በምዕራቡ ዓለም ብዙ ዕውቅናንና ተወዳጅነትን ካተረፉት ድንቅ የክርስትና ጠበቃዎች መካከል ትውልደ ሕንዱ ደራሲና መምህር ዶ/ር ራቪ ዘካርያስ አንዱ ናቸው። በግንቦት ወር ላይ ሕይወታቸው ያረፈው (ነፍሳቸውን ይማርላቸው!) እኝህ ካናዳዊ–አሜሪካዊ ኢ–አማንያንን ያንቀጠቀጡ፣ ሞርሞኖችን ጸጥ ያሰኙ፣ ሸሆችንና ኢማሞችን ጨምሮ በጣም ብዙ ሙስሊሞችን ከእስልምና ባርነት ነፃ ያወጡ ግለሰብ ነበሩ። በንግግር የማሳመን ችሎታቸው በጣም የሚደነቅ ነበር። እናዳምጣቸው፦
ከዕለታት አንድ ቀን በማሌዢያ ጥንታዊ በሆነው የእስልምና ዩኒቨርሲቲ ንግግር እያደርኩ ነበር። በወቅቱ በጣም ውጥረት ነበር፤ እስልምና እምነታቸውን እንደማላጠቃባቸው፤ ነገር ግን ክርስትና እምነቴን እንደምከላከል ቃል ገባሁላቸው፤ ስለ ክርስትና የፈለጉትን እንዲጠይቁኝ ነገርኳቸው።
የማላይ እስላም ዩኒቨርሲቲ የእስላማዊ ጥናቶች መምሪያ ሊቀመንበር ባሃራዲን የተባለች ሴት ነበረች፤ አሉ የተባሉትን ሙላዎችና የእስልምና ‘ሊቆች‘ በመጀመሪያው ረድፍ ወንበር ላይ ቦታ እንዲይዙ አድርጋቸው ነበር፤ በጣም ውጥረት የተሞላበትና አስፈሪ ሁኔታ ነበር።
መከላከያዬን ማቅረብ የጀመርኩት ኢየሱስ ክርስቶስ በቃሉ ውስጥ ነኝ ስላለው አምላክነቱ በማውሳት ነበር።
ለ፵፭ ደቂቃ ያህል ውጥረት በተሞላበት መልክ ለጥያቄዎቻቸው ሁሉ መልስ ሰጠሁ፤ ከዚያም ወደ ሊቀመንበሯ ጽሕፈት ቤት እንዳመራሁ በኢየሩሳሌም ስላገኘሁትና የሃማስ መስራቾች ከነበሩት መካከል አንዱ ስለሆነው ሸህ ታሪክ ነገርኳት።
ሽሁ የክርስቶስን አምላክነት በሚያሳምን መልክ ሳስረዳው “ሌላ ጊዜ ባገኝህ ደስ ይለኛል” ብሎ ሁለቱንም ጉንጮቼን ስሞ ተሰናበተኝ።” አልኳት።
የዩኒቨርሲቲው ሊቀመንበሯም “አቶ ዘካርያስ፤ ክልክል ባይሆን ኖሮ እኔም እንደ ሸሁ ለስንብት ጉንጮችህን እስማቸው ነበር፤ ለዩኒቨርሲቲው እጅግ በጣም ጠቃሚ የሆነ ትምህርት ነው ዛሬ የሰጠኸንና” አለችኝ። እኔም፤ ‘ወ/ሮ ባሃራዲን እኔ የክርስቶስ አምባሳደር ነኝ” አልኳት።
በዚህ ወቅት አንድ ክርስቲያን ፕሮፌሰር (ሊ) ወደኔ መጥቶ እንዲህ አለኝ፤
“ዶ/ር ዛካርያስ ዛሬ ምን ያህል ወሳኝ ቀን እንደሆነ ታውቃለህን? ፥ ደቡብ አፍሪቃዊው ፀረ–ክርስቶስ፣ መርዘኛ፣ ጉረኛ፣ ጠላተኛ የእስልምና ‘ሊቅ‘ አህመድ ዲዳት ዛሬ እዚህ መጥቶ ክርስትናን በመናቅ በአጸያፊ ሁኔታ ሲሰድብ፣ ሲያንቋሽሽና ሲያጣጥል አይቼ “ይህ ሰው ይህ ሰው ሊሠራው የፈለገው ነገር ምንድር ነው? ምን ይጠቅመዋል?| ብዬ እራሴን ጠየቅኩ።
በዚህ ወቅት በአዳራሹ እጄን አንስቼ “ፕሮፌሰር ዲዳት እኔ ክርስቲያን ነኝ ለምንድን ነው ክርስትናዬ እምነት የሚጣልበት ሃይማኖት አይደለም” ያልከው ብዬ ጠየቅኩት፤ ወዲያውም አህመድ ዲዳት ቆጣ ብሎ፤ “ወደዚህ ና! መድረኩ ላይ ውጣ!” አለኝ።
መድረኩ ላይ እንደወጣሁም አህመድ ዲዳት እጁን በሰፊው ዘርግቶ ፊቴ ላይ ክፉኛ አጮለኝ፤ በዚህ ወቅት መቆም እስኪያቅተኝ ጉልበቴ መንቀጥቀጥ ፊቴም መጮኽ ጀመረ፤ ዲዳት ግን „ሌላኛውን ጉንጭህን አዙረው” አለኝ።
በዚህ ወቅት “አምላኬ በእውነት እፈልግሃለሁ” እያልኩ መጸለይ ጀመርኩና ጉንጬን አዞርኩለት፥ አህመድ ዲዳትም ቡጢውን ሰብስቦ “ጉዳዩን ፈጣን ማድረግ አለብን፤ ሸሚዝህን አውልቅ!” አለኝ፤ እኔም ሸሚዜን አውልቄ ሰጠሁት፤ “ሱሪህንም አውልቀህ ስጠኝ” አለኝ ፥ እኔም በአዳራሹ ሰልሚገኙት ተማሪዎቼ ዘወር ብዬ “ይቅርታ አድርጉልኝ፤ ግን ጥያቄውን ለማሟላት ሱሪየን አውልቄ እሰጠዋለሁ” አልኳቸው።
መድረክ ላይ በተማሪዎቼ ፊት እርቃኔን ቀረሁ፤ ሸሚዜንና ሱሪየን ለአህመድ ዲዳት አስረክቤ ወደ ጽሕፈት ቤቴ አመራሁ፤ እዚያም ከፊቴ ህመም ጋር በማልቀስ አምላኬን ለሰጠኝ ብርታት አመሰግነው ጀመር።
በዚህ ወቅት በሩ ተንኳኳ፤ እንደከፈትኩትም፤ ብዙ ተማሪዎች ረጅም ሰልፍ ሠርተው አየኋቸው፤ 98% ሙስሊም ተማሪዎች ናቸው። አህመድ ዲዳት በክርስቲያኑ ፕሬፌሰር ላይ ለፈጸመው ወራዳ ተግባር ይቅርታ ለመጠየቅ ሁሉም ተንበርክከው መለመን ጀመሩ።
ፍቅር ጭፍን ጥላቻን ያሸንፋል ፥ ጥላቻ ማንንም ከማጥፋቱ በፊት ጠይውን ያጠፋል ፥ ፍቅር በሰው ልብ ውስጥ ያሉትን ይዘቶች አሸንፏል ፣ በመጨረሻም ፣ ውጭውን ያሸንፋል።
ባንድ ወቅት ዝነኛው የቀድሞው የፈረንሳይ መሪ ናፖሊዎን ቦናፓርት እንዲህ ብሎ ነበር፤
“የታላቁ አሌክሳንደር እና የእኔ መንግስታት መጨረሻቸው ይመጣል፥ የክርስቶስ ግን ዘላለማዊ ነው፤ ምክኒያቱም እኛ በጦር መሳሪያ ሃይል ስላሸነፍን ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን በፍቅር ስላሸነፈ ነው”።