Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ኅዳር ሚካኤል’

‘White Ethiopians’ Singing Hymn to St. Michael in Ethiopic/ Geez | የቅዱስ ሚካኤል ግዕዝ መዝሙር በነጭ ኢትዮጵያውያን አንደበት

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 21, 2022

❖ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትናን የተቀበለ ሁሉ የክርስቶስ ቤተሰብ ነው፤ ኢትዮጵያዊ ነው!

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትናን የሚቀበል ሁሉ የእግዚአብሔር ቤተሰብ አካል ነው፤ ስለዚህ ኢትዮጵያዊ ነው! የእግዚአብሔር ልጅ መባል እና የቤተሰቡ አባል መሆን ትልቅ ክብር ነው። የትም ብትሄድ ወይም ማን ብትሆን ሁልጊዜም የእግዚአብሔር ቤተሰብ አካል ትሆናለህ። ሁሉም አማኞች የቸሩ ጌታ የልዑል እግዚአብሔር ልጆች ናቸው።

በኢየሱስ የሚያምኑ ብቻ የእግዚአብሔር ቤተሰብ አካል ይሆናሉ። የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፩፥፲፪፡፲፫፤

ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም።”

በዓለም ላይ ያለ ማንኛውም ክርስቲያን የእግዚአብሔር ቤተሰብ አካል ነው። አማኞቹ በአፍሪካ፣ በአሜሪካ፣ በአውሮፓ፣ በእስያ ወይም በአውስትራሊያ ቢኖሩ የእግዚአብሔር ቤተሰብ አካል ናቸው። የእግዚአብሔር ቤተሰብ በማንኛውም ባህል፣ ጎሣ፣ ዕድሜ፣ ወይም ጾታ የተገደበ አይደለም (ገላትያ ፫፥፳፰)። በእግዚአብሔር ቤተሰብ ውስጥ ያለ ሰው ሁሉ እኩል ነው (ሮሜ ፪፲፩)

የማያምኑ ሰዎች በክርስቶስ ስቅለት፣ ቀብር እና ትንሣኤ ላይ እምነት ስላላደረጉ የእግዚአብሔር ቤተሰብ አባል አይደሉም። አማኝ ከሆኑ ግን እነሱም የእግዚአብሔር አምላክ ቤተሰብ አባላት መሆን ይችላሉ። የእግዚአብሔር ቤተሰብ አባል መሆን ድንቅ ነገር ነው። የእግዚአብሔር ቤተሰብ አካል ከመሆን የበለጠ ምንም ነገር የለም።

እነዚህ ፈረንጅ ወንድሞች ኢትዮጵያን፣ ተዋሕዶ ክርስትናን እና የግዕዝ ቋንቋን ለመክዳት ከወሰኑት ጋላኦሮሞዎች ይልቅ የክርስቶስ አምላክ ቤተሰብ አካል ለመሆን በመብቃታቸው በጣም የታደሉ ናቸው። ከሃዲዎቹ ግን ወዮላቸው!

❖ Everyone who accepts Orthodox Tewahedo Christianity is part of the Family of God Egziabher, and He or She is Ethiopian! It is a great honor to be called a child of God Egziabher and to be a part of His family. No matter where you go or who you are, you will always be part of God’s family. All believers are children of the Good Lord God Almighty Egziabher.

Only those who place faith in Jesus become part of God’s family. John 1:12-13 says;

“Yet to all who did receive him, to those who believed in his name, he gave the right to become children of God — children born not of natural descent, nor of human decision or a husband’s will, but born of God.”

If you are a Christian, then you are a child of God and you are part of God’s family. You will never lose your place in God’s family as once a person is saved; they are always saved. Nobody can lose their salvation as salvation is a gift from God. Salvation is not based on anything we do, but rather on placing faith in Jesus (Ephesians 2:8-9).

Unbelievers are not part of the family of God because they have not placed faith in Jesus’ death, burial, and resurrection. If they become a believer, then they too can become members of God’s family. Becoming a member of the family of God is a wonderful thing. There is nothing greater than being part of the family of God.

It is a great honor and privilege to know God as your Father. Being a member of the family of God includes knowing that you are eternally and forever loved by God Almighty. It means that you can never lose your place in His family. The concept of being part of “a family” can be foreign to many of us.

Broken homes, hatred between family members, or never knowing your parents can cause an individual to be skeptical of the idea of a “family.” In God’s family, there is no abandonment, hatred, or abuse. Only love, forgiveness, and grace abide within God’s family. He will never cast you out or turn you away (Isaiah 41:10).

Since we have God as our Father, we can freely talk to Him in prayer any time we want. God is the Holy Trinity, which is the Father, Jesus, and the Holy Spirit. Three distinct Persons — One God. As children of God, we can pray to Him anytime, anywhere.

You do not have to use eloquent words, lengthy prayers, or rehearse your words in order for God to hear you. Jesus’ death on the cross enabled us to become children of God. If it was not for Jesus’ death, burial, and resurrection, we would not be children of God. This is something worth reflecting on as we owe our entire beings to God.

It is only by His mercy that we are privileged to spend eternity with Him. God loves us so much that He willingly sent His Son to die for us (John 3:16-17). There is no greater love than the love God has for His children.

Maybe your father, mother, or siblings did not treat you very well growing up. Even if our earthly families have hurt us or abandoned us, we know God never will. Psalm 27:10 tells us, “Though my father and mother forsake me, the Lord will receive me.” God will never forsake you. He can be fully trusted.

We Are the Family of God

Every Christian in the world is part of the family of God. Whether the believer lives in Africa, America, Europe, Asia, or Australia, they are part of the family of God. God’s family is not restricted to any culture, ethnicity, age, or gender (Galatians 3:28). Every person within the family of God is equal (Romans 2:11).

Likewise, each person is strongly beloved by God, and He wants all people to know Him. Once we accept Jesus as our Savior, we become eternally part of God’s family. As part of God’s family, we inherit thousands of brothers and sisters in Christ.

😇 Commemoration of the Archangel Saint Michael- የሕዳር ሚካኤል

Ethiopian Orthodox Tewahedo Church honors Saint Michael (Kidus Mikael); the Angel of mercy; on the 12th of each month of which two of them are great annual feasts of the saint – on Hidar 12 (November 21) and Senie 12 (June 19). His name Michael means “who is like God”.

Saint Michael is one of the seven Archangels, who is always standing besides God’s throne and is honored for defeating Devil at God’s command (Rev.12:7-9).

In addition to the Holy Bible, “Dersane Michael” contains the miracles of St. Michael. Archangel Saint Michael is powerful and the guardian of the souls and fighter against evil. He is often painted in the walls of every Ethiopian Orthodox Tewahedo church followers with a flaming sword and spear, which pierces the devil.

❖ On Hidar / ሕዳር ፲፪/ 12 (November 21):

1. Crowned and became the Arch of the Archangel’s

Saint Michael is one of the seven Archangels, who is always standing besides God’s throne and is honored for leading the army of Holy Angels and defeated Satan and the rebellious angels into Hell. Revelation 12:7 On this day God crowned him with his glory and mercy and become the Arch of the the Archangel’s

2. The Commander of the Lord’s Army

Joshua, the son of Nun, saw him in great glory and was frightened by him and fell on his face to the earth and said to him, “Are you for us, or for our adversaries?” So he said, “No; but as Commander of the army of the Lord… I have given Jericho into your hand, … and its king.” (Joshua 5:13-15, 6:2)

3. The Exodus of Israel from Egypt through the help of the Arch Angle Michael

Exodus 14:19-22:

19 Then the angel of God, who had been traveling in front of Israel’s army, withdrew and went behind them. The pillar of cloud also moved from in front and stood behind them, 20 coming between the armies of Egypt and Israel. Throughout the night the cloud brought darkness to the one side and light to the other side; so neither went near the other all night long.

21 Then Moses stretched out his hand over the sea, and all that night the Lord drove the sea back with a strong east wind and turned it into dry land. The waters were divided, 22 and the Israelites went through the sea on dry ground, with a wall of water on their right and on their left.

23 The Egyptians pursued them, and all Pharaoh’s horses and chariots and horsemen followed them into the sea. 24 During the last watch of the night the Lord looked down from the pillar of fire and cloud at the Egyptian army and threw it into confusion. 25 He jammed[a] the wheels of their chariots so that they had difficulty driving. And the Egyptians said, “Let’s get away from the Israelites! The Lord is fighting for them against Egypt.”

26 Then the Lord said to Moses, “Stretch out your hand over the sea so that the waters may flow back over the Egyptians and their chariots and horsemen.” 27 Moses stretched out his hand over the sea, and at daybreak the sea went back to its place. The Egyptians were fleeing toward[b] it, and the Lord swept them into the sea. 28 The water flowed back and covered the chariots and horsemen—the entire army of Pharaoh that had followed the Israelites into the sea. Not one of them survived.

29 But the Israelites went through the sea on dry ground, with a wall of water on their right and on their left. 30 That day the Lord saved Israel from the hands of the Egyptians, and Israel saw the Egyptians lying dead on the shore. 31 And when the Israelites saw the mighty hand of the Lord displayed against the Egyptians, the people feared the Lord and put their trust in him and in Moses his servant.

Michael, is the commander of the angels, came down from heaven, and rolled back the stone from the mouth of the tomb, and announced the women “Christ is risen from the dead”.

St. Paul observes that the Hebrews “ all our fathers were under the cloud, and all passed through the sea; and were all baptized unto Moses in the cloud and in the sea” (1 Cor. 10:1-4; Rom. 6:3-4; Gal. 3:27).

There is a common ritual practiced by the devotees in order to commemorate, worship and give thanks. Ethiopian traditional bread – Difo Dabo, roasted barley – Kolo in the name of St. Michael are being prepared and shared in the church.

May the prayer of Archangel Saint Michael be up on us!

______________

Posted in Ethiopia, Faith, Saints/ቅዱሳን | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

“በዚያ ወራት ስለ ሕዝብ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል” [ዳን ፲፪.፩]

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 21, 2022

✞✞✞

እያንዳንዱ ክርስቲያን በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙ ቅዱሳን መላእክት አሉት

የእግዚአብሔር መልአክ ስሙ ድንቅ ነው … ኃያሉ ሚካኤል ድንቅን አደረገ

😇 ፈጣኑ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ፤ አስቀድሞ የተጣላህን በቀል ባለመርሳት ጋሻህን አንሣ፤ ፈጣኑ መልአክ ሆይ ነበልባላዊ ሰይፍህን በጠላታችን በዲያብሎስ ላይ መዘህ ተነሣሣበት።

ኃያሉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ፤ ኃይልህን የስው ኃይል ሊተካከለው አይችልምና የክርስቶስን ልጆች ጽዮናውያንን፤ “እንግደላቸው፣ ከምድረ ገጽ እናጥፋቸው ብለው በአባቶቼና እናቶቼ ላይ፣ በወንድሞቼና እኅቶቼ እና ልጆቻቸው ሁሉ ላይ የዘመቱትን የዋቄዮ-አላህ-ዲያብሎስ ጭፍሮች ጠላቶቻችንን ጭጋን በቀላቀለ ዓውሎ ነፋስ በታትነህ ከገጸ ምድር አጥፋቸው። ሕፃናትን በርሃብ ለመፍጀት የጨከኑትን እነዚህን አውሬዎች በእሳት ጠራርጋቸው። ድል አድራጊው መልአክ ሆይ፤ ያ የቀድሞ አመፀኛው አውሬ ዲያብሎስ የጥንት ተንኰሉ ሊተው አልቻለምና የጦር መሣሪያህን ታጥቀህ፣ መጥተህ እነ ግራኝ አብዮት አህመድ አሊንና ጭፍሮቹን ሁሉ ድምጥማጣቸውን አጥፋቸው።

😇 እንኳን ለሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤል አመታዊ የንግስ በዓል አደረሳችሁ። በዓሉን የበረከት በዓል ያድርግልን።

😇 ሊቀ መላእክ ቅዱስ ሚካኤል ይጠብቅን

______________

Posted in Ethiopia, Faith, War & Crisis | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

እስኪ ተመልከቱ | የሰላም ሚንስቴር ተዋሕዶ ፥ የኖቤል ተሸላሚ እነዚህ ውብ ልጆቿ መሆን ነበረባቸው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 24, 2019

በጤናማው ዓለም። ግን ምግባረ ብልሹ ከሆነው ከዚህ የሰይጣን ዓለም ብዙም አይጠበቀም። የዲያብሎስ ልጆች እርስበርስ እየተሿሿሙና እየተሸላለሙ በዚህ የዋሕ ሕዝብ ላይ ይሳለቁበታል። ግድ የለም፡ ጊዚያቸው በጣም አጭር ነው!

እየበረረ ከሰማይ

************

እየበረረ ከሰማይ

ምሕረትን ይዞ ከአዶናይ

የሙሴ ረዳት የእስራኤል

ሊረዳኝ መጣ ሚካኤል

ዐይኖቹ እንደርግብ ልብሱ እንደመብረቅ

መስቀሉን ጨብጦ ምልክቱን የእርቅ

የመላእክት አለቃ ከፍ ያለ መንበሩ

ኢዮርና ራማ ኤረር ነው ሀገሩ

ያላገዘው የለም ያልረዳው ሚካኤል

በምልጃው ተማምኖ ከሚጠሩት መሐል

ዘወትር የሚሰግድ በእግዚአብሔር ፊት

መጋቤ ብሉይ ነው ሊቀ መላእክት

ታሪክ መዝግቦታል መጋቤ መሆኑን

መንገድ እየመራ ህዝበ እስራኤልን

በሚፈሩት ዙሪያ በክንፎቹ ጋርዶ

ከጭንቅ ይሰውራል ከሰማያት ወርዶ

መሪ ነው ሚካኤል በቃዴስ በሲና

ሌሊቱን በብርሃን ቀኑን በደመና

ከሰማይ ወደ ምድር ዘንዶውን ጥሎታል

ከመላእክት መሐል ማንስ ይመስለዋል

________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

ዲያብሎስን የሚያስቀናው ይህ የተዋሕዶ ፍቅር፣ ውበት፣ ጽናትና እርግባዊ ቅንነት ነው

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 23, 2019

የኅዳር ፲፪ / ፪ሺ፲፪ ዓ.(ልብ እንበል በ፲፪/ ፲፪) የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን

ሌላው ያስደሰተኝ ነገር፤ የሉሲፈር ኮከብ ከሰንደቅ ዓላማችን ላይ ተነስቶ ማየቴ ነው። ዲያብሎስ ይቃጠል!

ቅዱስ ሚካኤል ጠላታችንን ሰይጣንን በሰይፉ ቆራርጦ ከእግራችን ስር ይጣልልን

________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

አብዮት እና ታከለ ይሆኑ አቡነ መልከጼዴቅን በቅዱስ ሚካኤል ዕለት ከአዲስ አበባ ያባረሯቸው? ወንበሩን የኢሬቻ ዘመዳቸው ጠቅልለው ይይዙት ዘንድ?

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 22, 2019

በዚህ ድንቅ ስብከታቸው(ሙሉውን በሌላ ጊዜ አቀርበዋለሁ) ምክኒያት ይሆን አቡነ መልከጼዴቅ የተባረሩት? ወይስ ሌላ ነገር አለ?

ከመፈንቅለ መንግስቱ ቀጥሎ አሁን መፈንቅለ ወንበር በቤተክርስቲያናችን ውስጥ እየተካሄደ ይሆን?

መጀመሪያ ላይ፤ ከአብዮት አህመድ ትውልድ ከተማ ከጂማ እና ከታከለ ገማ ትውልድ ከተማ ከ አንቦ ተባርረው ወደ አዲስ አበባ የመጡትንና በአዱሱ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ተጠልለው የነበሩትን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ቤተከርስቲያኑን ለቀቅው እንዲወጡ ተደረጉ፤ ከዚያ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የፓትርያርኩ ረዳት የሆኑት ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ከወንበራቸው እንዲነሱ ተደረጉ፤ ያውም በቅዱስ ሚካኤል ዕለት! ተማሪዎቹ የአዲሱ ሚካኤል ቤተክርስቲያንን ግቢ እንዲለቅቁ በከፍተኛ ባለስልጣን ትዕዛዙ እንደተሰጠ ተወርቶ ነበር። አሁን የፕሮፓጋንዳና ቅጥፈት አርቲስቶቹ አብዮት አህመድና ታከል ገማ፤ አቡነ መልኬ ጻዲቅ ናቸው ይህን ትዕዛዝ ሰጥተው የነበሩት፣ ከአዲስ አበባ መባረራቸውም ተገቢ ነውየሚል ተልካሻ ቅስቀሳ እንዲካሄድ እያደረጉ ነው።ውሻውን መጥፎ ስም ሰጥተህ ስቀለው / ‘Give the dog a bad name and hang him ይሉ የለ።

ቀደም ሲል አቡነ መልከጼዴቅ ለታከለ ገማ ገንዘብ ለመስጠት ፈቃደኛ ነበሩእየተባለ ሲነገር ነበር። በእውነት ይህን ለማድረግ ከወሰኑ ምክኒያታቸው ምን ይሆን? አብዮትና ታከለ ወንበራቸውን በመነቅነቅ ላይ እንደሆኑ ስላወቁ ይሆን? ወይስ ሌላ ነገር አለ? ለማንኛውም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ ተደረገው የተሾሙት የአብዮት አህመድና የታገለ ገማ ኦሮሞ ወንድም መ/ር አባ ሞገስ ኃይለማርያም ናቸው። *(ሌላ ኃይለማርያም?!)

በሁሉም ቦታ መፈንቅለ ወንበር፣ መፈንቅለ ሥርዓት እየተካሄደ ነው። ከዓመታት በፊት በአዲስ አበባ አብያተ ክርስቲያናት ላይ የዋቄዮአላህን የጥፋት ዘመቻ ለመጀመር አሁን ለመስለም በመዘጋጀት ላይ የሚገኘውን ኢሬቻ በላይን የሃገረ ስብከቷ ስራ አስኪያጅ ማድረጋቸው የሚታወስ ነው። ዛሬም ዓይናችን እያየ ታሪክ ራሱን እየደገመ ይሆን? *(ሌላ ኢሬቻ በላይ?! )

በአብዮትና በታከለ እንዲሁም በአራት ኪሎ የጂሃድ ዋሻቸው ላይ ቅዱስ ሚካኤል እሳቱን ያውርድባቸው!

________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , | Leave a Comment »

እጹብ ድንቅ ነው | ህመምተኞች በንቡ የሚፈውሱበት ተዓምረኛው “ንቡ ቅዱስ ሚካኤል”

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 21, 2019

በእውነት እናት ኢትዮጵያ ብዙ እጹብ ድንቅ የሆኑ ምስጢሮችን የያዘች ተዓምረኛ አገር ናት።

ንቡ ሚካኤል” በአዲስ አበባ፡ አያት የሚባለውን ቦታ አለፍ ብሎ በሻሌ ኮረብታ ላይ የሚገኝ ቤተክርስቲያን ነው። ወደዚህ ቤተክርስቲያን እንዴት እነደመጣሁ ሁሉ አላውቅም፤ ቅዱስ ሚካኤል ነው ያመጣኝ።

የንቡ ቀፎ ቤተክርስቲያኑ ውስጥ ነው ያለው። የንቡም መንጋ ቤተልሔም ውስጥ ገብቶ እስከአሁን ድረስ ሰፍሮ ይገኛል። በቅዳሴ ሰዓትና ታቦት በሚወጣበትም ጊዜ ሁሉ ቤተክርስቲያኑ ውስጥ ንቡ ይወጣል። በንብ የሚነደፍ ከተለያዩ በሽታዎች ይፈወሳል። ንቦቹ ዝም ብለው አይናድፉም፤ የተፈቀደለት ሰው ነው ሊነደፍ የሚችለው። ይሄን እንደሰማሁ በጣም ተደስቼ ጢናማ ያደረገኝ ቸሩ እግዚአብሔር ይመስገን፤ ዶክተር ካየሁ ሃያ ዓመት ገደማ ሆኖኛል ፥ ግን ሳጥናኤል አገር እየተኖረ ጋኔን መግቢያ ቀዳዳ አያጣምና በቃ ንቦቹ በውስጤ ሊኖር የሚችለውን መርዝ ነቅለው ሊያወጡልኝ ነው ብዬ ቤተክርስቲይኑን መዞር እንደጀመርኩ ከየት እንደመጣ ያላየሁት አንድ ጎረመሳ ልጅ አብሮኝ ይዞር ጀመር(አልፎ አልፎ ቪዲዮው ላይ ይሰማል)“ከየት መጣህ? ትምህርት ቤት የለህም እንዴ? እንዴት ወደዚህ ብዙ ሰው ወደ ሌለበት ቦታ መጣህ?” ብዬ ጠየቅኩት። እርሱም፡ አይ መንገድ ላይ ከጓደኞቼ ጋር በመኪና መጥተን ተጠፋፋን፣ ከዚያም እኔ ዝም ብዬ ወደዚህ መጣሁአለኝ። ትህትና ያለው ስለነበር አመንኩት። ንቦቹ ቢነድፉኝ በማለት ቤተክርስቲያኑን መዞሩን ቀጠልኩ ግን አሁንም አብሮኝ ይዞራል። በቃ ስላልተነደፍኩ ራመድ ብዬ ከአንዲት ሱባኤ ከያዙና ደስ ከሚሉ እናት ጋር ማውራት ጀመርኩ። ስለቤተክርስቲያኑ በይበልጥ ማወቅ ከፈለግክ በጥቅምት ተመልሰህ ና፤ ያኔም ማር ይቆረጣል ፈውስ ነው ይዘህ ትሄዳለህ አሉኝ። እኔም ከምስጋና ጋር በጥቅምት ስለምጓዝ እንደማልችል አሳውቂያቸውና ተሰናብቻቸው ድንቅ የሆነ ቦታ ላይ ካለው የቤተክርስቲያን ግቢ ወጣሁ። አሁንም ያ ጎረምሳ ተከትሎኝ መጣ፤ እስኪ ባክህ ወደ አያት የሚወሰደው ታክሲ የሚቆምበትን ቦታ አሳየኝአልኩት፤ ቦታውን ካሳየኝ በኋል ሞባይሉን አውጥቶ መደወል ጀመረ። መንገዱ በጣም ጭር ያለ ነው፣ መኪናም ብዙ የለም። በዚህ ጊዜ ከአውቶብስ ማቆሚያው ፊት ለፊት አንድ የስልክ ምሰሶ ላይ ነጭና ጥቁር ቀለም ያለው ቁራ ወደ እኛ አቅጣጫ ሲጮህ ይሰማል። በጣም የሚገርም ነው፤ ጉሮሮው እስኪወጣድርስ በኃይል ነበር የሚጮኸው። ምን እያለን ይሆን?” አልኩት ለልጁ፡ በዚህ ሰዓት መልስ ሳይሰጠኝ ፊቱ ሲለዋወጥ አየሁት። በዚህ ጊዘ አንድ ታክሲ ከች አለ። እንደገባሁ ታክሲው በቅዱስ ሚካኤል እና ቅዱስ ገብርኤል ስዕሎች የደመቀ ነበር። ዋው! ቅዱስ ሚካኤል በቁራው በኩል ስለሆነ ነገር እያስጠነቀቀኝ ነበርአልኩ፤ በጣም በመገረምና በመደሰት።

ከሁለት ቀን በኋላ፡ ማታ ላይ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስቲያን አካባቢ ሦስት ቻይናዎች ወደ ዘረጓቸው እጆቻቸው ሞባይላቸውን አብርተው አየሁና እንግሊዝኛ ትችሉ ይሆን ምን ችግር ገጠማችሁ?” አልኳቸው። እነርሱም በጠራ እንግሊዝኛ እጃችንን ቢንቢዎችን ልናስነክስ ፈልገን ነው፤ ቢንቢዎች ጎጂ ባክቴሪያዎችን ያጠፉልናል፤ እዚህ አገር አየሩ ቆንጆ ስለሆነ ጤናማ ቢንቢዎች ናቸውአሉኝ። ቻይኖቹ ትክክል ናቸው፤ በቅድስት ኢትዮጵያ ንቦቹና ቢንቢዎቹ መድኃኒቶቻችን ናቸው፣ አዕዋፋቱና እንስሳቱ ረዳቶቻችን ናቸው። ቸሩ እግዚአብሔር ለሕዝባችን ሁሉንም ነገር በነፃ አዘጋጅቶለት ሳለ፡ ከወጣት እስከ አዛውንቱ ለቀላል በሽታ የፈረንጁን ኪኒንና መርፌ በውድ ገንዘብ ሲሸምት ሳይ በጣም አዝናለሁ።

በአውሬው መዳፍ ሥር የሚሰቃዩትን ወገኖቻችንን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በዕለተ ቀኑ ይድረስላቸዉ ካሉበት መከራና ስቃይ በምልጃው ያውጣቸው! የእግዚአብሔርን ሕዝብ ከመከራ ታዳጊ ቅዱስ ሚካኤል ነውና የሃገራችን ጠባቂ የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ረድኤት በረከቱ ከሁላችን አይለየን!!!


ተዓምረኛው በሻሌ ንቡ ቅ/ሚካኤል እናሰማዕቱ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን


በንብ መንጋ የተከበበው የበሻሌ(ንቡ) /ሚካኤል፣ ቅ/እስጢፋኖስ እና ወአባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ቤተክርስቲያን አመሰራረትና ገቢረ ተዓምራት አጭር መግለጫ

ቤተክርስቲያኑ ከመመስረቱ በፊት በቦታው ላይ ሲከናወኑ የነበሩ ልዩ ልዩ ተዓምራት፡

1. ለብዙ ዓመታት ከተለያየ ቦታ ተጣልተው የነበሩ ምዕመናን ቦታው ላይ እየመጡ እርቀ ሰላም ሲፈጽሙበት ኖረዋል፤

2. ቤተክርስቲያኑ ከተተከለበት ቦታ ትልቅ የጽድ ዛፍ ላይ የሚወጣው ሙጫ እንደ እጣን ጢስ ሽታ ለብዙ ዓመታት አካባቢውን መዓዛው (ሽታው) ያውድ ነበር፡፡

3. በዚሁ ቦታ ላይ ሌሊት ሌሊት የመላዕክት ዝማሬ (ጣዕመ ዜማ) የከበሮ ድምጽ ይሰማ እንደነበረ በዕድሜ የገፉ የአካባቢው አዛውንቶች ተናግረዋል፡፡

4. በአካባቢው ከሚኖሩ ምዕመናን መካከል በመልካም ስራቸው የታወቁና ከ90 ዓመት በላይ ዕድሜ የነበራቸው እናት የቅዱስ ሚካኤል ታቦት(ጽላት) እንደሚተከል በተደጋጋሚ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ይናገሩ ነበር፡፡

5. ቀደም ሲል በእነ አብርሃ ወአጽብሃ ዘመነ መንግሥት አካባቢ ጀምሮ ከተለያየ አካባቢ የሞቱ አባቶች አስከሬናቸው እየመጣ በቤተመቅደሱ ስለሚገኘው የንብ መንጋ አገባብ(አመጣጥ)

እግዚአብሔር አስቀድሞ ቦታውን ስለመረጠው፡

1. ሕዳር 12 ቀን 2002 .ም የቅዱስ ሚካኤል በዓል ሲከበር በዋዜማው ሊቃውንቱ በአገልግሎት ላይ እንዳሉ ማለትም ሕዳር 11 ቀን 2002 .ም ከቀኑ 900 ሰዓት ገደማ ከምስራቅ አቅጣጫ የንብ መንጋ መጥቶ የቃል ኪዳኑ ታቦት በሚገኝበት በመንበሩ ውስጥ ገብቶ ካደረ በኋላ በነጋታው ታቦቱ ወጥቶ በሚከበረበት ጊዜ ንቡ ከመንበሩ ወጥቶ እንደ ደመና ረቦ ካሉት

ምዕመናን ጋር ታቦቱን ዙሮ አክብሯል፡፡ በዕለቱም ይህን አስደናቂ ታምር ያዩና የተመለከቱ ምዕመናንም በከፍተኛ ድምጽ እግዚአብሔርን አመስግነዋል፡፡

2. ሕዳር 11 ቀን 2004 .ም የድንግል ማርያም ዕለት ካህናቱ ቅዳሴ ገብተው በሚቀድሱበት ጊዜ ቅዱስ ወንጌል ሲነበብ የንብ መንጋ መጥቶ ከቤተክርስቲያኑ ጉልላት ላይ የመስቀል ምልክት ሰርቶ ከሰፈረ በኋላ ከቀኑ 1100 ሰዓት ላይ ተነስቶ ቤተክርስቲያኑን ዙሮ ወደ ቤተልሔም ውስጥ ገብቶ እስከአሁን ድረስ ሰፍሮ ይገኛል፡፡

3. ታህሳስ 9 ቀን 2004 .ም ከቀኑ 900 ሰዓት የንብ መንጋ መጥቶ ከቤተክርስቲያኑ ጎን ላይ ከሰፈረ በኋላ ከቀኑ 1130 ተነስቶ ቤተክርስቲያኑን ዙሮ ወደ ግብር ቤት ገብቶ እስከአሁን

ድረስ ሰፍሮ ይገኛል፡፡

4. ታህሳስ 19 ቀን 2005 .ም የቅዱስ ገብርኤል ዕለት ካህናት ቅዳሴ ገብተው በሚቀድሱበት ጊዜ ቅዱስ ወንጌል ሲነበብ የንብ መንጋ መጥቶ በሴቶች መግቢያ በር ወደቤተክርስቲያኑ ከገባ በኋላ በቀጥታ ወደ ቤተመቅደሱ ውስጥ ገብቶ በአጎበሩ ላይ ሰፍሯል፡፡ ይህ በቤተክርስቲያናችን ላይ ያለው የንብ መንጋ ማሩ ተቆርጦ በተለያየ ጊዜ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰጥቶ ከአገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ በጉበት፣ በካንሰር፣ በኪንታሮት፣ በስኳር፣ በአስም፣ በጨጓራ፣ በኩላሊት፣ በደም ግፊት፣ በኤች አይ ቪ፣ ሽባዎች፣ አይነስውራን፣ አፈ ዲዳዎወች፣ መስማት የተሳናቸው፣ በጭንቀትና በልዩ ልዩ በሽታ የታመሙ ሰዎች ማሩን በልተው ጸበሉን ጠጥተው እምነቱን ተቀብተው ከበሽታቸው ተፈውሰው ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡ እንዲሁም ለብዙ ዓመታት ልጅ አጥተው የነበሩ ሰዎች (መካኖች) በአንድ ጊዜ ሁለት ልጆች መንታ እንዲሁም በአንድ ጊዜ ሶስት ልጆች መንታ ወልደው

ታቅፈው መጥተው ጥምቀተ ክርስትናቸውን በዚሁ ቤተክርስቲያን እንዲፈፀም ማድረጋቸውና ሌሎች በዚህ አነስተኛ ጽሁፍ ሊገለፁ የማይችሉ በርካታ ገቢረ ተዓምራትና ፈውሶች እስከአሁኗ ሰዓት እየተደረጉ ናቸው፡፡ ክብርና ምስጋና ለአምላካችን ለልዑል እግዚአብሔር ይሁን አሜን፡፡

በእግዚአብሔር ፈቃድ በንቦቹ የተደረገው ተዓምራት በከፊል

1. ሕዳር 12 ቀን 2002 .ም የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል ታቦቱ ወጥቶ በሚከበርበት ጊዜ ከቤተመቅደሱ ያለው ንብ ወጥቶ ታቦቱን አክብሯል፡፡

2. 2003 .ም የስቅለት በዓል ሲከበር ንሴብሆ እየተባለ በሚዘምርበት ጊዜ ንቡ ወጥቶ ቤተክርስቲያኑን ዙሮ ገብቷል፡፡

3. መጋቢት 12 ቀን 2004 .ም የቅዱስ ሚካኤል ወርሃዊ በዓል ቅዳሴ እየተቀደሰ ሳለ የቤተመቅደሱ ንብ ከመንበሩ ላይ የመስቀል ምልክት ሰርቶ (ሰፍሮ) ታይቷል፡፡

4. ሕዳር 11 ቀን 2005 .ም ንቡ ለመጀመሪያ ጊዜ የገባበትን ዕለት ለማስታወስ ከቀኑ 400 ሰዓት ላይ ንቡ ወጥቶ ቤተክርስቲያኑን ዙሮ ገብቷል፡፡

5. 2005 .ም ፀሎተ ሐሙስ የሕጽበተ እግር ጸሎት ሲከናወን የመቅደሱ ንብ ወጥቶ ፀበሉ ላይ ሰፍሮ (ረቦ)ታይቷል፡፡

6. 2006 .ም እሁድ የሆሳዕና በዓል ሲከበር ሆሳዕና በአርያም እየተባለ እየተዘመረ ዑደት በሚደረግበት ጊዜ ብዙ ምዕመናን ባለቡት የቤተመቅደሱ ንብ ወጥቶ ዞሮ ገብቷል፡፡ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል፡፡ ለዘላለሙ አሜን፡፡

ሥርዓተ ቀብር ሲፈጸምበት የቆየ እና በተለያየ ጊዜ የቀስተ ደመና ብርሃን በመቃብሩ ላይ ይታይ እንደነበር በአካባቢው የሚኖሩ በዕድሜ የገፉ አዛውንቶች በግልጽ መስክረዋል፡፡ ዛሬም መቃብሩ በግልጽ ይታያል፡፡ ይህ ሁሉ ታሪክ ሲከናወን ከቆየ በኋላ እግዚአብሔር የፈቀደው ጊዜ ሲደርስ በአካባቢው ከሚኖሩ በዕድሜ ከገፉ አዛውንቶች መካከል በአንድ አርሶ አደር ምዕመን አማካኝነት በእግዚአብሔር ፈቃድ በተደጋጋሚ ራዕይ ተገልጾላቸው ያርሱበት የነበረውን ይዞታቸውን መሬት

ለዚህ ታቦት መትከያ ቤተክርስቲያን እንዲሰራ መሬት በመስጠት አሁን በሚገኘው መቃኞ ቤተክርስቲያን ግንቦት 12 ቀን 2001.ም ታቦቱ ሊገባ ችሏል፡፡

አድራሻ፡

በአዲስ አበባ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 10 የሚገኝ ሲሆን ከተለያየ አቅጣጫ ተነስተው መገናኛ ከመገናኛ ሲ.ኤም.ሲ መሪ አያት የሚለውን ትራንስፖርት ይዘው አያት አደባባይ ይውረዱ፡፡ ከአያት አደባባይ ባጃጆች እና ታክሲዎች በሻሌ ንቡ ሚካኤል እና እስጢፋኖስ ካሉ እስከ ቤተክርስቲያኑ ያደርሰዎታል፡፡

እንኳን ለቅዱስ ሚካኤል አመታዊ በዓል አደረሰን!

ይልቃል እርሱ❖

ይልቃል እርሱ ከመላእክት

ትሑት ነው አዛኝ ለፍጥረታት

በክብሩ ምድር ትበራለች

ታላቅ ነህ ሚካኤል እያለች

✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞

ማን እንደ እግዚአብሔር ስሙ ነው የከበረ

ያስጨነቀንን በምልጃው የሰበረ

አለቃ የሆነ ለአእላፍ መላእክት

ታማኝ ባለሟል የምንዱባን አባት

ሚካኤል ነው እርሱ ሚካኤል ነው

ያሳደገን በረከት ያደለን

✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞

መጎናፀፊያው እሳት ነበልባላዊ

ከምድር ያይደለ ክቡር ነው ሰማያዊ

አሸናፊ ነው ጠላትን ድል አድራጊ

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ከመከራ ታዳጊ

ሚካኤል ነው እርሱ ሚካኤል ነው

ያሳደገን በረከት ያደለን

✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞

ከእግዚአብሔር ዘንድ በተሰጠው ኪዳን

በጥልቅ ያሉትን ይሄዳል ለማዳን

ሺዎች በክንፉ ሺዎችን በአክናፉ

ከእሳት የሚያድን ሸሽጎ በእቅፉ

ሚካኤል ነው እርሱ ሚካኤል ነው

ያሳደገን በረከት ያደለን

✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞

አርምሞ ጽርአትት ሳይኖረው መሰልቸት

የሚያሳርገው ተወዳጁን መስዋዕት

በልዑል ዙፋን በፊቱ በሰጊድ

ማነው ስለእኛ በፅኑ ሚማልድ

ሚካኤል ነው እርሱ ሚካኤል ነው

ያሳደገን በረከት ያደለን

✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞

________________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ቅዱስ ምካኤል ወዳጅ ነህ ለሁሉ፤ ዛሬም ቆመሃል በኪዳንህ ላሉ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on November 21, 2017

እርጉም የዲያብሎስ ልጆች በሴቶቻችን፣ በህፃናቶቻችንና በመላው ሕዝባችን ላይ ዘምተዋል፤ ማን ያየናል፣ ማን ያውቅብናል በማለት ሌት ተቀን ይፈታተኗቸዋል፤ ዲያብሎስን ድል የነሣህ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ! የምስጋናን መሥዋዕት የምታዘጋጅ አንተ ነህና ጠላት ዲያብሎስ ተረማምዶ በእደ ፃዕረ ሞት ወገኖቻችንን እንዳያፍን በአፋቸው ላይ ጥበቃህን አጠንክር።

የቅዱስ ሚካኤል አምላክ ሆይ! በአርአያህ በአምሣልህ የፈጠርከን ሕዝቦችህን ሁሉ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ሠውረን ለዘላለሙ አሜን።

ኅዳር ፲፪ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ታላቅ በዓል

ሚካኤል ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ ሚመኑከመኤልአምላክ ማለት ሲሆን በአንድነት ሲነበብ መኑ ከመ አምላክ (እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው) ማለት ነው፡፡ ይህ ታላቅ መልአክ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራዕዩ ‹‹በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ›› ብሎ ከተናገረላቸው መላእክት ውስጥ የሚመደብ ሲሆን የሰባቱም ሊቃነ መላእክት አለቃ እንዲሆን እግዚአብሔር መርጦ ሹሞታል፡፡ ይህ ታላቅ መልአክ ያደረጋቸው የሠራቸው እጅግ ብዙ የሆኑ ተአምራት አሉት፡፡

ስለዚህ ስለ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ክብር፤ ጠባቂነትና አማላጅነት ከአባቶቻቸው የተማሩትን በኑሮአቸው ያዩትን አባቶቻችን ጽፈዋል፡፡ ስለ ቅዱስ ሚካኤል ከጻፉት አባቶች መካከል የተወሰኑትን ለመጥቀስ ያክል፡

  • + ዮሐንስ አፈወርቅ
  • + ኤዎስጣቴዎስ ዘአንፆኪያ
  • + ቅዱስ መቃርዮስ
  • + ቅዱስ ያሬድ
  • + አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
  • + የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ አባዲማቴዎስ ናቸው፡፡

እኛም የአባቶቻችንን አንደበት አንደበታችን አድርገን በኅዳር 12 ክቡር ገናና የሆነ ቅዱስ ሚካኤል ካደረጋቸውና ከሠራቸው ብዙ ተአምራት ውስጥ የተወሰኑትን በመልአኩ ተረዳኢነት እንዲህ ብለን እንናገራለን አንጽፋለን፡፡

ንግስት ክሌዎፓትራ ‹‹ሳተርን›› ለሚባለው ጣዖት የሠራችው ቤተ ጣዖት በእስክንድርያ ነበር፡፡ ይህ ቤተ ጣዖት እስከ እስክንድርያው ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ /312 – 326/ ዘመን ድረስ ነበር፡፡ እለ እስክንድሮስ ሊያጠፋው ሲነሣ ሕዝቡ ከልቡ ገና የአምልኮ ጣዖት ስላልጣፋ 18 ፓትርያርኮች ያልነኩትን አንተ ለምን ታፈርስብናለህ ብለው ተቃወሙት፡፡ እለ እስክንድሮስም ሕዝቡን መክሮና አስተምሮ የሳተርን በዓል ይውልበት በነበረው ዕለት የቅዱስ ሚካኤልን በዓል እንዲያከብሩ አውጆ ቤተ ጣዖቱንም በቅዱስ ሚካኤል ስም ሰይሞ ቤተክርስቲያን አደረገው፡፡ ከዚህ በኋላ በቅዱስ ሚካኤልም ስም አብያተ ክርስቲያናት መታነጽ ጀመሩ በዓሉ በዚህ ቀን እንዲከበር ተወስኗል፡፡

እንዲህም ሆነ የእግዚአብሔር ወዳጅ የሆነ ስሙ ዱራታዎስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፡፡ የሚስቱም ስም ቴዋብለት ነው፡፡ እነርሱም ሁልጊዜ ያለ ማቋረጥ የዚህን የከበረ መልአክ የሚካኤልን የበዓሉን መታሰቢያ ያረጉ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ በሀገር ውስጥ ችግር በሆነ ጊዜ ገንዘባቸው አለቀ፡፡ በዚህም የተነሳ ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ሚካኤል ለበዓሉ መታሰቢያ የሚያደርጉትን አጡ፡፡ ዱራታዎስም ሽጦ ለበዓሉ መታሰቢያ ያደርገው ዘንድ የእርሱን ልብስና የሚስቱን ልብስ ይዞ ወጥቶ ሄደ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በታላቅ መኮንን አምሳል ለዱራታዎስ ተገለጠለት፤ ቅዱስ ሚካኤልም ዱራታዎስን ወደ በጎች እንዲሔድና በእርሱ ዋስትና በአንድ ዲናር አንድ በግ እንዲወስድ አዘዘው፤ ሁለተኛም ወደ ዓሣ አጥማጅ ሔዶ አንድ ዓሣ እንዲወስድ አዘዘው፡፡ መልአኩም ወደ ቤት ሳይደርስ የዓሣውን ሆድ እንዳይቀድ አስጠነቀቀው፡፡ ወደ ባለ ስንዴም እንዲሔድና የሚሻውን እንዲሁ በእርሱ ዋስትና እንዲወስድ አዘዘው ዱራታዎስም ቅዱስ ሚካኤል እንዳዘዘው አደረገ፡፡

ወደ ቤቱም በተመለሰ ጊዜ በረከትን ሁሉ ቤቱ ተመልቶ አገኘው፤ እጅግም አደነቀ፤ የዚህንም የከበረ መልአክ የበዓሉን መታሰቢያ እንዳስለመደው አደረገ፡፡ የተራቡ ድሆችን ሁሉንም ጠርቶ መገባቸውና ወደ ቤታቸው አሰናበታቸው፡፡

ከዚህም በኋላ ለዱራታዎስና ለሚስቱ ቅዱስ ሚካኤል ለሁለተኛ ጊዜ ተገለጠላቸው ዱራታዎስንም የዓሳውን ሆድ እንዲሰነጥቅ አዘዘው፤ በሰነጠቀውም ጊዜ ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር በዓሳው ሆድ ተገኘ፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ዱራታዎስንና ቴዋብስታን እንዲህ አላቸው፡፡ ‹‹ከዚህ ዲናር ወስዳችሁ ለባለ በጉ ለባለ ዓሳውና ለባለ ስንዴው ዕዳችሁን ክፈሉ የቀረውም ለፍላጎታችሁ ይሁናችሁ፤ እግዚአብሔር አስባችኋልና በጎ ሥራችሁን መስዋዕታችሁን ምጽዋዕታችሁን በዚህ ዓለም አሳመረላችሁ፡፡ በኋላኛውም መንግስት ሰማያትን አዘጋጅቶላችኋል፡፡››

በአንድ ዘመን ብዙ ሰዎች ከግብፅ አውራጃ መጥተው ወደ ባሕር ማዶ ሄዱ፡፡ ከባሕሩም በደረሱ ጊዜ በመርከብ ላይ ተሳፍረው ከየብሱ ጥቂት በራቁና ወደ ባሕሩ መካከል በደረሱ ጊዜ ጽኑ ነፋስ ተነሳባቸው ለመስጠም እስኪ ደርሱ ድረስ፡፡

የማዕበሉ ሞገድ እየጨመረ እየጸና ከፍ አለ፡፡ ታላቅም ማዕበል መጥቶ ሊገለብጣቸው ደረሰ፡፡ ፍጹም ጥፋትና ክፉ ሞት እንደ መጣባቸው ባዩ ጊዜ ጽኑ ሐዘን ያዛቸው፡፡ የሚያድናቸው የሚያጽናናቸው አጥተው ተስፋ ቆረጡ፡፡ ያን ጊዜ እንዲህ ብለው ጮኹ፡፡

‹‹የመላእክት አለቃቸው ግሩም ገናና የምትሆን ሚካኤል ሆይ የተአምራትና የይቅርታ መልአክ ነህና፡፡ ልዑል ቸርነቱን የሚገልጥብህ መልአክ ሆይ! እግዚአብሔር ፍቅሩን የሚያስታውቅብህ መልአክ ሆይ ወደኛ ተመልከት እርዳን፡፡ የተጨነቅን እኛን አድነን፡፡ ከመጣብን ሞትና ጥፋት እንድን ዘንድ ስለኛ ወደ ፈጣሪህ ወደ ፈጣሪያችን ወደ እግዚአብሔር ለምንልን፡፡ አሁን የሞት መጋረጃ ዓይናችንን ሸፍኖታልና፡፡ ፍጹም የጥፋት ጥላንም አይተናታልና›› ብለው በፍጹም ልቦናቸው ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፡፡ በመርከብ ውስጥ ያሉት ሁሉ ጽኑ ለቅሶ እያለቀሱ መራራ እንባ እያፈሰሱ ጮኹ፡፡

ከባሕር ጽኑ ማዕበል ከሞት ያድናቸው ዘንድ ያን ጊዜ በዚያች ሰዓት እግዚአብሔር የልቦናቸውን ሐዘንና ልመናቸውን ሰማቸው፡፡ ያን ጊዜም ይገዳቸው ዘንድ ቸር መልአኩን ሚካኤልን ላከላቸው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ከሰማይ ወረደ መርከቡን በእጁ ይዞ ሳበው፡፡ በመርከቡ ውስጥ ያሉትንም ወደ የብስ አወጣቸው፡፡ በደኅናቸው ተሻገሩ፤ ክፉ ነገር ጥቂትስ ስንኳ ፈጽሞ አላገኛቸውም፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ገናና የሆነ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ልመናውና አማላጅነቱ ፈጽሞ ይጠብቀን፡፡ ከጽኑ ጠላት እጅ በክንፎቹ ጋርዶ ይሰውረን፡፡ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

ምንጮች

-ድርሳነ ሚካኤል ዘኅዳር

-መጽሐፈ ስንክሳር ዘኅዳር

-የሐመር መጽሔት 1993 ዓም መጋቢትና ሚያዚያ

ቅዱስ ምካኤል ወዳጅ ነህ ለሁሉ፤ ዛሬም ቆመሃል በኪዳንህ ላሉ። አሜን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ካኤል ሆይ ስለእኛ ስለሰው ልጆች በጌታ ፊት ቁምልን ምልጃና ጸሎትህ ተራዳእነትህ ጥበቃህ ለዘወትር አይለየን!! አሜን።

አስደናቂ አይደለም!? ላይ ያቀረብኩትን መልዕክት ከላኩ በኋላ፡ ቅዱስ ሚካኤልን ስጠራና ይህን ድህረገጽ ስከፍት፤ ያው የአምላኬ መልአክ በላዬ በራ፦

One Of The Biggest Alternative Media Networks In Italy Is Spreading Anti-Immigrant News And Misinformation On Facebook

______

Antivenom vs Venom | ሊቀ መላእክት ሚካኤል (Michael)በእነዚህ ገዳዮች ላይ ስይፉን ዘርግቶባቸዋል፤ ይገርማል ሁሉም ስማቸው በ “Mይጀምራል

  • ሜርከል (Merkel) ወደ ሞት እየሄደች ነው
  • ሙጋቤ (Mugabe) ወደ ሞት እየሄደ ነው
  • መንግስቱ (Mengistu) ወደ ሞት እየሄደ ነው
  • ሜይ (May) ወደ ሞት እየሄደች ነው
  • ማክሮን (Macron) ወደ ሞት እየሄደ ነው
  • ማንሰን (Manson) ሞተ
  • መሀመድ (Mohammad) ሞቷል
  • ሙስሊም (Muslim) እየሞቱ ነው

______

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: