Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on August 11, 2020
በቤይሩት የቅድሱ ዲሚትሪዮስ ግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አባት አባ ዮኢል ናሲፍ ነው ይህን ለቢቢሲ የተናገሩት።
የቅዱስ ዲሚትሪዮስ ግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የሚገኘው የቤይሩት ፍንዳታ ከተከሰተበት ቦታ አንድ ኪሎ ሜትር ብቻ ርቆ ነው፡፡
አባ ዮኢል ናሲፍ ቤተክርስቲያኑ የደረሰበትን ጉዳት ለመመርመር በፍጥነት ወደ ቤተክርስቲያኑ በመሮጥ ቤተክርስቲያን ሲገቡ የቤተክርስቲያኑ የመጀመሪያ ክፍል(ቅኔ ማህሌት)ሙሉ በሙሉ ወድሟል፡፡ ነገር ግን ቤተ መቅደሱ ለጭረት እንኳን አልተነካም ነበር ፥ በፍንዳታው ወቅት ሁሉ እንደበራ የቆየውን የዘይት ሻማ መብራት ጨምሮ፡፡
____________________________________
Like this:
Like Loading...
Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith, Infos | Tagged: Altar, ሊባኖስ, መቅደስ, ቤሩት, ቤተ መቅደስ, ቤተ ክርስቲያን, ቤይሩት, ተስፋ, ተዓምር, ኢየሱስ ክርስቶስ, እምነት, ግሪክ ኦርቶዶክስ, ፍንዳታ, Beirut, Blast, Greek Orthodox Church, Lebanon, Miracle | Leave a Comment »
Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 13, 2019
ይህ የተነሳው ከምድራችን በሦስት መቶ ሃምሳ ኪሎሜትር ከፍታ ላይ ከሚገኘውና ዓለማችንን በመዞር ላይ ካለው ከአለም አቀፉ የጠፈር ምርምር መእከል (ISS) ነው። ይህን ቪዲዮ በአጋጣሚ ማታ ላይ ማየቴ ነበር። አስገራሚ ነው…እንዴት እንደገባሁ እንኳን አላውቅም።
ጥሩ ዓይን ያለው/ያላት ወገናችን “ልቡን” ስለጠቆሙኝ፡ ከምስጋና ጋር፡ ተሻሽሎ የቀረበ።
በፈርንጁ ዓለም ዘንድ ሙሉዋ ጨረቃና 13 የሚያርፍበት ዕለተ አርብ ብዙ ፈተና እና መዘዝ ያለው ነው። ያለምክኒያት በዚህ ወቅት የኢትዮጵያን ጠላት ገዳይ አብዮትን አልሸለሙትም፣ ያለምክኒያት በዚሁ ወቅት የዓለም ባንክ ገንዘቡን ሊያጎርፍለት ቃል አልገባለትም፣ ያለምክኒያት በዚሁ ወቅት በዓለ ጥምቀትን አውሬው ዩኔስኮ አልመዘገበውም።
ባለፈው ቪዲዮ ላይ፡ አውሬው ዓይኑን በጥምቀት፣ ቍርባንና በተቀሩት ምስጢራተ ቤተክርስቲያን ላይ ማነጣጠሩን አውስቼ ነበር። ያው… እመቤታችንም እየጠቆመችን እኮ ነው…
በዓታ ለማርያም | መልአኩ ቅዱስ ፋኑኤል ኅብስትና ሰማያዊ ጽዋዕ ይዞ ከሰማይ ወረደ
እንኳን አደረሰን
ቅድስት ድንግል ማርያም በ፶፻፬፻፹፭ ዓመተ ዓለም ከሐና እና ከኢያቄም በፈቃደ እግዚአብሔር ተወልዳ እስከ ሦስት ዓመት ድረስ የኖረችው በወላጆቿ ቤት ነበር፡፡ ከዚህ በኋላ ኢያቄምና ሐና የተሳሉትን ስእለታቸውን አስታውሰው ወስደው ለቤተ እግዚአብሔር ሰጧት፤ ካህኑ ዘካርያስም ስለምግቧ በመጨነቁ ሕዝቡን ሰብስቦ ሳለ መልአኩ ፋኑኤል ኅብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ይዞ ከሰማይ ወረደ፤ ዘካርያስ ለእርሱ የመጣ ሀብት መስሎት ታጥቆ እጅ ነስቶ ቢቆም ወደ ላይ ራቀበት፡፡ ከስምዖን ጀምሮ በዚያ የተሰበሰቡት ሰዎችም በተራ ቢሞክሩ በተመሳሳይ ወደ ላይ ራቀባቸው፡፡ ምን አልባት ለእንግዶች የመጣ ሀብት እንደሆነ ብለው ሐና እና ኢያቄም እንዲቀርቡ አደረጓቸው፤ ለእነርሱም ራቀባቸው፤ ዘካርያስም ሐናን ‹‹እግዚአብሔር የሚያደርገውን የሚያውቅ የለምና ልጅቷን ትተሸ ወደዚህ ነይ›› ባላት ጊዜ ቅድስት ማርያም ድክ ድክ እያለች እናቷን ስትከተል መልአኩ ፋኑኤል ወደ እርሷ ቀርቦ አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክንፉን ጋርዶ መግቧት ዐረገ፤ ሊቀ ካህናቱም ሕዝቡም የምግቧ ነገር ከተያዘልን በቤት እግዚአብሔር ትኑር ብለው አስገብተዋታል፡፡
ድንግል ማርያምም ሰማያዊ ኅብስትና መጠጥ እየተመገበች ፲፪ ዓመት በቤተ መቅደስ ኖረች፡፡ ፲፭ ዓመት ሲሞላት ግን ለአቅመ ሔዋን በመድረሷ ከቤተ መቅደስ ትውጣልን በማለት አይሁድ በጠላትነት ተነሱባት፡፡ ካህኑ ዘካርያስም ይህን ሰምቶ እመቤታችንን ጠየቃት «ኦ ወለተ እስራኤል እፎ ትፈቅዲ ትንበሪ፤ ልጄ እንደምን ሆነሽ ልትኖሪ ትወጂያለሽ?» አላት፡፡ እርሷም «ከእግዚአብሐር በታች ያለኸኝ አባት አንተ ነህ፤ በዚያውም ላይ እናት አባቴ አደራ ያሉህ አንተን ነው፤ ወደ እግዚአብሔር አመልክትልኝ፤» አለችው፡፡ ዘካርያስም ጸለየ፤ እግዚአብሔርም ከነገደ ይሁዳ ሚስቶቻቸው የሞቱባቸውን በትራቸውን ሰብስበህ በቀዳማይ ሰዓተ ሌሊት ከቤተ መቅደስ አግብተህ ስትጸልይ አድረህ በቀዳማይ ሰዓተ መዓልት አውጣው ብሎ ምልክትም እሳይህአለው ብሎ ነገረው፡፡ እርሱም እንዳለው አድርጎ በማግሥቱ በትሮቹን አውጥተው ቢያዩ የዮሴፍ በትር አብባና አፍርታ ተገኘች፡፡ ከበትሩ ጫፍ ላይ «ኦ ዮሴፍ ወልደ ዳዊት ዕቀባ ለማርያም ፍኅርትከ፤ ዮሴፍ ሆይ እጮኛህ ማርያምን ጠብቃት፤» የሚል ጽሑፍ አገኙ፤ርግብም መጥታ በራሱ ላይ አርፋለች፤ ስለሆነም ዮሴፍ እንዲጠብቃት ተወሰነ፡፡
የኢትዮጵያ ቀለማት / የማርያም መቀነት
የማርያም መቀነት ወርደሽ ንገሪያቸው
ወራሪና ባንዶች ካለ ባህሪያቸው
አይቶ ለመረዳት የታወሩ ናቸው
የኢትዮጵያ ሰንደቅ እኔ ነኝ በያቸው
በሠማዩ ላይ ሲታይ ቀለም
የሷ ነው እንጂ ሌላ አይደለም
+__________________________+
Like this:
Like Loading...
Posted in Curiosity, Ethiopia, Faith | Tagged: ሊቀ መላእክት ቅዱስ ፋኑኤል, ሐና, መንኮራኵር, ምድራችን, ቀስተ ደመና, ቅድስት ማርያም, በዓታ ለማርያም, ቤተ መቅደስ, ኢያቄም, ዘካርያስ, የማርያም መቀነት, የኢትዮጵያ ቀለማት, ዮሴፍ, ጠፈር | Leave a Comment »