ባለፈው ዓመት ላይ ሕዝብ ያለመረጠውና ለማ መገርሳ የተባለው ፖለቲከኛ የኢትዮጵያ አየር መንገድን፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን እና የኢትዮጵያ ቴሌኮምን ለመሸጥ በድብቅ ወደ ጀርመን ሄዶ እንደነበር እኅተ ማርያም ጠቁማን ነበር። የጉዞው ዋና ዓላማ ኢትዮጵያን ቀስበቀስ ማጥፋት ይቻላቸው ዘንድ የኤኮኖሚ ጥቅም ያስገኝልናል በሚል የማታለያ ስልት በቅድሚያ “ኢትዮጵያ” የሚለውን ቃል የያዙትን ሦስቱን ተቋማት ለኢትዮጵያ ጠላቶች ማስረከብ ነው።
እንደዚሁ ከወራት በፊት በኢትዮጵያ ሕዝብ ያለተመረጠው አብይ አህመድ የተባለ ፖለቲከኛ ይህን ጉዳይ አስመልክቶ ከፈረንሳዩ ባላጋሩ ኤማኑኤል ማክሮን ጋር የሚከተለውን መግለጫ አውጥቶ ነበር፦
„Joint Declaration Between PM Abiy and President Macron“ በጥቂቱ:
Both States welcome the intensification of the French Development Agency’s activities in Ethiopia. For this purpose, France and Ethiopia have signed two declarations of intent regarding:
- the support to Ethiopian Airlines investment program;
- Macron and Abiy also pledged to increase cultural cooperation, especially on World Heritage sites such as the rock-hewn churches of Lalibela. France will contribute to the maintenance and renovation of the site, Abiy said.
-
Macron announced he will visit Ethiopia in March. (M & M = Mason)
የእነዚህ ከሃዲዎች ዕቅድ “ኢትዮጵያ” የሚለውን ስም ለማጥፋት ነው። ሰሞኑን እንደምንሰማው፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን እያዘረፉ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ገጠመን ይላሉ፣ በኢትዮጵያ ቴሌኮም ደግሞ አስፈላጊውን ግልጋሎት የመስጠት አቅም የለውም ለማለት የስልክ መስመሮችን ሆን ብለው ይቆራርጣሉ፣ የኢንተርኔት ግኑኝነት እንዳይኖር አገልጋዮችን ይዘጋሉ። በኢትዮጵያ አየር መንግድም እንደዚሁ አደጋዎች እንዲዘወትሩ እየተደረገ ነው። “አልቻልንም፤ ባካችሁ እርዱን!” ለማለት፤ የአውሬውን Problem – Reaction – Solution ፎርሙላ በመጠቀም።
ለመሆኑ እነዚህ ሕብ ያልመረጣቸው የቀበሌ ፖለቲከኞች ምን መብት አላቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድን የመሰለ የሰባ–ዓመት–እድሜ–ያለው–ያገራችን–ኩራትን ለባዕዳኑ አሳልፈው ለመስጠት የተዘጋጁት? ማን ፈቀደላቸውና?
አዳዲስ መረጃዎች፦
-
+ በኢትዮጵያ የኢንተርኔት ግንኙነት ጠቅላላ ቆመ
- + የኢትዮጵያ ቴሌኮምን እነዚህ ባዕዳውያን ተቋማት ሊወርሱት ነው ይለናል አሁን የወጣው ዜና፤
ወራሾቹ፦
-
+ ደቡብ አፍሪቃ
-
+ ፈረንሳይ
-
+ የተባበሩት አረብ ኤሚራቶች
Ethiopia Plans To Issue Telco Licences by Year-End
Vodafone, South African operator MTN, France’s Orange and Etisalat of the United Arab Emirates are likely to be among the leading contenders vying for entry into the Ethiopian market.