Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • May 2023
    M T W T F S S
    1234567
    891011121314
    15161718192021
    22232425262728
    293031  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ተዋሕዶ ክርስቲያናት’

ይገርማል! | የተዋሕዶ ልጆች በሊብያ እና በናዝሬት በአንድ ዕለት ነው የተሰዉት | በትንሣኤ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 26, 2020

+አንድ ማሳሰቢያ!+

የአውሬውን የ”Copyright” ጨዋታ መብት በመጠቀም ይህን ቻነል ለማዘጋት እየሠሩ ያሉ “ተዋሕዶ ነን” የሚሉ ዩቱበሮች፦

👉 ቻነል ፦ “Lule Quanquayenesh (ሉሌ ቋንቋዬ ነሽ)”

👉 Content removed by Lule Quanquayenesh (ሉሌ ቋንቋዬ ነሽ)

👉 ቪዲዮዎች፦

+ “ኢትዮጵያ ማለት ቤተክርስቲያን ናት ፤ እየታረዱላት ያሉትም የተዋሕዶ ልጆች ናቸው”

+ “የሰይጣን ምልክት 666 ነው ፥ የክርስቶስ የሆኑት ደግሞ ባንገታቸው ላይ ያለው ማሕተብ ነው”

👉 ቻነል Semayat/ ሰማያት

👉 ቪዲዮ፦ + “በዶክተሮች ሊፈታ የማይችለው ወረርሽኝ በጻድቁ ማእጠንት ይታጠናል | የማእጠንት ፀሎት በአሜሪካ”

Content removed by Semayat የደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ወአቡነ ሀብተማርያም የማእጠንት ፀሎት በተወሰኑ የቨርጂንያ መንደሮችና

እንግዲህ እነዚህ ዩቱበሮች አውሬው ተነካባቸው መሰለን በምናቀርበው ነገር የተደሰቱ ሆነው አላገኘናቸውም። መልስ እንዲሰጡን ጊዜ ሰጥተናቸው ነበር።

ማንም የሜዲያ ሰው ነኝ ማለት በሚችልበትና መላው የሰው ልጅ በወረርሽኝ ጉዳይ በተጠመደበትና በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ወገን መቀራረብና መፈቃቀር በሚኖርበት በዚህ የጭንቀት ዘመን ነጋዴ እንጅ አንድ “ክርስቲያን ነኝ” የሚል አካል በጭራሽ “Copyright“ የተባለውን ዝባዝንኬ እንደ መሀመዳውያኑ መጠቀም የለበትም። በተለይ በፋሲካ ሰሞን፤ ያውም “ሰለጠነች” በምትባለዋ አሜሪካ እየኖሩ። የኛን ቪዲዮዎች ማንም መጠቀም ይችላል፤ እንዳውም ደስ ይለናል!

ልብ ብላችሁ ከሆነ እንደ ውቂያኖስ ሰፊ በሆነ የዩቱብ ቪዲዮዎች ዓለም “Copyright“ን በብዛት የሚጠቀሙት ኢትዮጵያዊ ነን” የሚሉ ዩቱበሮች ናቸው። ታዲያ ይህ የስግብግብነት፣ የምቀኝነት፣ የክፋትና የጠላትነት መገለጫ አይደለምን? 21ኛው ክፍለ ዘመን ፤ ምናልባትም ኢንተርኔት የሚባል ነገር በቅርቡ እልም ብሎ ሊጠፋ በተዘጋጀበት ወቅት በራስህ ወገን ላይ ይህን መሰል እቃ እቃ ጨዋታ መጫወቱ አያሳዝንምን? ሰው እንዲማርበት ነው፤ ““ኮፒራይት” ከ666ቱ ምልክቶች አንዱ ነው፤ የአውሬው ባሪያ ከመሆን ለመዳን ከዩቱብና ጓደኞቹ ገንዘብ አትቀበሉ” ለማለት ነው።

ይህ ቀላል ነገር ነው፤ ዋናው እና ትልቁ ተል ዕኳችን አውሬውን መታገል ነው፤ ሕዝባችንን የሚያሰቃይብንን፣ ሕፃናቱን የሚገድልብንን፣ ካህናትን የሚያስርና የሚገድልብንን፣ እናቶችን የሚያፈናቅልብንን የአውሬ ሥርዓት ማጋለጥ ነው፤ የተሰውትን ሰማዕታት ወገኖቻችንን ማስታወስ ነው።

ለማንኛውም ሌላው ቻነላችን እዚህ ይገኛል፦

+++ዘመነ ኢትዮጵያ+++

ከምስጋና ጋር

___________________________________

Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

የክፉ ትንቢት መፈጸሚያዎቹ ግራኝ አብዮት እና ኢሳያስ አፈቆርኪ ይህን ሲያዩ ምን ይሰማቸው ይሆን?

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 1, 2019

በጣም አሳዛኝ ነው፤ መከራቸው በዛ፡ ወገኖቼ ፥ ነፍሳቸውን ይማርላቸው!

[፪ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕራፍ ፬፥፲፯፡፲፰]

የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ ቀላል የሆነ የጊዜው መከራችን የክብርን የዘላለም ብዛት ከሁሉ መጠን ይልቅ ያደርግልናልና፤ የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው።

___________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

ሰማዕታት ተዋህዶ በ ሊብያ | ፬ኛ አመት ሙት መታሰቢያ ሳምንት

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on April 22, 2019

ሚያዝያ ፲፩/ ፪ሺ፯ ዓ.ም – ከ፬ ዓመታት በፊት፡ ልክ በዚህ ዕለት ወንድሞቻችን ሰማዕትነትን የተቀበሉበት ቀን ነው።

የሰማዕታት ደም የቤተ ክርስቲያን ችግኝ ነው! በረከታቸው ይድረሰ!

ምነው ወንድሞቻችንን እረሳናቸው? ሌሎቹስ ይተውት፡ የራሳቸው ጉዳይ! ግን፡ ማህበራዊ ሜዲያዎች ምነው ፀጥ አልን? አራተኛ አመትን አስመልክቶ አንድም የቀረበ የመታሰቢያ ጽሑፍ ወይም ቪዲዮ እስካሁን አላየሁም፤ ለምን? ምን መጣብን? ግድየለሽነት ይሆን?

ከአራት ወራት በፊት “የሰላሳ አራቱ ተዋሕዶ ሰማዕታት መቃብር በሊቢያ ተገኘ” የሚለውን ቪዲዮ አቅርቤ ነበር፤ ነገር ግን ጉዳዩ የት ደረጃ ላይ እንደደረስ፣ ወይም የ፴፬ቱን ሰማዕታት አካላትን ወደ አገራቸው ለመመለስ ምን እየተሠራ እንደሆነ ለማወቅ በጣም ተቸግረናል። ከመንግስት ብዙ መጠበቅ የለብንም፤ እንዲያውም የግራኝ አህመድ መንግስት በዚህ ጉዳይ ላይ ቆሻሻ እጁን በጭራሽ ማስገባት የለበትም፤ አይመለከተውምና! ግን ቤተ ክህነት ምን እየሠራች ነው? በተለይ፡ በመካከለኛው ምስራቅ ይኖሩ የነበሩትና በዚህ ረገድ ልምዱም ያላቸው አቡነ ማቲያስ ይህን የቤት ሥራ የመሥራት ግዴታ አለባቸው እኮ! ምን እየሠሩ ነው እሳቸው? ኧረ ዝምታው አደነቆረን!

[ትንቢተ ሆሴዕ ምዕራፍ ፬፥፮]

ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤ የአምላክህንም ሕግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ ልጆችህን እረሳለሁ።

[የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ ፮፡]

አምስተኛውንም ማኅተም በፈታ ጊዜ፥ ስለ እግዚአብሔር ቃልና ስለ ጠበቁት ምስክር የታረዱትን የሰዎች ነፍሳት ከመሠዊያ በታች አየሁ

በታላቅ ድምፅም እየጮኹ። ቅዱስና እውነተኛ ጌታ ሆይ፥ እስከ መቼ ድረስ አትፈርድም ደማችንንስ በምድር በሚኖሩት ላይ እስከ መቼ አትበቀልም? አሉ

፲፩ ለእያንዳንዳቸውም ነጭ ልብስ ተሰጣቸው፥ እንደ እነርሱም ደግሞ ይገደሉ ዘንድ ያላቸው የባሪያዎች ባልንጀራዎቻቸውና የወንድሞቻቸው ቍጥር እስኪፈጸም ድረስ፥ ገና ጥቂት ዘመን እንዲያርፉ ተባለላቸው

_____________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: