Addis Ethiopia Weblog

Ethiopia's World / የኢትዮጵያ ዓለም

  • June 2023
    M T W T F S S
     1234
    567891011
    12131415161718
    19202122232425
    2627282930  
  • Archives

  • Categories

  • Recent Posts

Posts Tagged ‘ምስራቅ ኦርቶዶክስ’

የምስራቅ ኦርቶዶክሱ ሊቅ | በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ደኖች መንፈሳዊ ቅናት ይሰማኛል

Posted by addisethiopia / አዲስ ኢትዮጵያ on September 19, 2019

ይህን የተናገሩት ካናዳዊው ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ዶ/ር ዴቪድ ጉዲን ናቸው።

Christology and Eco-Theology: Safeguarding Ethiopian Tewahedo Church Forests

Dr. David Goodin (Canada) presents “Christology and Eco-Theology: The Centrality of Cyril of Alexandria in Safeguarding Ethiopian Tewahedo Church Forests” at the Inaugural Conference of the International Orthodox Theological Association (IOTA), with the theme Pan-Orthodox Unity and Conciliarity, held January 9 to 12, 2019, in Iasi, Romania.

https://www.ancientfaith.com/specials/iota/50_christology_and_eco_theology_safeguarding_ethiopian_tewahedo_church_fore

+ አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት አሁን ማሕበረሰባቸውን ለማበረታት ደኖቻቸውን ለማስፋፋት እየሞከሩ ነው፤ይህም አበረታች የሆነ ተግባር ነው።

+ በኢትዮጵያ ጫካማ የሆነ ቦታ ካየን፥ መሀከል ላይ በርግጥ ቤተክርስቲያን እንዳለ የማወቅ እድል ይኖረናል።

+ ደኖቹ የመጠለያ፣ ፀሎት የማድረጊያ እና የመቃብር ቦታዎች ሆነው ያገለግላሉ።

+ አብዛኛው የአገሪቱ ጫካ እያደገ የመጣውን የአገሪቱን የሕዝብ ቁጥር ለመመገብ ሲባል ለግብርና መስዋእትነት ወስዷል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር ከ 100 ሚሊዮን በላይ ነው፣ ይህም በዓለም 12 ኛ ደረጃ ትልቁ ነው። በተለይ ከ 1974-1991 .ም በሀገሪቱ የኮሚኒዝም ሥርዓት፡ በ “መሬት ለአራሹ” ዘመን፡ የደን ጭፍጨፋው አሳዛኝ የሆነ ደረጃ ላይ ደርሶ ነበር፤ በተለይም የቤተ ክርስቲያኒቱን ሰፋፊ ቦታዎች በመውረስ ደኖቻቸውን እየመነጠሩ ለእርሻ እንዲውሉ አድርገዋቸዋል። በአሁን ዘመን በአገሪቱ 5% ብቻ በደን የተሸፈነ ሲሆን፤ በሀያኛው ክፍለ ዘመን እስከ 45 በመቶ ነበር።

+ ምን ያህል ስብጥር እንደጠፋ በውል አናውቅም ፥ ነገር ግን ከጠበቅነው በላይ በጣም ጉልህ የሆነ የስብጥር መጠን መትረፉን እናውቃለን።

+ ደን ብዝሃህይወት ስብጥርን መጠበቅ ለእርሻ በጣም አስፈላጊ ነው ምክንያቱም በዓብያተ ክርስቲያናቱ ጫካዎች ውስጥ የሚኖሩት ብዙዎቹ ወፎች እና ነፍሳት ሰብሎችን ለማዳቀል እና ተባይን ለመቆጣጠር ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታሉና ነው።

+ ከግማሽ በላይ ሚሆኑት ኢትዮጵያ ሕዝቦች እናት የሆነችው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ደኖቿ የሰማይ መንግስትን በምድር ላይ የሚወክሉ ናቸው፤ እያንዳንዱ ፍጥረት የእግዚአብሔር ስጦታ ስለሆነ መኖሪያ ይፈልጋል

+ የተፈጥሮ አካባቢዎች መንፈሳዊ ክልል አካል የሆኑት እነዚህ ደኖች በባህልና በሳይንሳዊ መልኩም በጣም አስፈላጊ ናቸው።”

______________________

Posted in Ethiopia, Faith | Tagged: , , , , , , , , , , , , | Leave a Comment »

 
%d bloggers like this: