Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ሳዩዝ’

ይህ ከጠፈር ታይቶ አይታወቅም | መብረቅ በአፍሪቃ ደመና ላይ | መንኮራኩሯ በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on December 22, 2018

ባለፈው ኃሙስ ምድርን ከሚዞረው የዓለም አቀፋዊ የጠፈር ጣቢያ፣ ቤተ ሙከራ፡ ከአይ ኤስ ኤስ ሦስት ጠፈርተኞችን ይዛ ወደ ምድር ትመለስ የነበረችውን የሩስያዋን ሳዩዝ መንኮራኩርን በመቶ ኪሎሜትር እርቀት ላይ ሆኖ የሚከታተለው ካሜራ በመካከለኛው አፍሪቃ አስገራሚ የመብረቅ ብልጭታ ለማንሳት በቅቶ ነበር። ከዚህ በተጨማሪም፡ ወደ ካዛክስታን ታመራ የነበረችውን መንኮራኩር አጅበው የነበሩት ሦስት የመንኮራኩሯ ክፍሎች የተለያዩት ልክ በሰተሰሜኑ የኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ነበር።

የሚገርም ነው አቡነ ማትያስ የሩስያ ጉብኝታቸውን አቋርጠው ወደ ኢትዮጵያ የተመለሱት በዚሁ ዕለት በዚሁ የአውሮፓላን አየር መንገድ አቅጣጫ ነበር። በመካከለኛው አፍሪቃ በተለይ በኮንጎ የኤቦላ ቫይርስ ብዙ ሰዎችን እየገደለ ነው። ይህ ብልጭታ ምናልባት በአፍሪቃውያን ላይ በሽታዎችን እያሰራጩ፣ ህፃናቶቻቸውን እያደነዘዙ እና ሴቶቻቸውን መኻን እያደረጉ ያሉት የዓለማችንን ፈላጭ ቆራጮች እያስጠነቀቀ ይሆናል።

ለመሆኑ እዚያ ጠፍር ላይ ምንድን ነው እየሠሩ ያሉት? ሩሲያና ምዕራባውያኑ እዚህ ምድር ላይ ጠላታሞች እንደሆኑ አድርገው እርስበርስ ሲፎካከሩና ሲወቃቀሱ ይሰማሉ፤ ጠፈር ላይ ግን አብረው ይሠራሉ። ለምንድንስ ነው አንድም አፍሪቃዊ ወደ ጠፈር ተልኮ የማያውቀው?

__________________

Posted in Curiosity, Ethiopia | Tagged: , , , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: