Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • March 2023
    M T W T F S S
     12345
    6789101112
    13141516171819
    20212223242526
    2728293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ኢትዮጵያ ጉብኝት’

ሸክ መሀመድ ለአሜሪካ ፕሬዚደንት ሴት ልጅ በቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አቀባበል አደረገ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 15, 2019

ምን? ማን? ለምን? የት? እንዴት?

ኢቫንካ ትራምፕ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን አደጋ ህይወታቸውን ላጡት የሀዘን መታሰቢያ ላይ ለመሳተፍ ነበር ወደ ቤተ ክርስቲያን ያመራችው። ይህ አሶሲየትድ ፕሬስ የዜና ወኪል ያቀረበው ቪዲዮ ነው፤ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች መሪ ሸክ መሀመድ አሚን እራሱን ሲያስተዋውቃት ይሰማልሙሉውን እስካላየን ድረስ አንፍረድምሆኖም፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ወይ የፈረንጅ ወይ የግራኝ አህመድ ተንኮል ሊኖርበት ይችላል። ቀደም ሲል በእስራኤል ፕሬዚደንት በ ቢንያም ኔተንያሁ ላይ በ ብሔራዊ ሙዚየም የሠሩትን ተንኮል እናስታውሳለን። እስልምና ተቃውሚውን ፕሬዚደንት ትራምፕን ለመተናኮል ይሆን? ምስል ሺህ ቃላት ይናገራል!

በሌላ በኩል፡ የፕሬዚደንት ትራምፕ ልጅ ትህትናዋ ደስ ይላል፤ ሴት ልጅ እንዲህ ነው የሚያምርባት – የካቶሊኩ ካርዲናልም ይታያሉ – ሆኖም ግን፡ የአንድ ዓለም ሃይማኖት የመፍጠሪያ አካሄድ እንዳይሆን መጠንቀቅ ይኖርባታል።

__________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , | Leave a Comment »

የኢቫንካ ትራምፕ ጉብኝት የሚያሳየን ባቢሎን አሜሪካ ከዝሙትዋ ቍጣ ወይን ጠጅ/ ቡና የተነሳ ትወድቃለች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 15, 2019

አሜሪካ በሁለቱ “በ” ዎች ሱስ ተጠምዳለች፤ ሰክራለች፦ ቡና እና ቤንዚን/ ነዳጅ ዘይት። የዮሐንስ ራዕይ “ወይን ጠጅ” የሚለን ቤንዚን/ የነዳጅ ዘይትና ቡና መሆናቸው ነው። እንዲያውም ቡና ነው በይበልጥ ደምና መቅኒ ውስጥ የሚገባው ኃይለኛ ዝሙት አስያዥ እና ነፍስ ገዳይ መጠጥ። ቀስ ብሎ የሚገባ

እኔ የፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ደጋፊ ነኝ፤ ቃለ የገባለትን ተግባራዊ ለማድረግ ስለሚፈጨረጨሩ፤ ሞኟ ልጁ ግን በተንኮለኛው ባሏ ግፊት የሉሲፈራውያን አምባሳደር ሆናለች፤ ታሳዝናለች፤ ግን በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ ላይ በእነ ጃዋር በኩል እየፈጸሙት ባሉት – በአሜሪካንህንዶች ላይ የተፈጸመው ዓይነት – ጭፍጨፋ ሳቢያ ባቢሎን አሜሪካ ትወድቃለች። አዎ! ባቢሎን አሜሪካ ከዘረኞች፣ ወራሪዎችና ጨፍጫፊዎች ጋር ብቻ ነው በመላው ዓለም ተመሳጥራ እየሠራች ያለችው።

የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ ፲፰

ከዚህ በኋላ ታላቅ ስልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፥ ከክብሩም የተነሣ ምድር በራች

በብርቱም ድምፅ። ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች፥ ወደቀች፥ የአጋንንትም ማደሪያ ሆነች፥ የርኵሳንም መናፍስት ሁሉ መጠጊያ የርኵሳንና የተጠሉም ወፎች ሁሉ መጠጊያ ሆነች

አሕዛብ ሁሉ ከዝሙትዋ ቍጣ ወይን ጠጅ የተነሳ ወድቀዋልና፥ የምድርም ነገሥታት ከእርስዋ ጋር ሴሰኑ የምድርም ነጋዴዎች ከቅምጥልነትዋ ኃይል የተነሳ ባለ ጠጋዎች ሆኑ ብሎ ጮኸ

_______________

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ኢቫንካ ትራምፕ የኢትዮጵያ ጉብኝቷን በቡና ስነ ሥርዓት / 666 መስዋዕት ጀመረች

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 14, 2019

ለአውሬው ፍየል መሆኑ ነው፤ ዋው! የቡናው ቤት ውስጥ ካልዲን እና ፍየሉን ለማስተዋወቅ ተሞክሯል። “ታሪኩ እንዲህ ይላል፦ አንድ ካልዲ የሚባል የፍየል እረኛ የሚጠብቃቸው ፍየሎች የሆነ ዛፍ ፍሬን በልተው ያልተገባ ባህርይ ማሳየት ጀመሩ”። የምል ጽሑፍ ግርግዳው ላይ ይነበባል።

አንዷ ፍየል ብቻ መስላኝ? ለማንኛውም በጉ ከፍየሎች የሚለይበት ዘመን ላይ ደርሰናልና ህዝበ ክርስቲያኑን አድነዝዞ ለእነ ዶ/ር አህመድ እንዲሰግድ ያደረገውን ቡናን አንጠጣ፤ ግድ የለም፤ ለፍየሎች እንተውላቸው።

ድርሳነ ጽዮን ማርያም” :- ተአምር 1 ላይ የተጻፈው በሙሉ ይህ ነው:-

ሰማያዊት የሆነች የእናታችን የጽዮን ተአምር ይህ ነው : ጸሎቷና በረከቷ ህዝበ ክርስቲያን ከምንሆን ከሁላችን ጋር ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን::

ህዝበ ክርስቲያን ሆይ ልንገራቹ ሁላችሁም ስሙ የተጻፈ መጽሃፍ ሁሉ እኛ ልንመክርበት ተጽፏል እንዳለ ጳውሎስ ሮሜ 13:4 :ከአዳም ልጆች ወገን ሴሩህ የሚባል ሰው ነበር ለሴሩህ ስሙ ብኑ የሚባል ልጅ ተወልዶ በህጻንነቱ ሞተበት በብኑ ስም በተቀረጸው ጣኦት መመለክ ተጀምሯል በመቃብሩም ላይ ሰይጣን የሚወዳት ከሱስ የተነሳ ጾምን የምታሽር የከፋች ዕጽ በቀለች ይህውም በስንዴ መካከል እንክርዳድ የዘራ ጠላት ዲያብሎስ ካለችበት አምጥቶ ዘራት ማቴ ፲፫: ፳፰::

በብኑ ስም ቡን ተብላለች ቡና ማለት ነው: ማክሰኞ ከተፈጠሩት ዕፅዋት መልካምና ክፉ አሉ መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ክፉም ዛፍ ክፉ ፍሬ ያፈራል እንዳለ ማቴ ፯:፲፪

እስማኤላውያን የሚያመልኳቸው የጣኦታቸው መስዋዕት ሆነች የተንባላት አለቃ የሚሆን እስከ መሃመድም ትደርሳለች ተንባላትም ያለ እርሷ ሌላ አይሰውም ተንባላት ማለት የመሃመድ ተከታዮች ናቸው: ጣኦት የሚያመልኩ ባለዛሮችም ይህችኑ ይሰዋሉ የቡና ሱስ ያዘን ብለው ጾምን የሚሽሩ በበዓል የሚወቅጡ ራሳችንን አመመን በማለት በውስጣቸው ላደረ ለሱስ ጋኔን የሚገብሩ ብዙዎች ናቸው ወደ ቅዳሴም እንዳይሄዱ በጥዋት እሷን እየጠጡ ይህችም ዕጽ ክፉ ሁና ሰውን ስታሳስት ትኖራለች::

ተአምር ፪፦

ሌላም የሚያስረዳና ልቡናን የሚያጸና ስሙ ልንገራችሁ የተንባላት መምህር የነበረ ስሙ መሀመድ የሚባል አንድ ሰው ከመካዱ የተነሳ ከአጋንንት ጋር ይውላል ከዕለታት አንድ ቀን ሲሰግድ በልጅነቱ ያመው የነበረው የራስ ምታት በሽታ ይነሳበታል በዚህ በሽታ እየተሰቃየ ሳለ ከዕለታት በአንዱ ቀን ዲያቢሎስ በተንኮሉ ያስተው ዘንድ ወደ እርሱ መጥቶ ወዳጄ መሀመድ ሆይ ምን ሆንክ ይለዋል የራስ ምታት በሽታ የሆነበት እርሱ ዲያቢሎስ ነው፡፡

መሀመድ መልሶ ከፍተኛ የራስ ምታት ነበረብኝ በዚህ ደዌ እጨነቃለው ይለዋል ዲያቢሎስም የራስ ምታት መድሀኒት ብነግርህ ታደርገዋለህን የልቦናዬን ፈቃድ ትፈጽመሀልን? ይለዋል መሀመድም ካዳንከኝ አዎ ያልከኝን ሁሉ አደርገዋለሁ ብሎ የመልስለታል፡፡

ከዚህ በኋላ ዲያቢሎስ

  • ዕጸ ጌት የተባለች ጫትን፣

  • ዕፀ ኩስራ የተባለችውን ቡናንና

  • ዕፀ ስጥራጢስ የተባለጭውን ጥንባሆን

እነዚህን ሶስቱን ዕፅዋት ከአሉበት አምጥቶ መድሀኒት ናቸው ብሎ ይሰጠዋል፡፡ይህንንም ቡና ከጠጣህ ፈጥነህ ትድናለህ ለልጅ ልጅ ዘመን በመካ መዲና መስዋዕት አድርገህ ሰዋ ብሎ ቆልቶ ያሰየዋል፡፡

መሀመድም ብረት ምጣድ አግሎ ያሳየዋል እንደመልኬ ከሰል አስመስልህ አጥቁረህ ትቆላለህ ይለዋል እንዳለው አድርጎ ከሰል አስመስሎ ይቆላል ሁል ጊዜም እንደዚሁ ካላከሰልክ መድሀኒት አይሆንህም ይለዋል ራስ ምታቱም ለጊዜው የተወው ይመስለዋል ኋላ ግን ሰዓት እየጠበቀ ይነሳበታል።

በመሓመድ ሥርዓትና ሕግ የሚጓዙ አወል ፤ ቶና ፤ በረካ የሚባሉ ሦስት ሰዎች ለንግድ የመጡ መስለው ከአምስት ተከታዬቻቸው ጋር እነዚህን ዕፅዋት ይዘው ይመጣሉ እነዚህም «ጫት፤ ቡና ፤ ጥንባሆ» ናቸው አህዛብ ለሰይጣን የሚያቀርቡዋቸው የጣኦት መስዋዕት ናቸው። የእግዚአብሔር መስዋእት ግን፤ 

  • ስንዴ
  • ዘቢብ
  • እጣን

ናቸው።

አርብ እና እሮብ ብዙ ሰዎችን እያዛጋ ከቅዳሴ የሚያስቀረው እኮ ቡና ነው። በፆም ሰዓት ብዙ ሰዎችን በራስ ምታት የሚቀውር ቡና ነው። ቡና ካልጠጡ ደስታቸውን የሚያጡ፣ የሚነጫነጩ፣ የሚሳደቡ፣ የሚደብራቸው ቤቱ ይቁጠራቸው። ቡና ቁጭ ተብሎ የሰው ሥጋ በሃሜት የሚበላበት ወሬ እንቶ ፈንቶ የሚሰለቅበት ነው። ሥራ ፈቶች እስከ 3ኛ የሚያንቃርሩት ቡና ቤተክርስትያን እስከምታወግዘው መጠበቅ የለብንም። እግዚአብሔር የሰጠንን አእምሮ መጠቀም ብቻ በቂ ነው።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

___________________

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: