Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • April 2023
    M T W T F S S
     12
    3456789
    10111213141516
    17181920212223
    24252627282930
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ኢሬቻ በላይ’

በስቅለት ዕለት የብጹዕነታቸውን ድምጽ ለማፈን ተሞክሮ ነበርን? | ኢሬቻ በላይ ምን ይሠራ ነበር?

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on May 9, 2021

ባለፈው የጌታችን የስቅለት ዕለት ከቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በቀጥታ ስርጭት ወቅት የብጹእ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስን መልዕክት ለማፈን ድምጽ /ኦዲዮ-አርታኢው ድምጹን “ምን ሊሉ ነው?” በሚል ፍርሃት እየተከታተለ ለማገድ/ለመዝጋት ሲሞክር እንደነበር ሆኖ በወቅቱ ተሰምቶኛል። ብዙዎችም፤ “ምነው ተቋረጠ? ድምጹ ምን ሆነ?” ብለው በቻት ክፍል ሲጽፉ ይነበብ ነበር።

ብጹእነታቸው መልዕክታቸውን ሳይጨርሱ ምስሉም ድምጹም ከቆመ/ከቀዘቀዘ በኋላ የዋቄዮ-አላህ-አቴቴ ጭፍራን አርዮስ-ኢሬቻ በላይን አመጡት፤ በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥም በኢንተርኔት የቀጥታ ስርጭት ላይም የነበሩት ምዕመናኑም ሁሉ ተረበሹ፣ ኩምሽሽ! አሉ።

ኢሬቻ በላይ ከሚያነባቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ለመረዳት እንደሞከርኩት፤ አውሬው በላይ “… የኢትዮጵያ ችግር የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢት ነው፤ በትግራይ ሰላም አይኖርም፣ ልጆቻቸው ያልቃሉ፣ ሰዎች ይራባሉ…ኢትዮጵያም ትፈርሳለች…”

የሚለውን መልዕክት ለማስተላለፍ የሞከረ ይመስላል፤ “አቡነ ፋኑኤል” የተባሉት “አባትም” የአርዮስን ፈልግ ከሚከተሉት ውስጥ አንዱ ናቸው። ወዮላቸው!

አርዮስ ስለ መንፈስ ቅዱስ ሲናገር “ወልድ ለአብ የመጀመሪያ ፍጥረቱ እንደሆነ፣ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ለወልድ የመጀመሪያ ፍጥረቱ ነው” ይል ነበር፡፡

ይህን የአርዮስን ክሕደት የሰማው የእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ (ፓትርያርክ) ተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስ አርዮስን አስጠርቶ የሚያስተምረው ትምህርት ሁሉ የተሳሳተ መሆኑን ገልጾለት ከስሕተቱ ተመልሶና ተጸጽቶ ከቅዱሳን አበው ሲተላለፍ በመጣው በኦርቶዶክስ እምነት እንዲጸና መከረው፡፡ አርዮስ ግን ከአባቱ ከተፍጻሜተ ሰማዕት ጴጥሮስ የተሰጠውን ምክር ወደ ጎን በመተው የክሕደት ትምህርቱን በሰፊው ማስተማር ቀጠለ፡፡ ይህንን የተመለከተ ያ ደግ አባት አርዮስን አውግዞ ከዲቁና ማዕረጉ ሻረው፡፡ የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት እንደሚለው፣ ተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስ አርዮስን ያወገዘው ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በራእይ ተገልጦለት በሰጠው ትእዛዝ መሠረት ነው፡፡

በአንድ ሌሊት በራእይ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድ ወጣት አምሳል እንደ ፀሓይ የሚያበራ ረጅም ነጭ ልብስ (ቀሚስ) ለብሶ ለቅዱስ ጴጥሮስ ይታየዋል፡፡ ልብሱ ለሁለት የተቀደደ ሆኖ ቢያየው ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ ደንግጦ ጌታን ‹‹መኑ ሰጠጣ ለልብስከ፤ ልብስህን ማን ቀደደብህ?›› ብሎ ይጠይቀዋል፡፡ ጌታም ‹‹አርዮስ ልብሴን ቀደደብኝ›› ብሎ መለሰለት፡፡ ይኸውም በአባቶች ትርጕም ‹‹አርዮስ ከባሕርይ አባቴ ከአብ ለየኝ (አሳነሰኝ)›› ማለት ነው፡፡ ጌታም አርዮስን ከእንግዲህ ወዲያ ወደ ቤተ ክርስቲያን አንድነት እንዳይቀበለው አዝዞት ተሰወረ፡፡

👉 ባለፈው ዓመት በትንሣኤ የቀረበ፦

✞“የፋሲካ የጸሎት መርሀ ግብሮችን ያስተላለፈውን የ ”ባላገሩ”ን የሉሲፈር ኮከብ አላያችሁምን?” ✞

__________________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ማህብረ ቅዱሳን በዋቄዮ-አላህ ኦሮሞ እና ኦሮማራ ቃኤላውያን እጅ ገብቷልን?

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on March 11, 2021

💭 ክፍል ፩

ማህብረ ቅዱሳን የትግርኛ ቋንቋ ሥርጭቱን አቁሟልን? በአማርኛ፣ በኦሮምኛ እና በእንግሊዝኛ ብቻ ነው ፕሮግራሙን ተንኮለኛ በሆነ መልክ በማሰራጨት ላይ ያለው።

💭 ክፍል ፪

ጥምቀት ከተራ ፪ሺ፲፫ ዓ.ም

አርዮስ ኢሬቻ ጂኒ በላይ “ነጭ ለብሶ” ቤተ ክህነትን በሂደት ሲረከባት፤ እግዚኦ!

🔥 “ፈንቅል! ፈንቅል! ፈንቅል!” ሲሉን የነበረው መፈንቅሉ በተዋሕዶ እና ኢትዮጵያ (ትግራይ) ላይ መሆኑ ነው።

ወንጀለኛው እባብ አብዮት አህመድ አሊ ለ“ፈንቅል ድራማው” በመሪነት አስቀምጦት የነበረውን አቶ የማነ ንጉሴን (ነፍሱን ይማርለት!)ልከ እንደ እነ ኢንጂነር ስመኘውና ጄነራል ሰዓረ አስጠግቶት አመቺ በሆነለት ወቅት ገደለው። አሁን ያቀደውን በቅደም ተከተልና አንድ በአንድ በማስፈጸም ላይ ነው። ግራኝ አብዮት አህመድ አሊ በቅርቡ የእርሱ ተራ ደርሶና በእሳት ተጠርጎ ወደ ሲዖል እስከሚወረወር ድረስ ደጋፊዎቹን ቃኤላውያኑን እያጋለጠልልንና እየገላለጠልን ያዋርድልን፣ ያቅበዝብዝልን! እኛ ሁሉንም እንመዘግበዋለን።

🔥 “ፈንቅል! ፈንቅል! ፈንቅል!”

🌑 ከሦስት ዓመታት በፊት የኦሮሞ መፈንቅለ መንግስት በአራት ኪሎ ተካሄደ

🌑 በሦስት ዓመታት ውስጥ መፈንቅለ ሠራዊት፣ ድርጅቶችና ተቋማት ተካሄደ

🌑 የመውረሱ ሂደቱ የቆየ ቢሆንም አሁን በማህበረ ቅዱሳን መፍንቅለ ማህበር ተካሄደ

🌑 ዛሬ ደግሞ መፈንቅለ ቤተ ክህነት በቅደም ተከተል እየተካሄደ ነው። እነ ኢሬቻ በላይን ቤተ ክህነትን እናወርሳችሁና ኢትዮጵያን የእግዚአብሔር ሳይሆን የዋቄዮ-አላህ-አቴቴ ምድር ታደርጓታላችሁ ፤ አትቸኩሉ መገንጠል አያስፈልግም” አሏቸው።

______________________________________

Posted in Conspiracies, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

አብዮት እና ታከለ ይሆኑ አቡነ መልከጼዴቅን በቅዱስ ሚካኤል ዕለት ከአዲስ አበባ ያባረሯቸው? ወንበሩን የኢሬቻ ዘመዳቸው ጠቅልለው ይይዙት ዘንድ?

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 22, 2019

በዚህ ድንቅ ስብከታቸው(ሙሉውን በሌላ ጊዜ አቀርበዋለሁ) ምክኒያት ይሆን አቡነ መልከጼዴቅ የተባረሩት? ወይስ ሌላ ነገር አለ?

ከመፈንቅለ መንግስቱ ቀጥሎ አሁን መፈንቅለ ወንበር በቤተክርስቲያናችን ውስጥ እየተካሄደ ይሆን?

መጀመሪያ ላይ፤ ከአብዮት አህመድ ትውልድ ከተማ ከጂማ እና ከታከለ ገማ ትውልድ ከተማ ከ አንቦ ተባርረው ወደ አዲስ አበባ የመጡትንና በአዱሱ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ተጠልለው የነበሩትን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ቤተከርስቲያኑን ለቀቅው እንዲወጡ ተደረጉ፤ ከዚያ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የፓትርያርኩ ረዳት የሆኑት ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ከወንበራቸው እንዲነሱ ተደረጉ፤ ያውም በቅዱስ ሚካኤል ዕለት! ተማሪዎቹ የአዲሱ ሚካኤል ቤተክርስቲያንን ግቢ እንዲለቅቁ በከፍተኛ ባለስልጣን ትዕዛዙ እንደተሰጠ ተወርቶ ነበር። አሁን የፕሮፓጋንዳና ቅጥፈት አርቲስቶቹ አብዮት አህመድና ታከል ገማ፤ አቡነ መልኬ ጻዲቅ ናቸው ይህን ትዕዛዝ ሰጥተው የነበሩት፣ ከአዲስ አበባ መባረራቸውም ተገቢ ነውየሚል ተልካሻ ቅስቀሳ እንዲካሄድ እያደረጉ ነው።ውሻውን መጥፎ ስም ሰጥተህ ስቀለው / ‘Give the dog a bad name and hang him ይሉ የለ።

ቀደም ሲል አቡነ መልከጼዴቅ ለታከለ ገማ ገንዘብ ለመስጠት ፈቃደኛ ነበሩእየተባለ ሲነገር ነበር። በእውነት ይህን ለማድረግ ከወሰኑ ምክኒያታቸው ምን ይሆን? አብዮትና ታከለ ወንበራቸውን በመነቅነቅ ላይ እንደሆኑ ስላወቁ ይሆን? ወይስ ሌላ ነገር አለ? ለማንኛውም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ ተደረገው የተሾሙት የአብዮት አህመድና የታገለ ገማ ኦሮሞ ወንድም መ/ር አባ ሞገስ ኃይለማርያም ናቸው። *(ሌላ ኃይለማርያም?!)

በሁሉም ቦታ መፈንቅለ ወንበር፣ መፈንቅለ ሥርዓት እየተካሄደ ነው። ከዓመታት በፊት በአዲስ አበባ አብያተ ክርስቲያናት ላይ የዋቄዮአላህን የጥፋት ዘመቻ ለመጀመር አሁን ለመስለም በመዘጋጀት ላይ የሚገኘውን ኢሬቻ በላይን የሃገረ ስብከቷ ስራ አስኪያጅ ማድረጋቸው የሚታወስ ነው። ዛሬም ዓይናችን እያየ ታሪክ ራሱን እየደገመ ይሆን? *(ሌላ ኢሬቻ በላይ?! )

በአብዮትና በታከለ እንዲሁም በአራት ኪሎ የጂሃድ ዋሻቸው ላይ ቅዱስ ሚካኤል እሳቱን ያውርድባቸው!

________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: