳን ስምህንም ለሚፈሩት ለታናናሾችና ለታላላቆችም ዋጋቸውን ትሰጥ ዘንድ” የሚል ተጽፏልና። ራእ. ፲፩፥፲፰።
* የእግዚአብሔር ስም የከበረና ቅዱስ ሲሆን በተራው ነገር ሁሉና በየአጋጣሚው ልንጠራው አይገባም፤ ምክንያቱም በሆነው ባልሆነው ስሙን በመጥራት ልማድ ወደማድረግ ደረጃ ደርሰን ክብሩንና ፍቅሩን እናጣለንና ነው። ከዚህ ይልቅ ልንጠራው የሚገባው በጸሎት ጊዜ ቸርነቱን ስንለምንና ስለተደረገልን ቸርነቱም ስናመሰግን፣ ስጦታውንም ተስፋ በማድረግ መሆን አለበት። ቅዱስ ዳዊት “በአንተም ስም እጆቼን አነሣለሁ፤ ነፍሴ በቅቤና በስብ እንደሚጠግቡ ትጠግባለች” “በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ” “ለልዑል እግዚአብሔር ስም እዘምራለሁ” በማለት በተደጋጋሚ የተናገራቸው ቃሎች የሚያስረዱት የእግዚአብሔርን ስም እንዴት ባለ ጊዜና በምን ሁኔታ ልንጠራው የሚገባ መሆኑን ነው። መዝ. ፷፪፥፬ – ፭፤ ፻፬፥፫፤ ፯፥፯።
__________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: ሃይማኖትና ፖለቲካ, አብይ አህመድ, ኢትዮጵያ, ኢትዮጵያዊነት, ኢየሱስ ክርስቶስ, እርግማን, ከሃዲ ትውልድ, ክርስትና, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት, የእግዚአብሔር ስም, ፓርላማ | Leave a Comment »