ከ ካይሮ በስተ ምሥራቅ በሚገኝ ቦታ ላይ በመካከለኛው ምስራቅ አንጋፋ የሆነውን ቤተክርስቲያን ሕንፃ ፓትሪያርክ ታዎድሮስ እና የግብጹ ፕሬዚደንት አብዱል–ፋታህ አሌ–ሲሲ መርቀው ከፈተዋል። ሕንፃው “የልደት ካቴድራል” የሚል ስም ተሰጥቶታል።
ቀደም ሲል፡ በቅዳሜው ዕለት፡ ሙስሊሞች ቤተከርስቲያኑን በቦምብ ለማፈንዳት ባቅራቢው በሚገኝ ትልቅ መስጊድ ጣራ ላይ ቦምብ አጥምደው ተገኝተው ነበር። ቦምቡን ያከሸፍ ዘንድ ወደ መስጊዱ ተልኮ የነበረው አንድ ፖሊስ በፍንዳታ ሳቢያ ሕይወቱን አጥቷል።
የግብጽ ፕሬዚዳንት በመክፈቻው ሥነ ሥርዓት ላይ “ይህ ታሪካዊና አስፈላጊ ጊዜ ነው፣
ነገር ግን፤ እኛ እዚህ በአንድ ላይ የተከልነውን የፍቅር ዛፍ መጠበቅ አለብን” በማለት ተናግረዋል።
የመሀመድ አርበኞች የክርስቶስ ተከታዮችን ክፉኛ በመምታት ላይ በሚገኙበት በዚህ ዘመን፡ በእስያ እና አፍሪቃ ክርስትና እንደ ምስማር በመጥበቅ ላይ ነው።
ይህ ድንቅ የገና ተዓምር ነው! በእውነት ለክርስቲያን ወገኖቻችን ትልቅ ድል ነው፤ እንግዲህ ዲያብሎስና አርበኞቹ አሁን እርር፡ ፍርክስክስ ይበሉ፤ ጊዚያቸው አጭር ነው።
እውነት ነው፤ የሰማዕታት ደም የቤተ ክርስቲያን [ምርጥ] ዘር ነው። እኛ ክርስቲያኖች እንገፋለን እንጂ አንወድቅም፤ አዎ! ክርስቲያን እንደ ምስማር ሲመቱት የሚጠብቅ ነው።
+++የባሪያይቱን መዋረድ አይቶ+++
+++ንጉሥ ወደደሽ ከሴት ለይቶ+++
+++ዝቅ ማለትሽ ከፍ አድርጐሻል+++
+++ድንግል ትሕትናሽ ፍቅር አስጊጦሻል+++